Monday, October 3, 2016

በመላው ኦሮሚያ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል።


Minilik Salsawi's photo.
በመላው ኦሮሚያ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። ለኣዲስ ኣበባ ቅርብ በሆነችው ቡራዩ የከባድ መሳሪያ ቶክስ ማምሻውን የጀመረ ሲሆን በሙገር የዳንጎቴ ንብረት የሆነ ከባድ መኪና በሕዝባዊ ንቅናቄው ኣራማጆች ሲጋይ በቡሌ ሆራ ፍርድ ቤቶች ጋይተዋል፤ ሲኤምሲ ልዩ ስሙ መሪ አካባቢ ህዝብ እና የወያኔ ወታደሮች ተናንቀዋል፡፡ ከፍተኛየተኩስ ለውውጥ እየተደረገ መሆኑንና ህዝቡ ቤንዚንና እሳት ይዞ የወያኔን ንብረት እያወደመው ነው፡፡ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች በቢሾፍቱ የተገደሉ ንጹሃንን ለመቅበር በተደረገ ስነስርዓት ላይ ከባባድ ተቃውሞዎች የተሰሙ ሲሆን በምዕራብ ሀረርጌ ፪ የሰላም ባስ አውቶብሶች ከጥቅም ውጭ ሆነዋል። ተቃውሞው የሚቀጥል ሲሆን ኣዳዲስ የትግል ስትራቴጂዎች እየተነደፉ የሕወሓት ጉጅሌ ኣገዛዝ እስኪወድቅ ድረስ ትግሉ ተቀጣጥሎ ይቀጥላል። 
Minilik Salsawi's photo.

No comments:

Post a Comment