Saturday, September 30, 2017

ለኢሬቻ በዓል እንግዶች ወደ ቢሾፍቱ እየገቡ ነውየጸጥታ አስከባሪዎች አስለቃሽ ጭስ የሚተኩሱ መሳሪያዎች ታጥቀው ይታያሉ።

ዓመታዊውን የኢሬቻ በዓል ለማክበር ቢሾፍቱ በዝግጅት ላይ ትገኛለች። ነገ ለሚከበረው የኢሬቻ በዓል አምቦ እና ጅማን ጨምሮ ከተለያዩ አካባቢዎች እንግዶች ወደ ቢሾፍቱ እየገቡ ነው። የጸጥታ አስከባሪዎች አስለቃሽ ጭስ የሚተኩሱ መሳሪያዎች ታጥቀው ይታያሉ። በከተማዋም ጥብቅ ጥበቃ በማድረግ ላይ ናቸው። በከተማ አደባባዮች በባህላዊ ልብሶች ያጌጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እና እንግዶቹ ይታያሉ። መዝናኛ ቤቶች እርጥብ ሳር (ቄጤማ) ጎዝጉዘዋል። በዓሉ የሚከበርበት የሆራ አርሰዲ ሐይቅ አቅራቢያን ጨምሮ በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ኢሬቻን የሚዘክሩ ማስታወቂያዎች ተሰቅለዋል። ወጣቶችም ጽዳት በማካሔድ ላይ ይገኛሉ። ከትናንትናው ዕለት ጀምሮ ወደ ከተማዋ የሚዘልቁ እንግዶች እና መንገደኞች ከሚጓዙበት ተሽከርካሪ ወርደው በጸጥታ ኃይሎች ይፈተሻሉ። የከተማዋ ነዋሪዎች የምሥጋናው በዓል እንደ ባለፈው ዓመት ተቃውሞ ሊደመጥበት ይችላል የሚል ሥጋት እንዳላቸው ለዶይቼ ቬለ ወኪል ተናግረዋል። (ፎቶ-ከተስፋለም ወልደየስ ማኅደር)
LikerVis flere reaksjoner
Kommenter

Thursday, September 28, 2017

አዲስ አበባ የሚገኘው የአፄ ሚኒልክ ሃውልት ሊታደስ ነው



መስከረም 18፣2010
በአዲስ አበባ የሚገኙ ሁለት የነገሥታት ሃውልቶችና ሶስት ጥንታዊ ቤቶች እድሳት ሊደረግላቸው ነው፡፡
መንግስት ለሃውልቶቹና ለጥንታዊ ቤቶች እድሳት 3ዐ ሚሊዮን ብር በጀት መመደቡንም የአስተዳሩ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል፡፡
እድሳት የሚደረግላቸው ሃውልቶች የአፄ ሚኒልክና የአፄ ቴዎድሮስ ሃውልቶች መሆናቸውንም ቢሮው አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ የመጀመሪያው ከንቲባ ቢትወደድ ወልደፃድቅ ጎሹ መኖሪያ ቤት፣ የሼክ ኦጄሌ አል ሀሰን ቤተ መንግሥትና በአሁኑ ጊዜ የአራዳ ፍርድ ቤት ሆኖ የሚያገለግለው የቀድሞ የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤትም እድሳት የሚደረግላቸው ጥንታዊ ቤቶች ናቸው፡፡
የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወርቁ መንገሻ ሃውልቶቹ የተቀመጡት አደባባይ ላይ በመሆኑ ለጎብኚዎች የማይመቹ ቢሆንም የትራፊክ እንቅስቃሴን በማይረብሽ መልኩ እንዲጎበኙ ይደረጋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

በእሬቻ በዓል ላይ የመንግስት ባለስልጣናት ንግግር አያደርጉም ተባለ



 

(ኢሳት ዜና–መስከረም 18/2010) ዕሁድ በሚከበረው የእሬቻ በዓል ላይ የመንግስት ባለስልጣናት ንግግር እንዳያደርጉ መወሰኑን የኦሮሚያ አባገዳዎች ምክር ቤት አስታወቀ።
በበዓሉ ላይ መሳሪያ የታጠቀ የመንግስት ሃይል እንደማይኖርም የኦሮሚያ አባገዳዎች ምክር ቤት ማስታወቁንም የቢቢሲ አማርኛው ክፍል ዘግቧል።
በበዓሉ ላይ የመንግስት ሰዎች ንግግር እንዳያደርጉና ታጣቂዎች በስፍራው እንዳይኖሩ የተላለፈው የአባገዳ ምክር ቤት ውሳኔ የባለፈው ዓመት ዕልቂት ተጠያቂው ማን እንደሆነ ማረጋገጫ የሚሰጥ ነው ተብሏል።
ለተገደሉት ወገኖች መታሰቢያ በመንግስት በቆመው ሀውልት ላይ ‘በድንገት የሞቱ ‘በሚል የተጻፈው ጽሁፍም እንዲፋቅ መደረጉ ታውቋል።
ምክር ቤቱ ቅዳሜ በዋዜማው ባለፈው አመት ለተገደሉት ወገኖች የህሊና ጸሎት እንደሚደረግ አስታውቋል።
መንግስት የተገደሉት ከ50 አይበልጡም ይላል። የዓይን እማኞችና የሆስፒታል ምንጮች ቁጥሩ በትንሹ ከ500 የሚልቅ እንደሆነ ይገልጻሉ።
በዕለቱ ህይወታቸውን ያጡት በድንገት ነው የሚለው የመንግስት መግለጫ ግን ለብዙዎች አስደንጋጭ ነበር። ከምንም በላይ ይህን አገላለጽ ለተገደሉት ወገኖች በቆመው ሀውልት ላይ እንዲሰፍር መደረጉ ተጠያቂነት ከመሸሽ ባሻገር ታሪክን አጣሞ ለማኖር የሚደረግ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው የሚለው ተቃውሞ ከየአቅጣጫው ሲሰማ ነው የሰነበተው።
በእሬቻ በዓል ለተገደሉት በመቶዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ተጠያቂ የሆነው መንግስት ራሱ ሀውልት ማቆሙ አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ ሲሆን የበዓሉ ጊዜ መቃረቡን ተከትሎ ጉዳዩ ትኩረትን አግኝቷል። በቅርቡ ከቦረና ኢትዮጵያ በስደት እዚህ አሜሪካን የመጡት አቶ ኡቱካና መሎ ራሱ ገድሎ ሀውልት ያቆመውን የህወሀት መንግስትን ድርጊት ከአንድ የጀርመን የጦር ጄነራል ታሪክ ጋር ያነጻጽሩታል።
ዕልቂት ከተፈጸመበት ቦታ ርቆ የቆመው ሀውልት ላይ የሰፈረው መልዕክት ሌላው አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኖ ሰንብቷል።
ያለቁት ወገኖች የተገደሉበትን ምክንያት ዓለም በቅርበት እየታዘበው በመንግስት በኩል በድንገት የተፈጸመ የሚል መግለጫ በሀውልቱ ላይ መቀመጡ ብዙዎችን አስቆጥቷል።
ሆኖም የኦሮሚያ አባገዳዎች ምክር ቤት ለቢቢሲ አማርኛ እንደገለጸው በድንገት የሚለው በመታሰቢያ ሀውልቱ ላይ የተጻፈው መግለጫ እንዲፋቅ ተደርጓል። አቶ ኡቱካና መሎ ግን መፋቅ ያለበት ቃሉ ብቻ አይደለም ይላሉ። ሀውልቱም መፍረስ አለበት።
የፊታችን ዕሁድ በሚከበረው የኢሬቻ በዓል መሳሪያ የታጠቀ ሰው በአካባቢው እንደማይኖር የኦሮሚያ ክልል መንግስት ቀደም ሲል ያስታወቀ ሲሆን የአባገዳዎች ምክር ቤትም ይህንኑ አረጋግጧል።
300 በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የአካባቢው ጸጥታ የሚያስክብሩ መመረጣቸውን የገለጸው የአባ ገዳዎች ምክር ቤት መንግስት በበዓሉ ምንም ድርሻ አይኖረውም ሲል አስታውቋል።
የመንግስት ባለስልጣናት በበዓሉ ላይ ንግግር እንደማያደርጉም ተገልጿል። የመንግስት ታጣቂዎች በቦታው እንዳይታዩና ባልስልጣናትም ንግግር እንዳያደርጉ መወሰኑ ለባለፈው ዓመት ዕልቂት ተጠያቂው ምን እንደሆነ ማረጋገጭ ይሰጣል ይላሉ አቶ ኡቱካና መሎ።

የአለም ባንክ እውነትና ኩሸት – ኤርሚያስ ለገሰ



  
By ሳተናውSeptember 27, 2017 23:53


ኤርሚያስ ለገሰ
ኤርሚያስ ለገሰ
ሰሞኑን ይፋ የተደረገው የአለም ባንክ ሪፓርት ብዙ የሚነግረን ቁምነገሮች አሉ። በአንድ በኩል የሕውሐት አገዛዝ የገባበትን ማጥ ያሳየናል ። ይህም አገዛዙ ጊዜውን ጠብቆ ተፈጥሮአዊ ሞቱን ሊሞት መቃረቡን ሐገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች የሚያሳዩበት ነው። በሌላ በኩል አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እና ምእራባውያን በሚያካሂዱት ስውር ደባ ስርአቱን ለማስቀጠል የሚያደርጉትን አገም ጠቀም እንመለከታለን ። እነዚህ የውጭ ሐይሎች እውነትና ውሸት እየመጋገቡ የሚያቀርቡት በዚህ ምክንያት ነው። የሰሞኑ የአለም ባንክ ሪፖርት ለዚህ አባባል ጥሩ ምሳሌ አድርጌ ወስጀዋለሁ። ለዚህ ብዙ ማስረጃዎች ከሪፖርቱ ውስጥ መጥቀስ ይቻላል። ለዛሬው አንድ ኩሸት እና እውነት እንውሰድ።
ኩሸት አንድ: ” ዳታ ማጣጣም!”
በሕውኃት/ ኢሕአዴግ ውስጥ ” ዳታ ማጣጣም” ልምድ የተወሰደው ከአለም ባንክ ነው። የአለም ባንክ እስከ ጐጥ የዘለቀ መዋቅር ስለሌለው የኢትዮጵያ መንግሥት የሚያቀርብለትን የእድገት አሃዝ መቀበል ይጀምራል። ይሄ ባለሁለት አሃዝ ( በአብዛኛው 11%) የተጋነነ መሆን እና እዛው ቁጥር ላይ ሙጭጭ ማለት እንዲሁም በኢትዮጵያ መሬት ላይ የተነጠፈው እውነት መረጃው ውሸት መሆኑን ይገነዘባል። በዚህ ምክንያት አለም ባንክ እስከ አስር የሚጠጉ ሠራተኞቹን ወደ መዲናችን አዲስአባ በመላክ በቁጥሮቹ ላይ ይደራደራል። አብዛኛውን ጊዜ አለም ባንክ ከ5 እስከ 8 % እድገት ይገልጣል። በነገራችን ላይ የአለም ባንክ ሰዎች ተጨማሪ ፈንድ ለማግኘትና ለግላቸው ጥቅም ሲሉ እድገት መጥቷል ማለታቸው የሚጠበቅ ነው። ህውሓት በበኩሉ የ11% እድገት ይዞ ይቀርባል። በድርድር የፀደቁት( በአብዛኛው አማካይ) ቁጥሮች የአለም ባንክ ዳታ ሆነው ይቀርባሉ። በዚህ አሃዝ አለም ባንክም ፈንዱን ያገኛል፣ ህውሓትም የፕሮፐጋንዳ ማድመቂያውን ያገኛል። አቶ በረከት “አለም የሰጠነውን ስለሚቀበል ጨማምራችሁ ከመስጠት አትቆጠቡ!” የሚለው ይሄንን ስለሚያውቅ ነው።
የአለም ባንክን ዳታ ማጣጣም ውሸት በአንድ ምሳሌ አስደግፈን እንመልከተው ። ሪፖርቱ ከኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሶስተኛው (33 ሚሊዬን) የሚጠጋው ከፍፅም ድህነት ወለል በታች በቀን ከ1•9 ዶላር በታች ገቢ ያገኛሉ ይላል። ከሁለት ዶላር በታች የሚለውን ስሌት ከሄድን “የጠቅላይ ሚኒስትሩን” (HD) ቤተሰብ ጀምሮ በድህነት ወለል ውስጥ እንከታቸዋል። ነብስ ይማርና “ከድርጅት ተቆራርጦ የሚቀረን አራት ሺህ ብር ነው!” የተባለላቸው የአቶ መለስ ቤተሰቦች ደግሞ በፍፅም ድህነት ውስጥ ኖረው የሞቱ ይሆናሉ። እንደውም ከዛሬ ጀምሮ ” ምጡቁ”፣ ” ዘመን ተሻጋሪ!”፣ ” የክፍለ ዘመን ክስተት!” እየተባለ መንፈሳቸው ከሚጨነቅ ” የደሃ ደሃ” ብንላቸው እረፍት የሚያገኙ ይመስለኛል። ሴትየዋ ጉልት ለመነገድ ያቀረበችው ሓሳብ በሕወሓት ደጃፍ ተቀባይነት ሊያገኝ ይችላል ። ጉልት ሸጦ የማክበር ሓሳብ! እስቲ እንሞክረው!
እስቲ ደግሞ አንድ መሬት የወረደ ተጨባጭ ምሳሌ እናንሳ። ሁለት የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ መምህራን የሆኑ ባልና ሚስት አሉ እንበል። እነዚህ ባለትዳሮች አራት ተማሪ የሆኑ ልጆች አሏቸው እንበል። እነዚህ ጥንዶች የወር ደሞዛቸው በድምሩ 10ሺህ ብር ይሁን። እንግዲህ በአለም ባንክና አለም አቀፍ ስታንዳርድ መሰረት ይሄ ቤተሰብ ከድህነት ወለል በታች የሚኖር ነው። እስቲ እግዜር ይታያችሁ እነዚህ የዪንቨርስቲ መምህራን ቤተሰቦች ከድህነት ጠለል በታች የሚኖሩ ከሆነ እንዴት 33 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ በፍጹም ድህነት ይኖራል? ፈፅሞ ውሸት ነው!!
በነገራችን ላይ ይሄ አለም ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ያመጣው ” ዳታ የማጣጣም ” ተሞክሮ ዛሬ በቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን፣ ክልል ፣ ሴክተር መሥሪያ ቤቶችና ማእከላዊ ስታስቲክስ ባለሥልጣን መደበኛ አሰራር ሆኗል። ቶጐ ጫሌ የሚገኘው የቀበሌ ሊቀመንበር እና አብርሃ አጽብሃ የሚገኘው የሕውሓት ካድሬዎች የሚያቀርቡት የኢኮኖሚ እድገት ቁጥር አንድ አይነት ነው። አንድ አይነት። 11 በመቶ። በጣም ያሳዝናል።
እውነት አንድ :- ” እኩል ተጠቃሚነት የለም!”
ሪፖርቱ “የኢኮኖሚ እድገቱ በክልሎች እና በሕዝቦች መካከል እኩል የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አላረጋገጠም” ይላል። እኛስ ከዚህ ውጭ ምን አልን? ምን ወጣን? የሕውኃት አገዛዝ በዘር ላይ የተሞረከዘ በመሆኑ መቼም ቢሆን በእኩልነት ተጠቃሚ ሊያደርግ የሚችል እድል መፍጠር እንደማይችል በተደጋጋሚ ገልጸናል ።
እርግጥም በማበላለጥ ፣ በጥላቻና በጠላትነት የተመሰረተው የአገዛዝ ስርአት ውጤቱ ከዚህ ውጭ ሊሆን አይችልም ። ጎጠኝነትና ጠባብነት የተከለው የመርዝ ዛፍ ፍሬውም መርዛም መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው። ይህ አንዱን ክልል ከሌሎች ለይቶ የማበልፀግና ሌላውን የማቆርቆዝ አድሎአዊ አሰራር በትውልዶች መካከል ከቶውንም ሊረሳ የማይችል የቂም በቀል ቋጠሮ የሚያኖር ነው። አንዱ አካባቢ እንደ የቁማሯ ከተማ ላስቬጋስ በምሽት ፀሐይ ተንቆጥቁጦ ሌላው በድቅድቅ ጨለማ ሲዋጥ የሚያመላክተን ነገር የአገዛዙን አድሎአዊነት እና ሸውራራ አመለካከት ነው። የዘረኝነት ፓሊሲ የወለደው ጐሰኝነት ነው።
አንዳንዶች ጐሰኝነትን ቀባብተው ብሔርተኝነት ቢሉትም በየትኛውም አቅጣጫ ቢታይ ለፓለቲካ መሳሪያ እስከተጠቀምንበት ድረስ ሁለቱም የዘረኝነት ፓሊሲ ነው። ለራስ ብሔረሰብ ሰው ድጋፍና ጥቅም የመስጠት አድሎአዊ አካሄድ ነው ። ለአጠቃላይ የአገር እድገት ሳይሆን በራስ ክልል ለሚካሄድ ልማት ቅድሚያ መስጠት ነው። አለም ባንክ አፋን ሞልቶ የአድሎው ምንጭ ጐሠኝነት የወለደው አትበል እንጂ መብራቱና መንገዱ በልዩ ትኩረት የት እየተሰራ እንደሆነ በማያሻማ መንገድ አመላክቷል። የባንኩ ከፍተኛ ኢኮኖሚስት ማይክል ጊገር የአገሪቱ እድገት ሁሉም አካባቢዎችና ዜጎች ማካተት እንደሚገባው፣ የኢኮኖሚ ርቀቱ መጥበብ እንዳለበትና መሠረተ ልማቶች ያለ አድሎ መስፋፋት እንደሚገባው በትኩረት ተናግረዋል ። የፈረንጁ ምክር ” የማይሆን ነገር ለሚስትህ አትንገር” ቢሆንም ከምክሩ ባሻገር ያለውን እዉነታ አሻግሮ ማየት የሚቻል ይመስለኛል። ማየታችንን ካልከለከሉን በስተቀር!!

የባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ተመራቂ የኢንጅነሪግ ተማሪዎችን ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አዘዘ – ሙሉቀን ተስፋው



  
By ሳተናውSeptember 28, 2017 06:08



በባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ ፖሊ ግቢ የHolistic ፈተናን ያልተፈተኑ ተማሪዎችን እንደሚያባርር በማስታወቂያ ዛሬ ማለዳ ገልጧል፡፡ ተማሪዎች እንደሚሉት ያለምንም ዝግጅት በድንገት እንድንፈተን በመወሱ ሁላችን ፈተናውን አልወሰድንም፤ ነገር ግን ዛሬ ፌደራል ፖሊስ እንዲገባ አድርገው ሁላችንም ትምህርት እንድናቋርጥ በዩንቨርሲቲው ተገልጾልናል ብለዋል፡፡ ተማሪዎች ለማስወጣት ፌደራል ፖሊስ እንዲገባ ካደረጉት የግቢው ባለሥልጣናት መካከል አቶ ተስፋዬ አባቡ ዋነኛው እንደሆነ ተማሪዎች ተናግረዋል፡፡
ዩንቨርሲቲው በውሳኔው ከጸና የፖሊ ግቢ ተመራቂ የኢንጅነሪንግ ተማሪዎች በዚህ ዓመት አይኖረውም፡፡

Wednesday, September 27, 2017

ሦስት ሺህ የሚሆኑ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ከሶማሌ ላንድ ተፈናቀሉ


Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች |


 



(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል የድንበር ግጭት የተነሳ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከሁለቱም ክልሎች መፈናቀላቸው ሲዘገብ የቆየ ሲሆን  አሁን ደግሞ  ከጎረቤት ሶማሌላንድ ሦስት ሺሕ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች መፈናቀላቸው ተሰማ፡፡
እንደ ሪፖርተር ዘገባ ከሆነ የሁለቱ ብሔሮች ተወላጆች ግጭት ድንበር ዘሎ ኢትዮጵያ ከሕግ በመለስ እንደ አገር ዕውቅና በሰጠቻት ሶማሌላንድ ውስጥ የሚኖሩ ከሦስት ሺሕ በላይ ኦሮሞዎችም መባረራቸውን፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

የተፈናቀሉት የኦሮሞ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን በአሁኑ ወቅት ቶጎ ውጫሌ በሚባለው የኢትዮጵያ ድንበር እንደሚገኙና ወደ ኦሮሚያ ክልል በመግባት ላይ መሆናቸውን ዶ/ር ነገሪ ገልጸዋል::

ኢትዮጲያ: በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ግጭት! – ስዩም ተሾመ


Filed under: ነፃ አስተያየቶች |


 


አሁን ባለው የኢትዮጲያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ግራ-መጋባት ይታየኛል። ግራ መጋባቱ በዋናነት “ሀገሪቱ ወደየት እያመራች ነው?” በሚለው ጥያቄ ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ግራ መጋባት ታዲያ በአንዱ ወይም በሌላኛው ወገን ላይ ሳይሆን በሁሉም ወገኖች ላይ የሚስተዋል ነው። የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እና ደጋፊዎች፣ በብሔርተኝነት እና በአንድነት ጎራ በተሰለፉት ተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችና ደጋፊዎች ላይ በግልፅ ይስተዋላል። በዚህ ፅሁፍ ከሦስቱም ጎራዎች አንዳንድ ምሳሌዎች በመጥቀስ ግራ መጋባቱን ለማሳየት እንሞክራለን። ከዚያ በቀጠል ደግሞ “ሀገራችን ወደየት እያመራች ነው?” የሚለውን ጥያቄ ከሌሎች ሀገራት ታሪክና ፖለቲካዊ ክስተት ጋር በማያያዝ ምላሽ ለመስጠት እንሞክራለን።
የመጀመሪያው ግራ መጋባት የህወሓት/ኢህአዴግ መስራች እና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ በኢትዮጲያ ፌደራሊዝም ስርዓትን አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት ነው። እንደ እሳቸው አገላለፅ፣ በዩጎዝላቪያ (Yugoslavia) የነበረው የፌደራሊዝም ስርዓት የወደቀው በአንድ ብሔር (the Serbs) የበላይነት ላይ የተመሰረተና ሌሎችን ብሔሮች ያገለለ በመሆኑ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ የሶቭዬት ፌዴሬሽን (Soviet federation) የተበታተነው ደግሞ በስርዓቱ ጨቋኝነት እና በዴሞክራሲ እጦት እንደሆነ ገልፀዋል።
“አዎ…የህወሓት/ትግራይ የበላይነት አለ’ በሚል ርዕስ ባወጣሁት ፅሁፍ በዝርዝር ለማብራራት እንደሞከርኩት አሁን ባለው ፖለቲካዊ ስርዓት ላይ የህወሓት/ትግራይ የበላይነት በግልፅ የሚታይ ሃቅ ነው። በሌላ በኩል፣ የኢህአዴግ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ከሕዝብ ለሚነሱ የነፃነት፥ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በኃይል ለማፈን ጥረት እያደረገ ነው። በዚህ ምክንያት፣ የኢህአዴግ መንግስት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ ጨቋኝና አምባገነን እየሆነ መጥቷል። ነገር ግን፣ የመንግስታዊ ስርዓቱ መስራችና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ “ዩጎዝላቪያና ሶቬት ሕብረት የፈረሱት አሁን የኢህአዴግ መንግስት እየፈፀመ ያለውን ስህተት በመፈፀማቸው ነው” ማለታቸው በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ግራ መጋባት ያሳያል።

ከላይ በተጠቀሰው የአቶ አባይ ፀሐዬ አስተያየት ግራ የተጋባው አንድ የኦሮሞ ብሔርተኛ ወዳጄ “ይሄ ነገር ‘ኣላዋቂነት’ ወይስ ‘ንቀት’ ነው?” በማለት ጠየቀኝ። በእርግጥ እንደ አባይ ፀሐዬ ያሉ አንጋፋ ፖለቲከኞች “አላዋቂ ናቸው” እንዳይባል ሀገሪቱ የምትመራበትን ፖለቲካዊ ስርዓት መዘርጋት የቻሉ ናቸው። አይ…ነገረ ስራቸው ሁሉ “ንቀት ነው” እንዳይባል ደግሞ በንቀት ራሳቸውን ለውድቀት አይዳርጉም። ምክንያቱም፣ የዩጎዝላቪያና ሶቬት ህብረት የወደቁበትን መሰረታዊ ምክንያት እያወሱ ተመሳሳይ ስህተት ይፈፅማሉ ብሎ ማሰብ ይከብዳል።
ሦስተኛውን ግራ መጋባት የታዘብኩት ደግሞ የአንድነት አቀንቃኝ በሆነው ወዳጄ ላይ ነው። ከዚህ ጓደኛዬ ጋር ከረጅም አመታት በኋላ ታክሲ ውስጥ ተገናኘንና እንዲህ ሲል ጠየቀኝ፡- “የኢህአዴግ መንግስት አሁን ካለንበት የፖለቲካ ቀውስ ላይ ያደረሰን አውቆና አቅዶ ነው ወይስ ሳያውቅ በስህተት ነው?” በእርግጥ አውቆና አቅዶ ሀገሪቱን አሁን ካለችበት ደረጃ ላይ ማድረስ በጣም ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካ ዕዉቀት ይጠይቃል። ነገር ግን፣ ሀገርና ሕዝብን ለፖለቲካ ቀውስና ውድቀት የሚዳርግ አሻጥር ክፋት እንጂ ዕውቀት ሊባል አይችልም። በሌላ በኩል ደግሞ “ሳያውቁ በስህተት የፈፀሙት ነው” እንዳይባል ደግሞ ስህተታቸውን የነገሯቸውን የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ የመብት ተሟጋቾች፣ …ወዘተ ለእስርና ስደት ዳርገዋቸዋል።
በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ዕልቂት!
በአጠቃላይ፣ የኢህአዴግ መሪዎች “አያውቁም” እንዳይባል ሀገርና ሕዝብ ይመራሉ፣ “ያውቃሉ” እንዳይባል ደግሞ ራሳቸውን ለውድቀት የሚዳርግ ስህተት ይሰራሉ። በዚህ ምክንያት፣ የእርስ-በእርስ ግጭትና የመበታተን አደጋ ሀገሪቱና ሕዝቡ ላይ ተጋርጧል። ይሄንን ግራ-መጋባት ለመፍታት የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ሃሳብ፣ ተግባራትና ስራዎችን እንደ ማሳያ እያነሱ መከራከር ይቻላል። ይህ ግን ከአንድ መቋጫ ላይ አንደርስም። ስለዚህ፣ ከሃሳብ ይልቅ አመለካከትን፣ ከተግባር ይልቅ መዋቅርን፣ ከሥራ ይልቅ አሰራርን፣… በአጠቃላይ ከፖለቲካዊ ስርዓቱ ይዘት (content) ይልቅ ቅርፁን (form) መመልከት ያስፈልጋል።
የኢህአዴግ መንግስት መስራቾችና ከፍተኛ አመራሮች፣ እንዲሁም ቀንደኛ ደጋፊዎች ሁሉንም ነገር የሚመለከቱት በብሔር ምንፅር ነው። ድጋፍና ተቃውሞ በብሔር ነው። ሥራቸውን የሚሰሩት በብሔር ነው። ሁሉም ሰው የሚሰራው በብሔር ይመስላቸዋል። ለምሳሌ፣ በኢትዮጲያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፕረዜዳንቶች በሙሉ የአከባቢው ብሔር ተወላጆች ናቸው። ለዚህ ምክንያቱ “የአከባቢው ተወላጅ የሆነ ሰው ለአካባቢው ማህብረሰብ ተገቢ የሆነ የማህብረሰብ አገልግሎት ይሰጣል” የሚል ነው። ስለዚህ የአንድ ዩኒቨርሲቲ ፕረዜዳንት በትምህርት የቀሰመው በዓለም-አቀፋዊ እውነታ ላይ የተመሰረተ ዕውቀትና ክህሎት ከተወለደበት ማህብረሰብ ውጪ ፋይዳ-ቢስ ነው። አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት ዕውቀትና ክህሎትን ሳይቀር የሚመለከተው ከብሔር አንፃር ነው።
የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊዎች ሃሳብና አመለካከታቸው ሙሉ በሙሉ በብሔር ላይ የተመሰረተ ነው። እ.አ.አ. ከ1945 – 1980 ዓ.ም ዩጎዝላቪያን የመሩት “Tito” (Josip Broz) ለረጅም አመታት የሀገሪቱን የመሩት በሀገራዊ አንድነትና የወደፊት አብሮነት መርህ ነበር። የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ አብዛኞቹ የህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮች ሀገሪቷን እየመሩ ያሉት በብሔርተኝነትና የታሪክ ቁርሾን በመቆስቆስ ነው። ለምሳሌ፣ “Tito” በዩጎዝላቪያ ”Serbs” እና “Croats” ሕዝቦች መካከል በቀድሞ ዘመን በተካሄደው የእርስ-በእርስ ጦርነት አማካኝነት የተፈጠረውን ቂምና ጥላቻ በማስወገድ የእርቅ መንፈስ ለማስፈን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
በተቃራኒው፣ የኢህአዴግ መንግስት ላለፈው ሩብ ክ/ዘመን በተለይ በአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች መካከል ያለውን የታሪክ ልዩነትና ቁርሾ በመቆስቆስ ቂምና ጥላቻ ለማስፋፋት ጥረት አድርጓል። ቀደም ሲል ለመግለፅ እንደተሞከረው፣ የምሁራን ዕውቀትና አገልግሎት በብሔርና ቋንቋ የሚከፋፍል የፖለቲካ ቡድን ለስርዓቱ ስጋት የሆነ የብሔሮች ጥምረት ሲፈጠር የእርስ-በእርስ ግጭት እንደሚፈጥር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንዲህ ያለ መንግስት አምሳያው ያለው ምስራቅ አውሮፓ ሳይሆን ደቡብ አፍሪካ ነው።
የሰቆቃ ልጆች እና የብሔር አፓርታይድ በሚሉ ተከታታይ ፅሁፎች በዝርዝር ለመግለፅ እንደሞከርኩት አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት እ.አ.አ. ከ1948 – 1994 ዓ.ም ድረስ በደቡብ አፍሪካ ከነበረው የአፓርታይድ ስርዓት ጋር ከአመሰራረቱ እስከ ውድቀቱ ድረስ ፍፁም ተመሳሳይ ነው። ብዙዎች በደቡብ አፍሪካ የነበረው የአፓርታይድ ስርዓት በዘር ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ያስባሉ። ነገር ግን፣ ለአፓርታይድ ስርዓት መመስረት ዋና ምክንያቱ ዘረኝነት አይደለም። የአፓርታይድ መነሻ ምክንያቱ እ.አ.አ. ከ1899 – 1902 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ነጭ ሰፋሪዎች እና በእንግሊዞች መካከል የተካሄደው ¨The Second Boers War” ነው። ይህ ጦርነት በነጮች መካከል የተካሄደ ጦርነት እንጂ በጥቁሮችና ነጮች መካከል የተካሄደ አልነበረም።
የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካን ሕዝብ በዘር ሀረግና በቆዳ ቀለም ነጮች፥ ጥቁሮች፥ ሕንዶችና ቅይጦች (colored) በማለት ለአራት ይከፍላቸዋል። ሆኖም ግን፣ የፀረ-አፓርታይድ ትግሉ ሲካሄድ የነበረው በዋናነት በጥቁሮችና በነጮች መካከል ነው። የአፓርታይድ ስርዓት መሰረታዊ ዓላማ ከሀገሪቱ ሕዝብ ውስጥ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ነጮችን የፖለቲካ የበላይነት ማረጋገጥ ነው። ለዚህ ደግሞ በሀገሪቱ 70% የሚሆኑትን ጥቁሮች በጎሳና ብሔር መከፋፈል አለበት።

