Monday, October 3, 2016

አሁን የደረሰን ዜና ህዝባዊ አመፁ ተፋፍማል

ትላንትና በእሬቻ በአል ላይ የሞቱት የኦሮሞና የአማራ ኢትዮጵያዊ ወንድሞቻቸው ደም ሰላም የነሳቸው ወገኖቻችን የወንድሞቻቸውን ደም ለመመለስ ዛሬ በወሎ የዋግ ሹሞች ሃገር ሰቆጣ ፣ በጎጃም ፍኖተ ሰላም ፣ በጎንደር ታች አርማጭሆ ፣ እና ደባርቅ አካባቢ፤ በሸዋ። መንዝ መራ ቤቴ ቀበሌ(13) ህዝቡ የወያኔን ሰራዊት እያሽመደመደው ይገኛል።
ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የወያኔ ሰራዊት ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ከነትጥቃቸው እየተደመሰሱ ነው።
በኦሮሚያም ትላንትና ቀትር ላይ በአንቦ የተጀመረው ትንቅንቅ ዛሬ አድማሱን አስፍቶ አብዛኛውን የኦሮሚያ ከተሞች ጨምሮ ወደ ገጠሩም ክፍል እያዳረሰ ነው።
ወያኔን ድራሹን ማጥፋት አለብን ወያኔ ሳይጠፋ ትግላችንን አናቆምም። በማለት የተጀመረው አመፅ ከአምቦ ትላንትና ቢነሳም ዛሬ ተጠናክሮ። ጉዞውን በማስፋፋት፦ በሀረርጌ ማዲቾቲ ፥ በቦረና ዞን ቡል ሆና ከተማ፥ በጅማ በኑኑ ከተማ ፥ በቄለም ወለጋ ፥