በዚህ መሰረት፣ የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ሕዝብን በጎሳና ብሔር ለአስር ክልሎች ከፋፍሏቸዋል። እያንዳንዱ ክልል ራሱን በራሱ የማስተዳደር ስልጣን አለው። ነገር ግን፣ የአንዱ ክልል ነዋሪ በሌላኛው ክልል ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ በሕግ የተከለከለ ነበር። ይህ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ የጋራ አጀንዳና የተቀናጀ እንቅስቃሴ እንዳይኖራቸው የታለመ ነው።
የአፓርታይድ ስርዓት የአነስተኛ ብሔርን የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን ሕዝቦች በጎሳና ብሔር በመከፋፈል ላይ የተመሰረተ ስርዓት ነው። አሁን በኢትዮጲያ ያለው ፖለቲካዊ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ ከነበረው ጋር ፍፁም ተመሳሳይ ነው። የህወሓት/ትግራይ የበላይነትን ለማስቀጠል በሀገሪቱ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን በተለይ የአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች በመለያየት ላይ የተመሰረተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ፣ እ.አ.አ. ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ወደጎን በመተው የመብትና ነፃነት ጥያቄያቸውን በጋራ መጠየቅ ሲጀምሩ የአፓርታይድ መንግስት የወሰደው እርምጃ አሁን በሀገራችን ለሚስተዋለው የፖለቲካ ቀውስና አለመረጋጋት መንስዔን፣ እንዲሁም በሁለቱ ስርዓቶች መካከል ያለውን ተመሳሳይነት በግልፅ ይጠቁማል።
እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ አመፅና ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። ልክ ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች እንደታየው እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ አመፅና ተቃውሞ ተቀስቅሶ ነበር። በሁለቱም አጋጣሚዎች የመንግስት እርምጃ አንድና ተመሳሳይ ነበር። የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማዳፈን ያለማቋረጥ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ምክንያት፣ የሕዝቡ ተቃውሞ ወደ ሁከትና ብጥብጥ እያመራ ሄደ።
ይህን ተከትሎ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ መሪ የነበሩት “Pieter Willem Botha” ልክ እንደ ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥልቅ ተሃድሶ በማድረግ ለሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ቃል ገቡ። የጠ/ሚ ኃይለማሪያም ንግግር ለሁላችንም የቅርብ ግዜ ትዝታ ስለሆነ እዚህ መድገም አያስፈልግም። የአፓርታይዱ መሪ ንግግርና የተሃድሶ እንቅስቃሴ ግን “Stephen Ellis” የተባለው የዘርፉ ምሁር ባቀረበው በጥናታዊ ፅሁፍ እንዲህ ገልፆታል፡-
“…in a series of speeches, Botha seemed to try to direct the country into reformist paths and away from the racial “Apartheid”…. What is certain is that his idea of ‘healthy power sharing’ meant he would cling to ‘group rights’ as a means of maintaining White control, which he claimed was still in the best interests of South Africa….A changing and increasingly volatile South African society led to the civil insurrection of 1984 and its repercussions around the country. Botha’s response was the repression of activists and liberation movements under a state of emergency. The reform policy stagnated.…” The Historical Significance of South Africa’s Third Force, Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299.
ይሁን እንጂ የሁለቱም ሀገራት መንግስታት ስር ነቀል ተሃድሶ ማምጣት ተሳናቸው። ከዚያ ይልቅ፣ የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማፈን ጥረት ማድረግ ቀጠሉ። ሆኖም ግን፣ የሁለቱም መንግስታት እርምጃ የሕዝቡን ቁጣና ተቃውሞን ይበልጥ እንዲባባስ አደረገው። በዚህ ምክንያት፣ እ.አ.አ. በ1986 በደቡብ አፍሪካ፣ ባለፈው የ2009 ዓ.ም ደግሞ በኢትዮጲያ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ታወጀ።
በሌላ በኩል የአፓርታይድ ስርዓት የመከላከያና ድህንነት ኃላፊዎች በሕቡዕ ሦስተኛው ኃይል (The third Force) የተባለ ፀረ-አብዮታዊ ቡድን አቋቋሙ። ይህ ከክልል ሚሊሺያዎችና ልዩ ፖሊስ ኃይል የተወጣጣው ቡድን እንደ ዝምባብዌና ሞዛምቢክ ባሉ ጎረቤት ሀገራት የነበረውን የአማፂያን እንቅስቃሴ እንዲያውኩ የተቋቋሙ ነበሩ። የአሰቸኳይ ግዜው ከታወጀ በኋላ ግን በደቡብ አፍሪካ ጦር ወታደራዊ ስልጠና እና ትጥቅ ተሰጥቷቸው የፀረ-አፓርታይድ ትግሉን በማጨናገፍ ተግባር እንዲሰማሩ ተደረገ። የአፓርታይድ ስርዓት በተለይ በደቡብ አፍሪካ “KwaZulu Natal” በሚባለው ክልል የታየውና ዛሬ በሶማሊ ክልል እየታየ ያለው ፍፁም ተመሳሳይ ነው።
“In April 1986, the State Security Council had endorsed guidelines for a strategy for counter-revolutionary war which, among other things, emphasised that the forces of revolution should not be combatted by the security forces alone, but also by ‘anti-revolutionary groups such as Inkatha … as well as the ethnic factor in South African society’. In the following months, specifically ethnic organisations were armed and trained in KwaZulu and Ciskei, while anti-ANC groups in other places were encouraged and armed in the form of kitskonstabels or special policemen and vigilantes….  In effect, military units, which had carried out the destabilisation of neighbouring countries, were now implementing similar strategies at home, on the instructions of the State President, the State Security Council and the head of the [South Africa Defense Force]”  
Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299
በአጠቃላይ፣ በተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ-በእርስ ግጭት ለመፍጠር የተደረገው ጥረት ዛሬ በአንዳንድ የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊና ደቡብ ክልሎች እየታየ ካለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ፣ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ስርዓት በተለያዩ ብሔሮች መካከል የአርስ-በእርስ ግጭት በመፍጠር የነጮች የበላይነትን ለማስቀጠል ካደረገው ጥረትና ካስከተለው ውጤት በመነሳት ሀገራችን ኢትዮጲያ ወደየት እየሄደች እንደሆነ መገመት ይቻላል።
በደቡብ አፍሪካ በተለይ እ.አ.አ. ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የጥቁር ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት ለመፍጠር በሕቡዕ የተሰራው ስራ እ.አ.አ. ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ፍሬ አፈራ። በእርግጥ ከመርዛማ ዛፍ መልካም ፍሬ አይጠበቅም። በእነዚህ አራት አመታት ውስጥ ብቻ በተነሳ ሁከትና ብጥብጥ 14,000 ደቡብ አፍሪካዊያን ሕይወታቸውን አጥተዋል።  እ.አ.አ. ከ1948 ዓ.ም የአፓርታይድ ስርዓትን ለመጣል በተደረገው ትግል ከተገደሉት ሰዎች ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ብቻ የተገደሉት ይበልጣል። ሀገራችን ወደየት እያመራች እንደሆነ ለማወቅ ለሚሻ ከዚህ በላይ ጠቋሚ ማስረጃ አይገኝም። አዎ…ኢትዮጲያ ወደ እርስ-በእርስ ግጭትና ዕልቂት እያመራች ነው!

ሳውዲ ሴቶች መኪና እንዲነዱ የሚፈቅድ አዋጅ አወጣች ! ነቢዩ ሲራክ



ሳውዲ ሴቶች መኪና እንዲነዱ የሚፈቅድ አዋጅ አወጣች ! ነቢዩ ሲራክ
===================================

* አዋጁን የተሰጠው ከሳውዲው ንጉስ ሰልማን ነው
* አዋጁ ተግባራዊ የሚሆነው እአአ June 24, 2018 ነው
* ታሪካዊ የተባለው የንጉሱ ውሳኔ ከባድና ያነጋግሪ ነው
* በፍቃዱ አሰጣጥና በትግበራው ዙሪያ ጥናት ተደርጎ በ30 ቀን ውስጥ እንዲቀርብ ንጉሱ አዘዋል
* የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትርና ከፍተኛ ህግ አስፈጻሚ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን በማቀናጀት ለፈቃዱ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ ትዕዛዝ ተላልፏል
ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ
መስከረም 17 ቀን 2010 ዓም

ሳውዲ ሴቶች መኪና እንዲነዱ የሚፈቅድ አዋጅ አወጣች ! ነቢዩ ሲራክ

 
ሳውዲ ሴቶች መኪና እንዲነዱ የሚፈቅድ አዋጅ አወጣች ! ነቢዩ ሲራክ
===================================

* አዋጁን የተሰጠው ከሳውዲው ንጉስ ሰልማን ነው
* አዋጁ ተግባራዊ የሚሆነው እአአ June 24, 2018 ነው
* ታሪካዊ የተባለው የንጉሱ ውሳኔ ከባድና ያነጋግሪ ነው
* በፍቃዱ አሰጣጥና በትግበራው ዙሪያ ጥናት ተደርጎ በ30 ቀን ውስጥ እንዲቀርብ ንጉሱ አዘዋል
* የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትርና ከፍተኛ ህግ አስፈጻሚ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን በማቀናጀት ለፈቃዱ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ ትዕዛዝ ተላልፏል
ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ
መስከረም 17 ቀን 2010 ዓም

ኢትዮጲያ: በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ግጭት! – ስዩም ተሾመ



Filed under: ነፃ አስተያየቶች |

 


አሁን ባለው የኢትዮጲያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ግራ-መጋባት ይታየኛል። ግራ መጋባቱ በዋናነት “ሀገሪቱ ወደየት እያመራች ነው?” በሚለው ጥያቄ ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ግራ መጋባት ታዲያ በአንዱ ወይም በሌላኛው ወገን ላይ ሳይሆን በሁሉም ወገኖች ላይ የሚስተዋል ነው። የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እና ደጋፊዎች፣ በብሔርተኝነት እና በአንድነት ጎራ በተሰለፉት ተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችና ደጋፊዎች ላይ በግልፅ ይስተዋላል። በዚህ ፅሁፍ ከሦስቱም ጎራዎች አንዳንድ ምሳሌዎች በመጥቀስ ግራ መጋባቱን ለማሳየት እንሞክራለን። ከዚያ በቀጠል ደግሞ “ሀገራችን ወደየት እያመራች ነው?” የሚለውን ጥያቄ ከሌሎች ሀገራት ታሪክና ፖለቲካዊ ክስተት ጋር በማያያዝ ምላሽ ለመስጠት እንሞክራለን።
የመጀመሪያው ግራ መጋባት የህወሓት/ኢህአዴግ መስራች እና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ በኢትዮጲያ ፌደራሊዝም ስርዓትን አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት ነው። እንደ እሳቸው አገላለፅ፣ በዩጎዝላቪያ (Yugoslavia) የነበረው የፌደራሊዝም ስርዓት የወደቀው በአንድ ብሔር (the Serbs) የበላይነት ላይ የተመሰረተና ሌሎችን ብሔሮች ያገለለ በመሆኑ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ የሶቭዬት ፌዴሬሽን (Soviet federation) የተበታተነው ደግሞ በስርዓቱ ጨቋኝነት እና በዴሞክራሲ እጦት እንደሆነ ገልፀዋል።
“አዎ…የህወሓት/ትግራይ የበላይነት አለ’ በሚል ርዕስ ባወጣሁት ፅሁፍ በዝርዝር ለማብራራት እንደሞከርኩት አሁን ባለው ፖለቲካዊ ስርዓት ላይ የህወሓት/ትግራይ የበላይነት በግልፅ የሚታይ ሃቅ ነው። በሌላ በኩል፣ የኢህአዴግ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ከሕዝብ ለሚነሱ የነፃነት፥ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በኃይል ለማፈን ጥረት እያደረገ ነው። በዚህ ምክንያት፣ የኢህአዴግ መንግስት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ ጨቋኝና አምባገነን እየሆነ መጥቷል። ነገር ግን፣ የመንግስታዊ ስርዓቱ መስራችና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ “ዩጎዝላቪያና ሶቬት ሕብረት የፈረሱት አሁን የኢህአዴግ መንግስት እየፈፀመ ያለውን ስህተት በመፈፀማቸው ነው” ማለታቸው በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ግራ መጋባት ያሳያል።
ከላይ በተጠቀሰው የአቶ አባይ ፀሐዬ አስተያየት ግራ የተጋባው አንድ የኦሮሞ ብሔርተኛ ወዳጄ “ይሄ ነገር ‘ኣላዋቂነት’ ወይስ ‘ንቀት’ ነው?” በማለት ጠየቀኝ። በእርግጥ እንደ አባይ ፀሐዬ ያሉ አንጋፋ ፖለቲከኞች “አላዋቂ ናቸው” እንዳይባል ሀገሪቱ የምትመራበትን ፖለቲካዊ ስርዓት መዘርጋት የቻሉ ናቸው። አይ…ነገረ ስራቸው ሁሉ “ንቀት ነው” እንዳይባል ደግሞ በንቀት ራሳቸውን ለውድቀት አይዳርጉም። ምክንያቱም፣ የዩጎዝላቪያና ሶቬት ህብረት የወደቁበትን መሰረታዊ ምክንያት እያወሱ ተመሳሳይ ስህተት ይፈፅማሉ ብሎ ማሰብ ይከብዳል።
ሦስተኛውን ግራ መጋባት የታዘብኩት ደግሞ የአንድነት አቀንቃኝ በሆነው ወዳጄ ላይ ነው። ከዚህ ጓደኛዬ ጋር ከረጅም አመታት በኋላ ታክሲ ውስጥ ተገናኘንና እንዲህ ሲል ጠየቀኝ፡- “የኢህአዴግ መንግስት አሁን ካለንበት የፖለቲካ ቀውስ ላይ ያደረሰን አውቆና አቅዶ ነው ወይስ ሳያውቅ በስህተት ነው?” በእርግጥ አውቆና አቅዶ ሀገሪቱን አሁን ካለችበት ደረጃ ላይ ማድረስ በጣም ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካ ዕዉቀት ይጠይቃል። ነገር ግን፣ ሀገርና ሕዝብን ለፖለቲካ ቀውስና ውድቀት የሚዳርግ አሻጥር ክፋት እንጂ ዕውቀት ሊባል አይችልም። በሌላ በኩል ደግሞ “ሳያውቁ በስህተት የፈፀሙት ነው” እንዳይባል ደግሞ ስህተታቸውን የነገሯቸውን የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ የመብት ተሟጋቾች፣ …ወዘተ ለእስርና ስደት ዳርገዋቸዋል።
በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ዕልቂት!
በአጠቃላይ፣ የኢህአዴግ መሪዎች “አያውቁም” እንዳይባል ሀገርና ሕዝብ ይመራሉ፣ “ያውቃሉ” እንዳይባል ደግሞ ራሳቸውን ለውድቀት የሚዳርግ ስህተት ይሰራሉ። በዚህ ምክንያት፣ የእርስ-በእርስ ግጭትና የመበታተን አደጋ ሀገሪቱና ሕዝቡ ላይ ተጋርጧል። ይሄንን ግራ-መጋባት ለመፍታት የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ሃሳብ፣ ተግባራትና ስራዎችን እንደ ማሳያ እያነሱ መከራከር ይቻላል። ይህ ግን ከአንድ መቋጫ ላይ አንደርስም። ስለዚህ፣ ከሃሳብ ይልቅ አመለካከትን፣ ከተግባር ይልቅ መዋቅርን፣ ከሥራ ይልቅ አሰራርን፣… በአጠቃላይ ከፖለቲካዊ ስርዓቱ ይዘት (content) ይልቅ ቅርፁን (form) መመልከት ያስፈልጋል።
የኢህአዴግ መንግስት መስራቾችና ከፍተኛ አመራሮች፣ እንዲሁም ቀንደኛ ደጋፊዎች ሁሉንም ነገር የሚመለከቱት በብሔር ምንፅር ነው። ድጋፍና ተቃውሞ በብሔር ነው። ሥራቸውን የሚሰሩት በብሔር ነው። ሁሉም ሰው የሚሰራው በብሔር ይመስላቸዋል። ለምሳሌ፣ በኢትዮጲያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፕረዜዳንቶች በሙሉ የአከባቢው ብሔር ተወላጆች ናቸው። ለዚህ ምክንያቱ “የአከባቢው ተወላጅ የሆነ ሰው ለአካባቢው ማህብረሰብ ተገቢ የሆነ የማህብረሰብ አገልግሎት ይሰጣል” የሚል ነው። ስለዚህ የአንድ ዩኒቨርሲቲ ፕረዜዳንት በትምህርት የቀሰመው በዓለም-አቀፋዊ እውነታ ላይ የተመሰረተ ዕውቀትና ክህሎት ከተወለደበት ማህብረሰብ ውጪ ፋይዳ-ቢስ ነው። አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት ዕውቀትና ክህሎትን ሳይቀር የሚመለከተው ከብሔር አንፃር ነው።
የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊዎች ሃሳብና አመለካከታቸው ሙሉ በሙሉ በብሔር ላይ የተመሰረተ ነው። እ.አ.አ. ከ1945 – 1980 ዓ.ም ዩጎዝላቪያን የመሩት “Tito” (Josip Broz) ለረጅም አመታት የሀገሪቱን የመሩት በሀገራዊ አንድነትና የወደፊት አብሮነት መርህ ነበር። የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ አብዛኞቹ የህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮች ሀገሪቷን እየመሩ ያሉት በብሔርተኝነትና የታሪክ ቁርሾን በመቆስቆስ ነው። ለምሳሌ፣ “Tito” በዩጎዝላቪያ ”Serbs” እና “Croats” ሕዝቦች መካከል በቀድሞ ዘመን በተካሄደው የእርስ-በእርስ ጦርነት አማካኝነት የተፈጠረውን ቂምና ጥላቻ በማስወገድ የእርቅ መንፈስ ለማስፈን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
በተቃራኒው፣ የኢህአዴግ መንግስት ላለፈው ሩብ ክ/ዘመን በተለይ በአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች መካከል ያለውን የታሪክ ልዩነትና ቁርሾ በመቆስቆስ ቂምና ጥላቻ ለማስፋፋት ጥረት አድርጓል። ቀደም ሲል ለመግለፅ እንደተሞከረው፣ የምሁራን ዕውቀትና አገልግሎት በብሔርና ቋንቋ የሚከፋፍል የፖለቲካ ቡድን ለስርዓቱ ስጋት የሆነ የብሔሮች ጥምረት ሲፈጠር የእርስ-በእርስ ግጭት እንደሚፈጥር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንዲህ ያለ መንግስት አምሳያው ያለው ምስራቅ አውሮፓ ሳይሆን ደቡብ አፍሪካ ነው።
የሰቆቃ ልጆች እና የብሔር አፓርታይድ በሚሉ ተከታታይ ፅሁፎች በዝርዝር ለመግለፅ እንደሞከርኩት አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት እ.አ.አ. ከ1948 – 1994 ዓ.ም ድረስ በደቡብ አፍሪካ ከነበረው የአፓርታይድ ስርዓት ጋር ከአመሰራረቱ እስከ ውድቀቱ ድረስ ፍፁም ተመሳሳይ ነው። ብዙዎች በደቡብ አፍሪካ የነበረው የአፓርታይድ ስርዓት በዘር ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ያስባሉ። ነገር ግን፣ ለአፓርታይድ ስርዓት መመስረት ዋና ምክንያቱ ዘረኝነት አይደለም። የአፓርታይድ መነሻ ምክንያቱ እ.አ.አ. ከ1899 – 1902 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ነጭ ሰፋሪዎች እና በእንግሊዞች መካከል የተካሄደው ¨The Second Boers War” ነው። ይህ ጦርነት በነጮች መካከል የተካሄደ ጦርነት እንጂ በጥቁሮችና ነጮች መካከል የተካሄደ አልነበረም።
የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካን ሕዝብ በዘር ሀረግና በቆዳ ቀለም ነጮች፥ ጥቁሮች፥ ሕንዶችና ቅይጦች (colored) በማለት ለአራት ይከፍላቸዋል። ሆኖም ግን፣ የፀረ-አፓርታይድ ትግሉ ሲካሄድ የነበረው በዋናነት በጥቁሮችና በነጮች መካከል ነው። የአፓርታይድ ስርዓት መሰረታዊ ዓላማ ከሀገሪቱ ሕዝብ ውስጥ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ነጮችን የፖለቲካ የበላይነት ማረጋገጥ ነው። ለዚህ ደግሞ በሀገሪቱ 70% የሚሆኑትን ጥቁሮች በጎሳና ብሔር መከፋፈል አለበት።
በዚህ መሰረት፣ የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ሕዝብን በጎሳና ብሔር ለአስር ክልሎች ከፋፍሏቸዋል። እያንዳንዱ ክልል ራሱን በራሱ የማስተዳደር ስልጣን አለው። ነገር ግን፣ የአንዱ ክልል ነዋሪ በሌላኛው ክልል ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ በሕግ የተከለከለ ነበር። ይህ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ የጋራ አጀንዳና የተቀናጀ እንቅስቃሴ እንዳይኖራቸው የታለመ ነው።
የአፓርታይድ ስርዓት የአነስተኛ ብሔርን የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን ሕዝቦች በጎሳና ብሔር በመከፋፈል ላይ የተመሰረተ ስርዓት ነው። አሁን በኢትዮጲያ ያለው ፖለቲካዊ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ ከነበረው ጋር ፍፁም ተመሳሳይ ነው። የህወሓት/ትግራይ የበላይነትን ለማስቀጠል በሀገሪቱ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን በተለይ የአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች በመለያየት ላይ የተመሰረተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ፣ እ.አ.አ. ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ወደጎን በመተው የመብትና ነፃነት ጥያቄያቸውን በጋራ መጠየቅ ሲጀምሩ የአፓርታይድ መንግስት የወሰደው እርምጃ አሁን በሀገራችን ለሚስተዋለው የፖለቲካ ቀውስና አለመረጋጋት መንስዔን፣ እንዲሁም በሁለቱ ስርዓቶች መካከል ያለውን ተመሳሳይነት በግልፅ ይጠቁማል።
እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ አመፅና ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። ልክ ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች እንደታየው እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ አመፅና ተቃውሞ ተቀስቅሶ ነበር። በሁለቱም አጋጣሚዎች የመንግስት እርምጃ አንድና ተመሳሳይ ነበር። የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማዳፈን ያለማቋረጥ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ምክንያት፣ የሕዝቡ ተቃውሞ ወደ ሁከትና ብጥብጥ እያመራ ሄደ።
ይህን ተከትሎ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ መሪ የነበሩት “Pieter Willem Botha” ልክ እንደ ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥልቅ ተሃድሶ በማድረግ ለሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ቃል ገቡ። የጠ/ሚ ኃይለማሪያም ንግግር ለሁላችንም የቅርብ ግዜ ትዝታ ስለሆነ እዚህ መድገም አያስፈልግም። የአፓርታይዱ መሪ ንግግርና የተሃድሶ እንቅስቃሴ ግን “Stephen Ellis” የተባለው የዘርፉ ምሁር ባቀረበው በጥናታዊ ፅሁፍ እንዲህ ገልፆታል፡-
“…in a series of speeches, Botha seemed to try to direct the country into reformist paths and away from the racial “Apartheid”…. What is certain is that his idea of ‘healthy power sharing’ meant he would cling to ‘group rights’ as a means of maintaining White control, which he claimed was still in the best interests of South Africa….A changing and increasingly volatile South African society led to the civil insurrection of 1984 and its repercussions around the country. Botha’s response was the repression of activists and liberation movements under a state of emergency. The reform policy stagnated.…” The Historical Significance of South Africa’s Third Force, Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299.
ይሁን እንጂ የሁለቱም ሀገራት መንግስታት ስር ነቀል ተሃድሶ ማምጣት ተሳናቸው። ከዚያ ይልቅ፣ የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማፈን ጥረት ማድረግ ቀጠሉ። ሆኖም ግን፣ የሁለቱም መንግስታት እርምጃ የሕዝቡን ቁጣና ተቃውሞን ይበልጥ እንዲባባስ አደረገው። በዚህ ምክንያት፣ እ.አ.አ. በ1986 በደቡብ አፍሪካ፣ ባለፈው የ2009 ዓ.ም ደግሞ በኢትዮጲያ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ታወጀ።
በሌላ በኩል የአፓርታይድ ስርዓት የመከላከያና ድህንነት ኃላፊዎች በሕቡዕ ሦስተኛው ኃይል (The third Force) የተባለ ፀረ-አብዮታዊ ቡድን አቋቋሙ። ይህ ከክልል ሚሊሺያዎችና ልዩ ፖሊስ ኃይል የተወጣጣው ቡድን እንደ ዝምባብዌና ሞዛምቢክ ባሉ ጎረቤት ሀገራት የነበረውን የአማፂያን እንቅስቃሴ እንዲያውኩ የተቋቋሙ ነበሩ። የአሰቸኳይ ግዜው ከታወጀ በኋላ ግን በደቡብ አፍሪካ ጦር ወታደራዊ ስልጠና እና ትጥቅ ተሰጥቷቸው የፀረ-አፓርታይድ ትግሉን በማጨናገፍ ተግባር እንዲሰማሩ ተደረገ። የአፓርታይድ ስርዓት በተለይ በደቡብ አፍሪካ “KwaZulu Natal” በሚባለው ክልል የታየውና ዛሬ በሶማሊ ክልል እየታየ ያለው ፍፁም ተመሳሳይ ነው።
“In April 1986, the State Security Council had endorsed guidelines for a strategy for counter-revolutionary war which, among other things, emphasised that the forces of revolution should not be combatted by the security forces alone, but also by ‘anti-revolutionary groups such as Inkatha … as well as the ethnic factor in South African society’. In the following months, specifically ethnic organisations were armed and trained in KwaZulu and Ciskei, while anti-ANC groups in other places were encouraged and armed in the form of kitskonstabels or special policemen and vigilantes….  In effect, military units, which had carried out the destabilisation of neighbouring countries, were now implementing similar strategies at home, on the instructions of the State President, the State Security Council and the head of the [South Africa Defense Force]”  
Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299
በአጠቃላይ፣ በተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ-በእርስ ግጭት ለመፍጠር የተደረገው ጥረት ዛሬ በአንዳንድ የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊና ደቡብ ክልሎች እየታየ ካለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ፣ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ስርዓት በተለያዩ ብሔሮች መካከል የአርስ-በእርስ ግጭት በመፍጠር የነጮች የበላይነትን ለማስቀጠል ካደረገው ጥረትና ካስከተለው ውጤት በመነሳት ሀገራችን ኢትዮጲያ ወደየት እየሄደች እንደሆነ መገመት ይቻላል።
በደቡብ አፍሪካ በተለይ እ.አ.አ. ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የጥቁር ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት ለመፍጠር በሕቡዕ የተሰራው ስራ እ.አ.አ. ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ፍሬ አፈራ። በእርግጥ ከመርዛማ ዛፍ መልካም ፍሬ አይጠበቅም። በእነዚህ አራት አመታት ውስጥ ብቻ በተነሳ ሁከትና ብጥብጥ 14,000 ደቡብ አፍሪካዊያን ሕይወታቸውን አጥተዋል።  እ.አ.አ. ከ1948 ዓ.ም የአፓርታይድ ስርዓትን ለመጣል በተደረገው ትግል ከተገደሉት ሰዎች ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ብቻ የተገደሉት ይበልጣል። ሀገራችን ወደየት እያመራች እንደሆነ ለማወቅ ለሚሻ ከዚህ በላይ ጠቋሚ ማስረጃ አይገኝም። አዎ…ኢትዮጲያ ወደ እርስ-በእርስ ግጭትና ዕልቂት እያመራች ነው

ኢትዮጲያ: በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ግጭት! – ስዩም ተሾመ

Filed under: ነፃ አስተያየቶች |    


አሁን ባለው የኢትዮጲያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ግራ-መጋባት ይታየኛል። ግራ መጋባቱ በዋናነት “ሀገሪቱ ወደየት እያመራች ነው?” በሚለው ጥያቄ ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ግራ መጋባት ታዲያ በአንዱ ወይም በሌላኛው ወገን ላይ ሳይሆን በሁሉም ወገኖች ላይ የሚስተዋል ነው። የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እና ደጋፊዎች፣ በብሔርተኝነት እና በአንድነት ጎራ በተሰለፉት ተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችና ደጋፊዎች ላይ በግልፅ ይስተዋላል። በዚህ ፅሁፍ ከሦስቱም ጎራዎች አንዳንድ ምሳሌዎች በመጥቀስ ግራ መጋባቱን ለማሳየት እንሞክራለን። ከዚያ በቀጠል ደግሞ “ሀገራችን ወደየት እያመራች ነው?” የሚለውን ጥያቄ ከሌሎች ሀገራት ታሪክና ፖለቲካዊ ክስተት ጋር በማያያዝ ምላሽ ለመስጠት እንሞክራለን።
የመጀመሪያው ግራ መጋባት የህወሓት/ኢህአዴግ መስራች እና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ በኢትዮጲያ ፌደራሊዝም ስርዓትን አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት ነው። እንደ እሳቸው አገላለፅ፣ በዩጎዝላቪያ (Yugoslavia) የነበረው የፌደራሊዝም ስርዓት የወደቀው በአንድ ብሔር (the Serbs) የበላይነት ላይ የተመሰረተና ሌሎችን ብሔሮች ያገለለ በመሆኑ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ የሶቭዬት ፌዴሬሽን (Soviet federation) የተበታተነው ደግሞ በስርዓቱ ጨቋኝነት እና በዴሞክራሲ እጦት እንደሆነ ገልፀዋል።
“አዎ…የህወሓት/ትግራይ የበላይነት አለ’ በሚል ርዕስ ባወጣሁት ፅሁፍ በዝርዝር ለማብራራት እንደሞከርኩት አሁን ባለው ፖለቲካዊ ስርዓት ላይ የህወሓት/ትግራይ የበላይነት በግልፅ የሚታይ ሃቅ ነው። በሌላ በኩል፣ የኢህአዴግ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ከሕዝብ ለሚነሱ የነፃነት፥ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በኃይል ለማፈን ጥረት እያደረገ ነው። በዚህ ምክንያት፣ የኢህአዴግ መንግስት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ ጨቋኝና አምባገነን እየሆነ መጥቷል። ነገር ግን፣ የመንግስታዊ ስርዓቱ መስራችና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ “ዩጎዝላቪያና ሶቬት ሕብረት የፈረሱት አሁን የኢህአዴግ መንግስት እየፈፀመ ያለውን ስህተት በመፈፀማቸው ነው” ማለታቸው በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ግራ መጋባት ያሳያል።
ከላይ በተጠቀሰው የአቶ አባይ ፀሐዬ አስተያየት ግራ የተጋባው አንድ የኦሮሞ ብሔርተኛ ወዳጄ “ይሄ ነገር ‘ኣላዋቂነት’ ወይስ ‘ንቀት’ ነው?” በማለት ጠየቀኝ። በእርግጥ እንደ አባይ ፀሐዬ ያሉ አንጋፋ ፖለቲከኞች “አላዋቂ ናቸው” እንዳይባል ሀገሪቱ የምትመራበትን ፖለቲካዊ ስርዓት መዘርጋት የቻሉ ናቸው። አይ…ነገረ ስራቸው ሁሉ “ንቀት ነው” እንዳይባል ደግሞ በንቀት ራሳቸውን ለውድቀት አይዳርጉም። ምክንያቱም፣ የዩጎዝላቪያና ሶቬት ህብረት የወደቁበትን መሰረታዊ ምክንያት እያወሱ ተመሳሳይ ስህተት ይፈፅማሉ ብሎ ማሰብ ይከብዳል።
ሦስተኛውን ግራ መጋባት የታዘብኩት ደግሞ የአንድነት አቀንቃኝ በሆነው ወዳጄ ላይ ነው። ከዚህ ጓደኛዬ ጋር ከረጅም አመታት በኋላ ታክሲ ውስጥ ተገናኘንና እንዲህ ሲል ጠየቀኝ፡- “የኢህአዴግ መንግስት አሁን ካለንበት የፖለቲካ ቀውስ ላይ ያደረሰን አውቆና አቅዶ ነው ወይስ ሳያውቅ በስህተት ነው?” በእርግጥ አውቆና አቅዶ ሀገሪቱን አሁን ካለችበት ደረጃ ላይ ማድረስ በጣም ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካ ዕዉቀት ይጠይቃል። ነገር ግን፣ ሀገርና ሕዝብን ለፖለቲካ ቀውስና ውድቀት የሚዳርግ አሻጥር ክፋት እንጂ ዕውቀት ሊባል አይችልም። በሌላ በኩል ደግሞ “ሳያውቁ በስህተት የፈፀሙት ነው” እንዳይባል ደግሞ ስህተታቸውን የነገሯቸውን የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ የመብት ተሟጋቾች፣ …ወዘተ ለእስርና ስደት ዳርገዋቸዋል።
በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ዕልቂት!
በአጠቃላይ፣ የኢህአዴግ መሪዎች “አያውቁም” እንዳይባል ሀገርና ሕዝብ ይመራሉ፣ “ያውቃሉ” እንዳይባል ደግሞ ራሳቸውን ለውድቀት የሚዳርግ ስህተት ይሰራሉ። በዚህ ምክንያት፣ የእርስ-በእርስ ግጭትና የመበታተን አደጋ ሀገሪቱና ሕዝቡ ላይ ተጋርጧል። ይሄንን ግራ-መጋባት ለመፍታት የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ሃሳብ፣ ተግባራትና ስራዎችን እንደ ማሳያ እያነሱ መከራከር ይቻላል። ይህ ግን ከአንድ መቋጫ ላይ አንደርስም። ስለዚህ፣ ከሃሳብ ይልቅ አመለካከትን፣ ከተግባር ይልቅ መዋቅርን፣ ከሥራ ይልቅ አሰራርን፣… በአጠቃላይ ከፖለቲካዊ ስርዓቱ ይዘት (content) ይልቅ ቅርፁን (form) መመልከት ያስፈልጋል።
የኢህአዴግ መንግስት መስራቾችና ከፍተኛ አመራሮች፣ እንዲሁም ቀንደኛ ደጋፊዎች ሁሉንም ነገር የሚመለከቱት በብሔር ምንፅር ነው። ድጋፍና ተቃውሞ በብሔር ነው። ሥራቸውን የሚሰሩት በብሔር ነው። ሁሉም ሰው የሚሰራው በብሔር ይመስላቸዋል። ለምሳሌ፣ በኢትዮጲያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፕረዜዳንቶች በሙሉ የአከባቢው ብሔር ተወላጆች ናቸው። ለዚህ ምክንያቱ “የአከባቢው ተወላጅ የሆነ ሰው ለአካባቢው ማህብረሰብ ተገቢ የሆነ የማህብረሰብ አገልግሎት ይሰጣል” የሚል ነው። ስለዚህ የአንድ ዩኒቨርሲቲ ፕረዜዳንት በትምህርት የቀሰመው በዓለም-አቀፋዊ እውነታ ላይ የተመሰረተ ዕውቀትና ክህሎት ከተወለደበት ማህብረሰብ ውጪ ፋይዳ-ቢስ ነው። አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት ዕውቀትና ክህሎትን ሳይቀር የሚመለከተው ከብሔር አንፃር ነው።
የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊዎች ሃሳብና አመለካከታቸው ሙሉ በሙሉ በብሔር ላይ የተመሰረተ ነው። እ.አ.አ. ከ1945 – 1980 ዓ.ም ዩጎዝላቪያን የመሩት “Tito” (Josip Broz) ለረጅም አመታት የሀገሪቱን የመሩት በሀገራዊ አንድነትና የወደፊት አብሮነት መርህ ነበር። የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ አብዛኞቹ የህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮች ሀገሪቷን እየመሩ ያሉት በብሔርተኝነትና የታሪክ ቁርሾን በመቆስቆስ ነው። ለምሳሌ፣ “Tito” በዩጎዝላቪያ ”Serbs” እና “Croats” ሕዝቦች መካከል በቀድሞ ዘመን በተካሄደው የእርስ-በእርስ ጦርነት አማካኝነት የተፈጠረውን ቂምና ጥላቻ በማስወገድ የእርቅ መንፈስ ለማስፈን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
በተቃራኒው፣ የኢህአዴግ መንግስት ላለፈው ሩብ ክ/ዘመን በተለይ በአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች መካከል ያለውን የታሪክ ልዩነትና ቁርሾ በመቆስቆስ ቂምና ጥላቻ ለማስፋፋት ጥረት አድርጓል። ቀደም ሲል ለመግለፅ እንደተሞከረው፣ የምሁራን ዕውቀትና አገልግሎት በብሔርና ቋንቋ የሚከፋፍል የፖለቲካ ቡድን ለስርዓቱ ስጋት የሆነ የብሔሮች ጥምረት ሲፈጠር የእርስ-በእርስ ግጭት እንደሚፈጥር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንዲህ ያለ መንግስት አምሳያው ያለው ምስራቅ አውሮፓ ሳይሆን ደቡብ አፍሪካ ነው።
የሰቆቃ ልጆች እና የብሔር አፓርታይድ በሚሉ ተከታታይ ፅሁፎች በዝርዝር ለመግለፅ እንደሞከርኩት አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት እ.አ.አ. ከ1948 – 1994 ዓ.ም ድረስ በደቡብ አፍሪካ ከነበረው የአፓርታይድ ስርዓት ጋር ከአመሰራረቱ እስከ ውድቀቱ ድረስ ፍፁም ተመሳሳይ ነው። ብዙዎች በደቡብ አፍሪካ የነበረው የአፓርታይድ ስርዓት በዘር ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ያስባሉ። ነገር ግን፣ ለአፓርታይድ ስርዓት መመስረት ዋና ምክንያቱ ዘረኝነት አይደለም። የአፓርታይድ መነሻ ምክንያቱ እ.አ.አ. ከ1899 – 1902 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ነጭ ሰፋሪዎች እና በእንግሊዞች መካከል የተካሄደው ¨The Second Boers War” ነው። ይህ ጦርነት በነጮች መካከል የተካሄደ ጦርነት እንጂ በጥቁሮችና ነጮች መካከል የተካሄደ አልነበረም።
የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካን ሕዝብ በዘር ሀረግና በቆዳ ቀለም ነጮች፥ ጥቁሮች፥ ሕንዶችና ቅይጦች (colored) በማለት ለአራት ይከፍላቸዋል። ሆኖም ግን፣ የፀረ-አፓርታይድ ትግሉ ሲካሄድ የነበረው በዋናነት በጥቁሮችና በነጮች መካከል ነው። የአፓርታይድ ስርዓት መሰረታዊ ዓላማ ከሀገሪቱ ሕዝብ ውስጥ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ነጮችን የፖለቲካ የበላይነት ማረጋገጥ ነው። ለዚህ ደግሞ በሀገሪቱ 70% የሚሆኑትን ጥቁሮች በጎሳና ብሔር መከፋፈል አለበት።
በዚህ መሰረት፣ የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ሕዝብን በጎሳና ብሔር ለአስር ክልሎች ከፋፍሏቸዋል። እያንዳንዱ ክልል ራሱን በራሱ የማስተዳደር ስልጣን አለው። ነገር ግን፣ የአንዱ ክልል ነዋሪ በሌላኛው ክልል ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ በሕግ የተከለከለ ነበር። ይህ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ የጋራ አጀንዳና የተቀናጀ እንቅስቃሴ እንዳይኖራቸው የታለመ ነው።
የአፓርታይድ ስርዓት የአነስተኛ ብሔርን የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን ሕዝቦች በጎሳና ብሔር በመከፋፈል ላይ የተመሰረተ ስርዓት ነው። አሁን በኢትዮጲያ ያለው ፖለቲካዊ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ ከነበረው ጋር ፍፁም ተመሳሳይ ነው። የህወሓት/ትግራይ የበላይነትን ለማስቀጠል በሀገሪቱ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን በተለይ የአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች በመለያየት ላይ የተመሰረተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ፣ እ.አ.አ. ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ወደጎን በመተው የመብትና ነፃነት ጥያቄያቸውን በጋራ መጠየቅ ሲጀምሩ የአፓርታይድ መንግስት የወሰደው እርምጃ አሁን በሀገራችን ለሚስተዋለው የፖለቲካ ቀውስና አለመረጋጋት መንስዔን፣ እንዲሁም በሁለቱ ስርዓቶች መካከል ያለውን ተመሳሳይነት በግልፅ ይጠቁማል።
እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ አመፅና ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። ልክ ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች እንደታየው እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ አመፅና ተቃውሞ ተቀስቅሶ ነበር። በሁለቱም አጋጣሚዎች የመንግስት እርምጃ አንድና ተመሳሳይ ነበር። የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማዳፈን ያለማቋረጥ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ምክንያት፣ የሕዝቡ ተቃውሞ ወደ ሁከትና ብጥብጥ እያመራ ሄደ።
ይህን ተከትሎ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ መሪ የነበሩት “Pieter Willem Botha” ልክ እንደ ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥልቅ ተሃድሶ በማድረግ ለሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ቃል ገቡ። የጠ/ሚ ኃይለማሪያም ንግግር ለሁላችንም የቅርብ ግዜ ትዝታ ስለሆነ እዚህ መድገም አያስፈልግም። የአፓርታይዱ መሪ ንግግርና የተሃድሶ እንቅስቃሴ ግን “Stephen Ellis” የተባለው የዘርፉ ምሁር ባቀረበው በጥናታዊ ፅሁፍ እንዲህ ገልፆታል፡-
“…in a series of speeches, Botha seemed to try to direct the country into reformist paths and away from the racial “Apartheid”…. What is certain is that his idea of ‘healthy power sharing’ meant he would cling to ‘group rights’ as a means of maintaining White control, which he claimed was still in the best interests of South Africa….A changing and increasingly volatile South African society led to the civil insurrection of 1984 and its repercussions around the country. Botha’s response was the repression of activists and liberation movements under a state of emergency. The reform policy stagnated.…” The Historical Significance of South Africa’s Third Force, Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299.
ይሁን እንጂ የሁለቱም ሀገራት መንግስታት ስር ነቀል ተሃድሶ ማምጣት ተሳናቸው። ከዚያ ይልቅ፣ የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማፈን ጥረት ማድረግ ቀጠሉ። ሆኖም ግን፣ የሁለቱም መንግስታት እርምጃ የሕዝቡን ቁጣና ተቃውሞን ይበልጥ እንዲባባስ አደረገው። በዚህ ምክንያት፣ እ.አ.አ. በ1986 በደቡብ አፍሪካ፣ ባለፈው የ2009 ዓ.ም ደግሞ በኢትዮጲያ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ታወጀ።
በሌላ በኩል የአፓርታይድ ስርዓት የመከላከያና ድህንነት ኃላፊዎች በሕቡዕ ሦስተኛው ኃይል (The third Force) የተባለ ፀረ-አብዮታዊ ቡድን አቋቋሙ። ይህ ከክልል ሚሊሺያዎችና ልዩ ፖሊስ ኃይል የተወጣጣው ቡድን እንደ ዝምባብዌና ሞዛምቢክ ባሉ ጎረቤት ሀገራት የነበረውን የአማፂያን እንቅስቃሴ እንዲያውኩ የተቋቋሙ ነበሩ። የአሰቸኳይ ግዜው ከታወጀ በኋላ ግን በደቡብ አፍሪካ ጦር ወታደራዊ ስልጠና እና ትጥቅ ተሰጥቷቸው የፀረ-አፓርታይድ ትግሉን በማጨናገፍ ተግባር እንዲሰማሩ ተደረገ። የአፓርታይድ ስርዓት በተለይ በደቡብ አፍሪካ “KwaZulu Natal” በሚባለው ክልል የታየውና ዛሬ በሶማሊ ክልል እየታየ ያለው ፍፁም ተመሳሳይ ነው።
“In April 1986, the State Security Council had endorsed guidelines for a strategy for counter-revolutionary war which, among other things, emphasised that the forces of revolution should not be combatted by the security forces alone, but also by ‘anti-revolutionary groups such as Inkatha … as well as the ethnic factor in South African society’. In the following months, specifically ethnic organisations were armed and trained in KwaZulu and Ciskei, while anti-ANC groups in other places were encouraged and armed in the form of kitskonstabels or special policemen and vigilantes….  In effect, military units, which had carried out the destabilisation of neighbouring countries, were now implementing similar strategies at home, on the instructions of the State President, the State Security Council and the head of the [South Africa Defense Force]”  
Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299
በአጠቃላይ፣ በተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ-በእርስ ግጭት ለመፍጠር የተደረገው ጥረት ዛሬ በአንዳንድ የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊና ደቡብ ክልሎች እየታየ ካለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ፣ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ስርዓት በተለያዩ ብሔሮች መካከል የአርስ-በእርስ ግጭት በመፍጠር የነጮች የበላይነትን ለማስቀጠል ካደረገው ጥረትና ካስከተለው ውጤት በመነሳት ሀገራችን ኢትዮጲያ ወደየት እየሄደች እንደሆነ መገመት ይቻላል።
በደቡብ አፍሪካ በተለይ እ.አ.አ. ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የጥቁር ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት ለመፍጠር በሕቡዕ የተሰራው ስራ እ.አ.አ. ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ፍሬ አፈራ። በእርግጥ ከመርዛማ ዛፍ መልካም ፍሬ አይጠበቅም። በእነዚህ አራት አመታት ውስጥ ብቻ በተነሳ ሁከትና ብጥብጥ 14,000 ደቡብ አፍሪካዊያን ሕይወታቸውን አጥተዋል።  እ.አ.አ. ከ1948 ዓ.ም የአፓርታይድ ስርዓትን ለመጣል በተደረገው ትግል ከተገደሉት ሰዎች ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ብቻ የተገደሉት ይበልጣል። ሀገራችን ወደየት እያመራች እንደሆነ ለማወቅ ለሚሻ ከዚህ በላይ ጠቋሚ ማስረጃ አይገኝም። አዎ…ኢትዮጲያ ወደ እርስ-በእርስ ግጭትና ዕልቂት እያመራች ነው!


ኢትዮጲያ: በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ግጭት! – ስዩም ተሾመ



Filed under: ነፃ አስተያየቶች |

 

አሁን ባለው የኢትዮጲያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ግራ-መጋባት ይታየኛል። ግራ መጋባቱ በዋናነት “ሀገሪቱ ወደየት እያመራች ነው?” በሚለው ጥያቄ ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ግራ መጋባት ታዲያ በአንዱ ወይም በሌላኛው ወገን ላይ ሳይሆን በሁሉም ወገኖች ላይ የሚስተዋል ነው። የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እና ደጋፊዎች፣ በብሔርተኝነት እና በአንድነት ጎራ በተሰለፉት ተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችና ደጋፊዎች ላይ በግልፅ ይስተዋላል። በዚህ ፅሁፍ ከሦስቱም ጎራዎች አንዳንድ ምሳሌዎች በመጥቀስ ግራ መጋባቱን ለማሳየት እንሞክራለን። ከዚያ በቀጠል ደግሞ “ሀገራችን ወደየት እያመራች ነው?” የሚለውን ጥያቄ ከሌሎች ሀገራት ታሪክና ፖለቲካዊ ክስተት ጋር በማያያዝ ምላሽ ለመስጠት እንሞክራለን።
የመጀመሪያው ግራ መጋባት የህወሓት/ኢህአዴግ መስራች እና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ በኢትዮጲያ ፌደራሊዝም ስርዓትን አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት ነው። እንደ እሳቸው አገላለፅ፣ በዩጎዝላቪያ (Yugoslavia) የነበረው የፌደራሊዝም ስርዓት የወደቀው በአንድ ብሔር (the Serbs) የበላይነት ላይ የተመሰረተና ሌሎችን ብሔሮች ያገለለ በመሆኑ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ የሶቭዬት ፌዴሬሽን (Soviet federation) የተበታተነው ደግሞ በስርዓቱ ጨቋኝነት እና በዴሞክራሲ እጦት እንደሆነ ገልፀዋል።
“አዎ…የህወሓት/ትግራይ የበላይነት አለ’ በሚል ርዕስ ባወጣሁት ፅሁፍ በዝርዝር ለማብራራት እንደሞከርኩት አሁን ባለው ፖለቲካዊ ስርዓት ላይ የህወሓት/ትግራይ የበላይነት በግልፅ የሚታይ ሃቅ ነው። በሌላ በኩል፣ የኢህአዴግ መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ከሕዝብ ለሚነሱ የነፃነት፥ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በኃይል ለማፈን ጥረት እያደረገ ነው። በዚህ ምክንያት፣ የኢህአዴግ መንግስት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ ጨቋኝና አምባገነን እየሆነ መጥቷል። ነገር ግን፣ የመንግስታዊ ስርዓቱ መስራችና ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ “ዩጎዝላቪያና ሶቬት ሕብረት የፈረሱት አሁን የኢህአዴግ መንግስት እየፈፀመ ያለውን ስህተት በመፈፀማቸው ነው” ማለታቸው በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ግራ መጋባት ያሳያል።
ከላይ በተጠቀሰው የአቶ አባይ ፀሐዬ አስተያየት ግራ የተጋባው አንድ የኦሮሞ ብሔርተኛ ወዳጄ “ይሄ ነገር ‘ኣላዋቂነት’ ወይስ ‘ንቀት’ ነው?” በማለት ጠየቀኝ። በእርግጥ እንደ አባይ ፀሐዬ ያሉ አንጋፋ ፖለቲከኞች “አላዋቂ ናቸው” እንዳይባል ሀገሪቱ የምትመራበትን ፖለቲካዊ ስርዓት መዘርጋት የቻሉ ናቸው። አይ…ነገረ ስራቸው ሁሉ “ንቀት ነው” እንዳይባል ደግሞ በንቀት ራሳቸውን ለውድቀት አይዳርጉም። ምክንያቱም፣ የዩጎዝላቪያና ሶቬት ህብረት የወደቁበትን መሰረታዊ ምክንያት እያወሱ ተመሳሳይ ስህተት ይፈፅማሉ ብሎ ማሰብ ይከብዳል።
ሦስተኛውን ግራ መጋባት የታዘብኩት ደግሞ የአንድነት አቀንቃኝ በሆነው ወዳጄ ላይ ነው። ከዚህ ጓደኛዬ ጋር ከረጅም አመታት በኋላ ታክሲ ውስጥ ተገናኘንና እንዲህ ሲል ጠየቀኝ፡- “የኢህአዴግ መንግስት አሁን ካለንበት የፖለቲካ ቀውስ ላይ ያደረሰን አውቆና አቅዶ ነው ወይስ ሳያውቅ በስህተት ነው?” በእርግጥ አውቆና አቅዶ ሀገሪቱን አሁን ካለችበት ደረጃ ላይ ማድረስ በጣም ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካ ዕዉቀት ይጠይቃል። ነገር ግን፣ ሀገርና ሕዝብን ለፖለቲካ ቀውስና ውድቀት የሚዳርግ አሻጥር ክፋት እንጂ ዕውቀት ሊባል አይችልም። በሌላ በኩል ደግሞ “ሳያውቁ በስህተት የፈፀሙት ነው” እንዳይባል ደግሞ ስህተታቸውን የነገሯቸውን የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ የመብት ተሟጋቾች፣ …ወዘተ ለእስርና ስደት ዳርገዋቸዋል።
በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ዕልቂት!
በአጠቃላይ፣ የኢህአዴግ መሪዎች “አያውቁም” እንዳይባል ሀገርና ሕዝብ ይመራሉ፣ “ያውቃሉ” እንዳይባል ደግሞ ራሳቸውን ለውድቀት የሚዳርግ ስህተት ይሰራሉ። በዚህ ምክንያት፣ የእርስ-በእርስ ግጭትና የመበታተን አደጋ ሀገሪቱና ሕዝቡ ላይ ተጋርጧል። ይሄንን ግራ-መጋባት ለመፍታት የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ሃሳብ፣ ተግባራትና ስራዎችን እንደ ማሳያ እያነሱ መከራከር ይቻላል። ይህ ግን ከአንድ መቋጫ ላይ አንደርስም። ስለዚህ፣ ከሃሳብ ይልቅ አመለካከትን፣ ከተግባር ይልቅ መዋቅርን፣ ከሥራ ይልቅ አሰራርን፣… በአጠቃላይ ከፖለቲካዊ ስርዓቱ ይዘት (content) ይልቅ ቅርፁን (form) መመልከት ያስፈልጋል።
የኢህአዴግ መንግስት መስራቾችና ከፍተኛ አመራሮች፣ እንዲሁም ቀንደኛ ደጋፊዎች ሁሉንም ነገር የሚመለከቱት በብሔር ምንፅር ነው። ድጋፍና ተቃውሞ በብሔር ነው። ሥራቸውን የሚሰሩት በብሔር ነው። ሁሉም ሰው የሚሰራው በብሔር ይመስላቸዋል። ለምሳሌ፣ በኢትዮጲያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፕረዜዳንቶች በሙሉ የአከባቢው ብሔር ተወላጆች ናቸው። ለዚህ ምክንያቱ “የአከባቢው ተወላጅ የሆነ ሰው ለአካባቢው ማህብረሰብ ተገቢ የሆነ የማህብረሰብ አገልግሎት ይሰጣል” የሚል ነው። ስለዚህ የአንድ ዩኒቨርሲቲ ፕረዜዳንት በትምህርት የቀሰመው በዓለም-አቀፋዊ እውነታ ላይ የተመሰረተ ዕውቀትና ክህሎት ከተወለደበት ማህብረሰብ ውጪ ፋይዳ-ቢስ ነው። አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት ዕውቀትና ክህሎትን ሳይቀር የሚመለከተው ከብሔር አንፃር ነው።
የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊዎች ሃሳብና አመለካከታቸው ሙሉ በሙሉ በብሔር ላይ የተመሰረተ ነው። እ.አ.አ. ከ1945 – 1980 ዓ.ም ዩጎዝላቪያን የመሩት “Tito” (Josip Broz) ለረጅም አመታት የሀገሪቱን የመሩት በሀገራዊ አንድነትና የወደፊት አብሮነት መርህ ነበር። የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ አብዛኞቹ የህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮች ሀገሪቷን እየመሩ ያሉት በብሔርተኝነትና የታሪክ ቁርሾን በመቆስቆስ ነው። ለምሳሌ፣ “Tito” በዩጎዝላቪያ ”Serbs” እና “Croats” ሕዝቦች መካከል በቀድሞ ዘመን በተካሄደው የእርስ-በእርስ ጦርነት አማካኝነት የተፈጠረውን ቂምና ጥላቻ በማስወገድ የእርቅ መንፈስ ለማስፈን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
በተቃራኒው፣ የኢህአዴግ መንግስት ላለፈው ሩብ ክ/ዘመን በተለይ በአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች መካከል ያለውን የታሪክ ልዩነትና ቁርሾ በመቆስቆስ ቂምና ጥላቻ ለማስፋፋት ጥረት አድርጓል። ቀደም ሲል ለመግለፅ እንደተሞከረው፣ የምሁራን ዕውቀትና አገልግሎት በብሔርና ቋንቋ የሚከፋፍል የፖለቲካ ቡድን ለስርዓቱ ስጋት የሆነ የብሔሮች ጥምረት ሲፈጠር የእርስ-በእርስ ግጭት እንደሚፈጥር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንዲህ ያለ መንግስት አምሳያው ያለው ምስራቅ አውሮፓ ሳይሆን ደቡብ አፍሪካ ነው።
የሰቆቃ ልጆች እና የብሔር አፓርታይድ በሚሉ ተከታታይ ፅሁፎች በዝርዝር ለመግለፅ እንደሞከርኩት አሁን በሀገራችን ያለው መንግስታዊ ስርዓት እ.አ.አ. ከ1948 – 1994 ዓ.ም ድረስ በደቡብ አፍሪካ ከነበረው የአፓርታይድ ስርዓት ጋር ከአመሰራረቱ እስከ ውድቀቱ ድረስ ፍፁም ተመሳሳይ ነው። ብዙዎች በደቡብ አፍሪካ የነበረው የአፓርታይድ ስርዓት በዘር ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ያስባሉ። ነገር ግን፣ ለአፓርታይድ ስርዓት መመስረት ዋና ምክንያቱ ዘረኝነት አይደለም። የአፓርታይድ መነሻ ምክንያቱ እ.አ.አ. ከ1899 – 1902 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ነጭ ሰፋሪዎች እና በእንግሊዞች መካከል የተካሄደው ¨The Second Boers War” ነው። ይህ ጦርነት በነጮች መካከል የተካሄደ ጦርነት እንጂ በጥቁሮችና ነጮች መካከል የተካሄደ አልነበረም።
የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካን ሕዝብ በዘር ሀረግና በቆዳ ቀለም ነጮች፥ ጥቁሮች፥ ሕንዶችና ቅይጦች (colored) በማለት ለአራት ይከፍላቸዋል። ሆኖም ግን፣ የፀረ-አፓርታይድ ትግሉ ሲካሄድ የነበረው በዋናነት በጥቁሮችና በነጮች መካከል ነው። የአፓርታይድ ስርዓት መሰረታዊ ዓላማ ከሀገሪቱ ሕዝብ ውስጥ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ነጮችን የፖለቲካ የበላይነት ማረጋገጥ ነው። ለዚህ ደግሞ በሀገሪቱ 70% የሚሆኑትን ጥቁሮች በጎሳና ብሔር መከፋፈል አለበት።
በዚህ መሰረት፣ የአፓርታይድ ስርዓት የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ሕዝብን በጎሳና ብሔር ለአስር ክልሎች ከፋፍሏቸዋል። እያንዳንዱ ክልል ራሱን በራሱ የማስተዳደር ስልጣን አለው። ነገር ግን፣ የአንዱ ክልል ነዋሪ በሌላኛው ክልል ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ በሕግ የተከለከለ ነበር። ይህ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ የጋራ አጀንዳና የተቀናጀ እንቅስቃሴ እንዳይኖራቸው የታለመ ነው።
የአፓርታይድ ስርዓት የአነስተኛ ብሔርን የስልጣን የበላይነት ለማረጋገጥ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን ሕዝቦች በጎሳና ብሔር በመከፋፈል ላይ የተመሰረተ ስርዓት ነው። አሁን በኢትዮጲያ ያለው ፖለቲካዊ ስርዓት በደቡብ አፍሪካ ከነበረው ጋር ፍፁም ተመሳሳይ ነው። የህወሓት/ትግራይ የበላይነትን ለማስቀጠል በሀገሪቱ አብላጫ ድምፅ ያላቸውን በተለይ የአማራና ኦሮሞ ሕዝቦች በመለያየት ላይ የተመሰረተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ፣ እ.አ.አ. ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ወደጎን በመተው የመብትና ነፃነት ጥያቄያቸውን በጋራ መጠየቅ ሲጀምሩ የአፓርታይድ መንግስት የወሰደው እርምጃ አሁን በሀገራችን ለሚስተዋለው የፖለቲካ ቀውስና አለመረጋጋት መንስዔን፣ እንዲሁም በሁለቱ ስርዓቶች መካከል ያለውን ተመሳሳይነት በግልፅ ይጠቁማል።
እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ አመፅና ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። ልክ ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች እንደታየው እ.አ.አ. በ1984 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ አመፅና ተቃውሞ ተቀስቅሶ ነበር። በሁለቱም አጋጣሚዎች የመንግስት እርምጃ አንድና ተመሳሳይ ነበር። የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማዳፈን ያለማቋረጥ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ምክንያት፣ የሕዝቡ ተቃውሞ ወደ ሁከትና ብጥብጥ እያመራ ሄደ።
ይህን ተከትሎ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ መሪ የነበሩት “Pieter Willem Botha” ልክ እንደ ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥልቅ ተሃድሶ በማድረግ ለሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ቃል ገቡ። የጠ/ሚ ኃይለማሪያም ንግግር ለሁላችንም የቅርብ ግዜ ትዝታ ስለሆነ እዚህ መድገም አያስፈልግም። የአፓርታይዱ መሪ ንግግርና የተሃድሶ እንቅስቃሴ ግን “Stephen Ellis” የተባለው የዘርፉ ምሁር ባቀረበው በጥናታዊ ፅሁፍ እንዲህ ገልፆታል፡-
“…in a series of speeches, Botha seemed to try to direct the country into reformist paths and away from the racial “Apartheid”…. What is certain is that his idea of ‘healthy power sharing’ meant he would cling to ‘group rights’ as a means of maintaining White control, which he claimed was still in the best interests of South Africa….A changing and increasingly volatile South African society led to the civil insurrection of 1984 and its repercussions around the country. Botha’s response was the repression of activists and liberation movements under a state of emergency. The reform policy stagnated.…” The Historical Significance of South Africa’s Third Force, Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299.
ይሁን እንጂ የሁለቱም ሀገራት መንግስታት ስር ነቀል ተሃድሶ ማምጣት ተሳናቸው። ከዚያ ይልቅ፣ የሕዝቡን የመብትና ነፃነት ጥያቄ በኃይል ለማፈን ጥረት ማድረግ ቀጠሉ። ሆኖም ግን፣ የሁለቱም መንግስታት እርምጃ የሕዝቡን ቁጣና ተቃውሞን ይበልጥ እንዲባባስ አደረገው። በዚህ ምክንያት፣ እ.አ.አ. በ1986 በደቡብ አፍሪካ፣ ባለፈው የ2009 ዓ.ም ደግሞ በኢትዮጲያ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ታወጀ።
በሌላ በኩል የአፓርታይድ ስርዓት የመከላከያና ድህንነት ኃላፊዎች በሕቡዕ ሦስተኛው ኃይል (The third Force) የተባለ ፀረ-አብዮታዊ ቡድን አቋቋሙ። ይህ ከክልል ሚሊሺያዎችና ልዩ ፖሊስ ኃይል የተወጣጣው ቡድን እንደ ዝምባብዌና ሞዛምቢክ ባሉ ጎረቤት ሀገራት የነበረውን የአማፂያን እንቅስቃሴ እንዲያውኩ የተቋቋሙ ነበሩ። የአሰቸኳይ ግዜው ከታወጀ በኋላ ግን በደቡብ አፍሪካ ጦር ወታደራዊ ስልጠና እና ትጥቅ ተሰጥቷቸው የፀረ-አፓርታይድ ትግሉን በማጨናገፍ ተግባር እንዲሰማሩ ተደረገ። የአፓርታይድ ስርዓት በተለይ በደቡብ አፍሪካ “KwaZulu Natal” በሚባለው ክልል የታየውና ዛሬ በሶማሊ ክልል እየታየ ያለው ፍፁም ተመሳሳይ ነው።
“In April 1986, the State Security Council had endorsed guidelines for a strategy for counter-revolutionary war which, among other things, emphasised that the forces of revolution should not be combatted by the security forces alone, but also by ‘anti-revolutionary groups such as Inkatha … as well as the ethnic factor in South African society’. In the following months, specifically ethnic organisations were armed and trained in KwaZulu and Ciskei, while anti-ANC groups in other places were encouraged and armed in the form of kitskonstabels or special policemen and vigilantes….  In effect, military units, which had carried out the destabilisation of neighbouring countries, were now implementing similar strategies at home, on the instructions of the State President, the State Security Council and the head of the [South Africa Defense Force]”  
Journal of Southern African Studies, Vol. 24, No.2. (Jun., 1998), pp. 261-299
በአጠቃላይ፣ በተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ-በእርስ ግጭት ለመፍጠር የተደረገው ጥረት ዛሬ በአንዳንድ የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊና ደቡብ ክልሎች እየታየ ካለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ፣ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ስርዓት በተለያዩ ብሔሮች መካከል የአርስ-በእርስ ግጭት በመፍጠር የነጮች የበላይነትን ለማስቀጠል ካደረገው ጥረትና ካስከተለው ውጤት በመነሳት ሀገራችን ኢትዮጲያ ወደየት እየሄደች እንደሆነ መገመት ይቻላል።
በደቡብ አፍሪካ በተለይ እ.አ.አ. ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የጥቁር ጎሳዎችና ብሔሮች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት ለመፍጠር በሕቡዕ የተሰራው ስራ እ.አ.አ. ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ፍሬ አፈራ። በእርግጥ ከመርዛማ ዛፍ መልካም ፍሬ አይጠበቅም። በእነዚህ አራት አመታት ውስጥ ብቻ በተነሳ ሁከትና ብጥብጥ 14,000 ደቡብ አፍሪካዊያን ሕይወታቸውን አጥተዋል።  እ.አ.አ. ከ1948 ዓ.ም የአፓርታይድ ስርዓትን ለመጣል በተደረገው ትግል ከተገደሉት ሰዎች ከ1990 – 1994 ዓ.ም ባሉት አራት አመታት ውስጥ ብቻ የተገደሉት ይበልጣል። ሀገራችን ወደየት እያመራች እንደሆነ ለማወቅ ለሚሻ ከዚህ በላይ ጠቋሚ ማስረጃ አይገኝም። አዎ…ኢትዮጲያ ወደ እርስ-በእርስ ግጭትና ዕልቂት እያመራች ነው!

Monday, September 25, 2017

የተፈናቃዮች ቁጥር አሁንም እየጨመረ ነው ወደ መቶ ሺህ ደርሷል፡፡



Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች |


(ቢቢኤን) በሰሞነኛው የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል ግጭት የተፈናቃዮች ቁጥር አሁንም እየጨረመ መሆኑ ታወቀ፡፡ መረጃዎች እንደጠቆሙት፣ የተፈናቃይ ሰው ቁጥር ወደ መቶ ሺህ ደርሷል፡፡ ድርጊቱ የተከሰተው በአጭር ጊዜ ውስጥ በመሆኑ፣ የተፈናቃዩን ሰው ቁጥር ለሰሚ አስደንጋጭ አድርጎታል፡፡ ግጭቱ አሁንም ሙሉ በሙሉ መፍትኤ አለማግኘቱ፣ የተፈናቃዮችን ቁጥር ከዚህም ይበልጥ ሊያንረው እንደሚችል ስጋት ፈጥሯል፡፡ ከአንድ ወር በላይ ለሆነ ጊዜ የዘለቀው የሁለቱ ክልሎች ግጭት፣ አሁን ላይ ሙሉ ለሙሉ መፍትኤ አግኝቷል የሚባልበት ደረጃ ላይ ገና አልደረሰም፡፡

ግጭቱ ከፍተኛ ጉዳት ያስከተለ እና እያስከተለ ሲሆን፣ በተለይ ተፈናቃዮችን በተመለከተ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጆሮ ጭው የሚያደርጉ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ አንዳንድ መረጃዎች በበኩላቸው የተፈናቃዮችን ቁጥር እስከ 120 ሺህ ሲያደርሱት ሌሎች ደግሞ እስከ መቶ ሺህ ይገምቱታል፡፡ ተፈናቃዮችን በተመለከተ የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ትክክለኛ ቁጥር ማስቀመጥ አልቻለም፡፡ በተከሰተው ግጭት ከሁለቱም ወገኖች የተፈናቀሉ ሰዎች ቢኖሩም፣ የላቀውን ወይም ከ95 ፐርሰንት በላይ የሚሆነውን ቁጥር የያዙት ግን የኦሮሞ ተወላጆች ሆነው ተገኝተዋል፡፡

የተፈናቃዮች ቁጥር እንዳለ ሆኖ ደግሞ፤ የሟቾችን ቁጥር በተመለከተም የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ በተከሰተው ግጭት የተነሳ በጠቅላላው ከሁለቱ ወገኖች እስከ 900 የሚደርስ ሰው ህይወቱን አጥቷል፡፡ ሟቾችን በተመለከተም በመንግስት በኩል ትክክለኛ መረጃ እየተሰጠ አይደለም፡፡ መንግስት ግጭቱ ብዙም ጉዳት አላስከተለም ለሚል ፕሮፓጋንዳ ሲል ብቻ፣ የሟቾች እና ተፈናቃይ ሰዎችን ቁጥር አሳንሶ እየተናገረ ይገኛል፡፡ ሆኖም የመረጃ ምንጮች ግን፣ የሟቾችን ቁጥር 900 ላይ ሲያቆሙት፣ የተፈናቃዮችን ቁጥር ደግሞ እስኪ 100 ሺህ ያደርሱታል፡፡

አቶ ለማ መገርሳ የኢሬቻ በዓል እንዳይከበር ማዘዛቸው ተሰማ


 


አባይ ሚዲያ
በወንድወሰን ተክሉ
የኦሮሚያ ክልል መስተዳድር ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ የዘንድሮውን ኢሬቻ ሃይማኖታዊ ክብረ በዓል እንዳይከበር ውሳኔ መስጠታቸው ታወቀ።
በትናትናው ዜና ዘገባችን የኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳድር በመጪው ጥቅምት 1 ቀን 2017 በቢሾፍቱ ለሚከበረው የኢሬቻ ክብረ በዓል ላይ ክልሉ ምንም አይነት መሳሪያ የታጠቀ ወታደርም ሆነ ፖሊስ ሃይል እንዳይኖር አዟል በሚል የዘገብን ሲሆን ዜናውን ከኢትዮጵያ የተከታተሉ ምንጮቻችን እውነተኛው ታሪክ በተዘገበው መልኩ አይደለም በማለት አዲስ መረጃ አቀብለውናል።
እንደምንጮቻችን አገላለጽ አቶ ለማ መገርሳ ባለፈው ነሀሴ ወር በቢሾፍቱ ከተማ የ2016ቱን ኢሬቻ ሰማእታት መታሰቢያ ሀውልት ከመረቁ በኋላ ከኦህዴድ ካድሬና ከኦሮሚያ ዞኖች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባ የዘንድሮውን [የጥቅምት 2017 ማለታቸው ነው] ኢሬቻ በዓል ሁላችንም በየቤታችን በራችንን ዘግተን ባለፈው ዓመት ያለቁብንን ወገኖች በማሰብ የምናከብረው ይሆናል የሚል ውሳኔ እንደወሰኑ ምንጮቻችን ገልጸዋል።
በውሳኔውም ማግስት አቶ ለማ መገርሳ የኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳድር የ2017ቱን ዓመታዊ ኢሬቻ በዓል ሁሉም የኦሮሞ ተወላጅ እቤቱ ሆኖ ባለፈው ዓመት የሞቱትን ወገኖቹን በመዘከር ለማክበር ስለወሰነ በቢሾፍቱ የሚካሄድ ዝግጅት የለም የሚል ደብዳቤ ለሶስት የፌዴራሉ ጽ/ቤቶች ማስገባቱን በወቅቱ በስብሰባው ላይ ተሳታፊ የሆኑት ምንጮቻችን ገልጸዋል።
የአቶ ለማ መገርሳ ደብዳቤ እና ውሳኔ እንዲደርሳቸው የተደረጉት የጠ/ሚ/ር ጽ/ቤት፣ የባህልና ቱሪዝም ም/ር ጽ/ቤት እና የደህንነት ክፍሉ ሲሆኑ ውሳኔውን ቀልባሽ ሌላ ውሳኔ የተሰጠው ከደህንነቱን ጽ/ቤት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በአቶ ለማ መገርሳ ሀሳብ አፍላቂነት የኦሮሚያ መስተዳድር የ2017 ኢሬቻ በዓልን በቤት ዘግቶ ለማክበር የተወሰነበት ምክንያት የደህንነትና የጸጥታ ስጋትን መሰረት በማድረግ ሲሆን በሁለተኛነት ደረጃ ደግሞ በ2016ቱ እልቂት አጠቃላይ የኦሮሞ ሕዝብ ወደ ቢሾፍቱ ላይመጣ ይችላል የሚል መረጃ ስላለ ነው በሚል ለጠ/ሚ/ሩ ቢሮና ለደህንነቱ ጽ/ቤት ማብራሪያ እንደሰጡ ምንጮቻችን ገልጸዋል።
ሆኖም በኦሮሚያ መስተዳድር በኩል የተወሰደው የመፍትሄ ውሳኔ ተቀባይነት ባለመግኘት በአንጻሩም ጠቃሚ ነው ተብሎ የታመነበትን ተግባራትን ያካተተ ውሳኔን ከደህንነት ቢሮ በመሰጠቱ የአቶ ለማ መገርሳ መስታዳድር ውሳኔውን ቀልብሶ የተሰጠውን ትእዛዝ እሱ ከሚመራው መስተዳድር የተሰጠ በማስመሰል እየተገበረ ነው ያለው በማለት ሁኔታውን ገልጸዋል።
በአቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የደህንነት ጽ/ቤት ከኦሮሚያ መስተዳድር በኩል የቀረበለትን ውሳኔና ምክንያት መሰረት በማድረግ ባወጣው ትእዛዝ ከእያንዳንዱ ኦሮሚያ ዞን በመንግስት [በኦህዴድ ማለት ነው] እየተመለመሉ እንዲመጡ ለዚህም ተግባር የኦሮሚያና የፌዴራል መንግስት በቂ ትራንስፖርት እንዲያዘጋጁ-ከ900 እስከ 1,500 ሲቪል የለበሱ ወታደሮች እንዲሰማሩና የእለቱን ሀይማኖታዊ ፕሮግራም በኦህዴድ አባልነቱና ታማኝነቱ የታወቀን ካድሬ/አባ ገዳ ወይም የሀገር ሽማግሌ ብቻ እንዲመራው ማድረግና መድረኩን በአጠቃላይ ሲቪል በለበሱ ወታደሮች ማስጠበቅ በሚል ትእዛዝ መሰረት ነው ዛሬ የአቶ ለማ መገርሳ ጽ/ቤት የኢሬቻን በዓል በተመለከተ ማንኛውንም መግለጫም ሆነ አዘገጃጀት እያደረገ ያለው ሲሉ አስረድተዋል።
የኢሬቻን በዓል ካለማክበር ይልቅ በእኛ ቁጥጥር ስር አድርገን ማክበሩ ታላቅ ፖለቲካዊ ፋይዳ አለው የሚል እድምታ ከደህንነትና የባህልና ቱሪዝም ቢሮ እንደተያዘ ለማወቅ ተችላል።
በ2016ቱ ዓመታዊ የኢሬቻ ክብረ በዓል ላይ ለመሳታፍ በተገኘው ከ3-4 ሚሊዮን ህዝብ ላይ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎችና ወታደሮች በወሰዱት እርምጃ ቁጥሩ ከ700 በላይ ህዝብ እንዳለቀ የተገለጸ ሲሆን በመንግስት በኩል ዛሬ ድረስ የማቾቹን ቁጥር በ55 ላይ ገድቦ መግለጹ ይታወቃል።

Sunday, September 24, 2017

ህዝብ የሚጠየፋቸው ገዢዎች እና ክፉ በሽታቸው – ግዛቸው አበጋዝ



  
By ሳተናውSeptember 24, 2017 23:12


 

ግዛቸው አበጋዝ ፤ ሳሰካችዋን ካናዳ፣
መስከረም 2010  
በኢትዮጲያ ታሪክ ውስጥ እንደወያኔ በህዝብ የሚጠላ ገዢ አላየሁም፤ አልሰማሁም እንዲሁም አላነበብኩም፡፡ በዚህ ወቅት ኢህአዴግን ሀገሪቱን የሚያስተዳድር መንግስት ብሎ እና ሹማምንቱን ደግሞ ህዝቡን የሚመሩ መሪዎቹን ብሎ መጥራት አይደለም መስማት ህሊናን የኮሰኩሳል፡፡ ምክንያቱም በሀገሪቷ እና በህዘቧቿ ላይ ያደረጉት እና የሚያደርጉትን ስትመለከት፡፡ ከተራ ወንበዴነት እስከ ሀገርን እና ህዝብን ለዘርፍ የመጣ የውጪ ጠላት የሚፈፅመውን ፈፅመዋል፡፡
እነሱንም እንመራዋለን የሚሉት ህዘብም በተግባራቸው ይጠየፋቸዋል፡፡ ከቀንን ወደ ቀንም የፓርቲው እና የሹሞቹ ስም ሲነሳ እንደ ዛር የሚያንዘ ዜጋ ከትላንቱ ይለቅ ዛሬ ላይ ቁጥሩ የትዬለሌ አሻቅቧል፡፡ ይህ በርሃብ፣ በስራ አጥነት፣ በነፃነት እጦት፣ በሙስና እና በመልካም አስተዳደር እጦት የሚሰቃይው ዜጋ ይህ ከፉ ስርአት ባመጣበት ሌላ የዘር በሽታ ዛሬ ላይ በእርስ በርስ ግጭት መታመስ ከጀመረ ውሎ አድሮአል፡፡
የኢትዮጲያ ህዝብ የሚጠየፈው አምባገነን ስርአት የዘራው ክፉ የዘር ስርአት (በሽታ) ዛሬ ላይ ፍሬ አፍርቶ የሀገሪቱ ግንባር ቀደም ስጋት እየሆነ መጥቷል፡፡ ይህም ክፉ ስርአት በህዝብ ጫንቃ ላይ የሚቆይ ከሆነ የሀገሪቱን ህልውና እና ዘላቂ ሰላም ላይ ምን ሊያሰከትል እንደሚችል ለመገመት ጠቢብ መሆን አያስፈልግም፡፡  ወያኔ የሚከተለውን የዘር ፖለቲካ ክፉ በሽታ እያለኩ  በፅሁፉ ውሰጥ የምጠቀመው ለሀገራችን አንድነት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እንደሚያመዝን በአለፉት 26 አመታት አይተነዋል፡፡ በተጨማሪም አንድ ዜጋ በዘሩ ከሚያገኘው ነፃነት ይልቅ በዜግነቱ የሚያገኘው ነፃነት ሚዛን ስለሚደፋ እና የሚያኮራ በመሆኑ ነው፤ የዘር ፖለቲካቸውን ክፉ በሽታ ያልኩት፡፡
ወያኔ ስልጣል ላይ በቆየበት ሩብ ምተአመት ውስጥ ሀገራችን ላይ ከዚህ ቀደም ተከስተው የማያውቁ ነገሮች ዛሬ ላይ በስፋት ተከስተዋል፡፡ ከነዚህም ውስጥ ዘር ያማከሉ ጦርነቶች እና ስደቶች ወይንም ከቦታ መፈናቀሎች ዋናዎቹ ናቸው፡፡ እነዚህን ቀንን ወደ ቀን እየተባባሱ  የመጡ የክፉው በሽታ ውጤቶች ሀገራችን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ በአጭሩ እንቃኘው፡፡
በቅርቡ በኦሮሚያና ሶማሌ አዋሳኝ አካባቢዎች በተቀሰቀሰው ግጭት ከ50 ሺ በላይ ኦሮሞዎችን ሲያፈናቅል በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ቀጥፏል። በዚህ ግጭት ታጣቂ የወያኔ ሀይሎች (የሶማሌ ክልል ልዩ ሀይል) ተሳትፈውበታል፡፡ ደብረ ዘይት ላይ የእሬቻ በአል ሊያከብር በወጣው ሰላማዊ ህዝብ ላይ ጥይት ያርከፈከፈው የኦሮሚያ ልዩ ሀይል ወይንም የፈደራል ወታደር ከሞት ተርፎ ወደ ጅጅጋ እና አጎራባች ከተሞች የሚሰደደው ዜጋን መኪና እያስቆመ ሲገደል፣ ሲገረፍ እና አካሉ ሲጎድል የት ነበር ያስብላል፡፡ እየፈሰሰ ያለው የወገኖቻችን ደም እና የስቃይ ጩኸት የሚሰማ መጥፋቱ እጅግ የሚያሰቆጭ ቢሆንም  ግጭቱን እሰከ ዛሬ ድረስ እንዳይበርድ ለምን እንደተገለገ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡
ሌላኛው የክፉ በሽታው ምሳል የሚሆኑት በቤንሻንጉል ክልል ጉራፍ ወረዳ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ገበሬዎች ላይ የዛሬ አምስት አመት አካባቢ የተከሰው ሞትና መፈናቀል፣ በጋንቤላ ክልል በንዌሮች እና በአኝዋክ ጎሳች መካከል የተካሄደው አሰቃቂ ጭፍጨፋ ናቸው፡፡
የነዚህ ከላይ የጠቀስኳቸውን ሶስት አሳዛኝ ክስተቶች ለማስረጃነት አነሳሁ እንጂ እነዚህ ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ መሽቶ እስኪነጋ መዘርዘር ይቻላል፡፡
መታወቅ ያለበት ዋናው ጉዳይ የግጭቶች መንስኤ በህዝብ ጫናቃ ላይ የሰፈረው ክፉ ስርአት መሆኑ ነው፡፡ ስርአቱ ለመሆኑ ደግሞ እኛ ተጎጂዎቹ / የምንኖረው/ አይደለንም አልፎ ሂያጅ የተቀረው የአለም ሰው ያገነዘበዋል፡፡ እኛን የስርአቱ ገፈት ቀማሾች የሆነውን ዜጎች እያሳሰበ የመጣው ይህ ዘርንና ክልልን ያማከለ ግጭት አለም ላይ ያሉ ጥልልቅ ሚዲያዎችን ትኩረት አግኝቷል፡፡ አልጄዚራም ምን እንደሸተተው ባይታወቅም በአለም ለጋዜጠኞች በአደገኝነት ሶስተኛ ደረጃ ላይ ወደ ሰፈረችው ኢትዮጲያ ተጉዞ ቢሮውን ከትሟል፡፡ ቢቢሲ ኬንያ ሆኖ ጆሮውን ከቀሰረ ሰነባብቷል ለዛውም በአራት የሀገራችን ቋንቋ ስርጭችን አካቶ፡፡ በነገራችን ላይ እነዚህን ሚዲያዎች እና የዘገባዎች መንፈስ በሌላ ፅሁፍ የምመለስበት በመሆኑ ለዛሬ በዚሁ ማለፍ እወዳለሁ፡፡ ነገር ግን እየተከሰተ ያለው ዘርንና ክልልን ያማከለ ግጭት ያሳሰባቸው ሁለት ኢትዮጲያዊ ምሁራን ያሉትን መጥቀስ እፈልጋለሁ፡፡
የቀድሞው የህውሀት መስራችና አመራር የነበሩት ዶ/ር አረጋዊ በርሄ ሰሞኑን ‹‹ትውልድ ፈታኝ ቀውጥ!›› በሚል ርዕስ ባስነበቡን ፅሁፋቸው በዚህ ክፉ በሽታ  የተሰማቸውን ስጋት እንዲህ አስፍረውታል፡፡ ‹‹ይህ እየተሰራጨ ያለው ክፉ ክስተት ማቆምያ ካልተበጀለት ሃገር-አልባ ሊያደርገን ይችላል። ቀውሱን የፈጠረው የህወሓት/ኢህኣዴግ ገዢ መደብ ለመሆኑ አጠያያቂ አይደለም። ይህ ሀላፊነት የማይሰማው አምባገነን ቡድን ገና ከጅምሩ የወጠናቸው ደንባራና ስግብግብ ፖሊሲዎች እንዲሁም አረመንያዊ የአገዛዝ ዘይቤዎች አሁን ከምንገኝበት አረንቋ ውስጥ ከቶናል።››
እኝህ ወያኔን ከጥንስሱ ጀምሮ የሚያቁት ሰው ስጋታቸው ‹‹አገር-አልባ›› እስከመሆን ያደረሰው የቀድሞ ወዳጆቻቸውን አላማ ሳያውቁት እንዳልሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን እንዲህ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደዚህ በፍጥነት ስጋ ለብሶ ማየታቸው ሳያስደነግጣቸው አልቀረም፡፡ ይህ ማለት ግን ስጋቱ እና ድንጋጤው የሳቸው ብቻ ነው ማለት አይደለም፡፡ 26 አመት ሙሉ ሁሉንም ዜጋ በየደረጃው እና በሚያየው አስጨንቆታል፡፡
ሌላኛው ታዋቂ የኢኮኖሚው ዘርፍ ምሁሩ ዶ/ር አክሎክ ቢራራ በዚህ ሳምንት ‹‹በኢትዮጵያ ላይ ያንዣበበውን የውጭ ኃይሎች ጫናና ሴራ እንዴት ለመቋቋም ይቻላል? በአዲሱ ዓመት ለጠባብ ብሄርተኞች እጃችን ላለመስጠት እንወስን›› በሚል ገራሚ የመጀመሪያ ክፍል  ጥናታዊ ፅሁፍ አስነብበዋል፡፡ ዶ/ሩ በፅሁፋቸው ውስጥ ‹‹የተፈጥሮ አደጋዎችና ሰው ሰራሽ ቀውሶች ለኢትዮጵያ ቀጣይነት አደጋዎች ናቸው።›› በሚል በሰጡት ንዑስ ርእስ ‹‹ዛሬ በኢትዮጵያ በመሬት ላይ የሚታየው የፖለቲካ ሁኔታ ከተፈጥሮ አደጋዎች ጋር–ለምሳሌ፤ ከድርቅ ረሃብ፤ ከድህነት፤ ከአገር ውስጥ የሕዝብ ፍልሰት፤ ከተስቦ በሺታዎች ወዘተ… ጋር ሲደማመር ኢትዮጵያን ወደማይመለስ ውድቀት እንድታመራ ያደርጋታል። ይህ፤ ከመጥፎ አገዛዝ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ሁኔታ እየተባባሰ ሲሄድ የሚታየው ክስተት ምንን ያንጸባርቃል? ብየ ራሴን ስጠይቅ መልሱ ሆነ ተብሎ የተጸነሰውና ሊቆም የማይችል የሚመስለው የብሄር የማንነት ጥያቄ እየተስፋፋና እየከረረ መሄዱን ያሳያል የሚል ይሆናል።›› ሲሉ አስፍረዋል፡፡
የኢኮኖሚ ምሁሩ ወያኔ በሀገራችን ህዘቦች ውስጥ የዘራውን ክፉ የዘር ስርአት ከተፈጥሮ በሽታዎች ጋር ተዳምሮ የሚያስከትለው ጉዳት በቀላሉ የማይታከም መሆኑ ቢያሰጋቸውም የዘር ፖለቲካው ብቻ በራሱም ለሀገራችን ነቀርሳ መሆኑን ነግረውናል፡፡
በአጠቃላይ በሀገራች ላይ የተከሰቱ ደም አፋሳሽ ግጭቶችን ፣ የንብረት ውድመቶችን ተመልክቶ እና የሙሁራኑን የስጋቶች ጥልቀን አሰተውሎ ዝም ብሎ መቀመጥ የሚችል ዜጋ ያለ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህም ሀገራችን ኢትዮጲያ እንደ ሀገር እንደትቀጥልና በህዝቦች መካከል ያለው አንድነት እንዲጠነክር መስራት ያስፈልጋል፡፡   ወያኔ የዘራው ክፉ በሽታ እንዲከስም በጋራ መቆም ፍቱን መዳኒቱ፤ ስርአቱን ከስሩ ነቅሎ መጣል ደግሞ የሀገሪቱ ፈውስ ነው፡፡   ሰለዚህ ……
ስለዚህ ‹‹ተነሳ ተራመድ ክንድህን አበርታ ….›› እያልን እየዘመርን (የቀድሞው ስርአት ናፋቂዎች ብንባልም)  ለሀገችን መስራት ነው፡፡ ጥያቄህ ለሀገሬ ምን ልስራ ከሆነ ራስህን ምን መስራት እችላለሁ ብለህ ጠይቅ ያኔ መልሱን ታገኘዋለህ፡፡ እውነቱ ግን ሀገራችን የኛ የህዝቦችዋን የአንድነት ስራ ትሻለች፡፡ (አራት ነጥብ !!!)

በኢትዮጵያ የድርቅ ተጎጂዎች ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ታወቀ


Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች |


 



በኢትዮጵያ በድርቅ የተጠቃው ህዝብ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ታወቀ፡፡ በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 7 ሚሊዬን ሰው በድርቅ መጠቃቱ ይታወቃል፡፡ ለድርቅ ተጎጂዎቹ በአብዛኛው ድጋፍ እየተደረገ ያለው በውጭ ረድኤት ተቋማት ሲሆን፣ በዚህ ውስጥ የመንግስት ሚና እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ የውጭ ተቋማት ለድርቅ ተጎጂዎቹ በገንዘብም ሆነ በቁስ ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም፣ ከተረጂው ሰው ቁጥር አንጻር ግን እርዳታው በቂ ሆኖ አልተገኘም፡፡

የውጭ ተቋማት እያደረጉ ያሉት ድጋፍ በትክክል ቢሰላ በበቂ ሁኔታ ሊከፋፈል የሚችለው ለ6 ሚሊዬን ሰዎች ብቻ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ለሁሉም ማለትም ለ8 ነጥብ 7 ሚሊዬን ህዝብ እርዳታውን ለማዳረስ ሲባል ብቻ፣ እርዳታውን ብዙ ቦታ የመቀነጣጠብ ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ይህም እየተደረገ ያለው የተገኘውን እርዳታ ለሁሉም ለማዳረስ ሲባል መሆኑን የገለጹት መረጃዎች፣ በዚህ ሁኔታ ብዙም መንገድ መጓዝ አዳጋች መሆኑንም ጠቁመዋል-መረጃዎቹ፡፡

ለዚህም ሲባል ተጨማሪ እርዳታ ለማግኘት የተለያዩ ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ጥሪ እያቀረቡ ናቸው፡፡ መንግስት በበኩሉ፣ ተቋማቱ ‹‹ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የተረጂዎችን ቁጥር ከፍ አድርገው እየተናገሩ ነው፡፡›› የሚል ስሞታ አቅርቧል፡፡ አንድ ዓለም ዓቀፍ የረድኤት ተቋም የተረጂዎችን ቁጥር ከፍ በማድረግ ምን ዓይነት ጥቅም ሊያገኝ እንደሚችል ግን መንግስት የገለጸው ነገር የለም፡፡ እርዳታ አቅራቢ ተቋማትን በተደጋጋሚ በመውቀስ የሚታወቀው መንግስት፣ ወይ ራሱ ለተረጂዎች ድጋፍ አያደርግ ወይም ድጋፍ የሚያደርጉ ተቋማትን መተንኮስ አያቆም የሚል ተደጋጋሚ ክስ ሲቀርብበት ይደመጣል::

የስኳር ፋብሪካዎች በመለዋወጫ ዕቃ እጦት ስራ አቁመዋል


Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች |


 


በኢትዮጵያ የሚገኙ የስኳር ፋብሪካዎች በመለዋወጫ ዕቃ እጦት ስራ ማቆማቸው ተጠቆመ፡፡ የቢቢኤን ምንጮች እንደጠቆሙት፣ መተሐራ፣ ፊንጫ እና ወንጂ ስኳር ፋብሪካዎች ለጥገና ተብለው ስራ ካቋረጡ ሳምንታት ቢቆጠሩም፣ መንግስት የመለዋወጫ ዕቃ ማቅረብ ባለመቻሉ ስራ ፈትተው ቆመዋል፡፡ የፋብሪካዎቹ ሰራተኞች መንግስት የመለዋወጫ ዕቃ እንዲያቀርብላቸው ተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ምላሽ ማግኘት አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

የስኳር ፋበሪካዎቹ የተገጠመላቸው ቦይለር ጥገና እንደሚያስፈልግው የገለጹት የስኳር ፋበሪካው ሰራተኞች፣ በተጨማሪም የተርባይን ግዢ ጥያቄ ቢያቀርቡም የሚመለከተው አካል ምላሽ እንዳልሰጣቸው ሰራተኞቹ አክለው ጠቁመዋል፡፡ ጉዳዩ የሚመለከተው እና ጥያቄ የቀረበለት የስኳር ኮርፖሬሽን ፋብሪካዎቹ ላቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ ያልሰጠው በምን ምክንያት እንደሆነ የታወቀ ነገር የለም፡፡ ሆኖም ምንጮች እንደሚጠቁሙት፣ ኮርፖሬሽኑ ፋብሪካዎቹ ለሚያስፈልጋቸው የመለዋወጫ እና የጥገና ዕቃዎች ምላሽ ያልሰጠው በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ ነው፡፡ የመለዋወጫ ዕቃዎቹ በአብዛኛው ከውጭ የሚገዙ እንደመሆናቸው፣ ሀገሪቱ አሁን ካለባት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት አንጻር ፋበሪካዎቹ የሚያስፈልጋቸውን የጥገና ዕቃ ማቅረብ አልተቻለም፡፡

በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የስኳር እጥረት መኖሩን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አንድ ኪሎ ስኳር እስከ 60 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝ የሚገልጹት መረጃዎች፣ መንግስት ለህብረተሰቡ ማቅረብ ያለበትን ያህል ያስኳር ፍጆታ እያቀረበ እንዳልሆነም ከመረጃዎች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ በሀገሪቱ የስኳር እጥረት በተከሰተበት በዚህ ሰዓት መንግስት ወደ ኬንያ ስኳር መላኩ ተቃውሞ ሲያስነሳበት የከረመ ሲሆን፣ ወደ ኬንያ የተላከው ከ44 ሺህ በላይ ስኳርም ተረካቢ አጥቶ ሞያሌ ድንበር ላይ ጸሐይ እና ዝናብ እየተፈራረቀበት ይገኛል፡፡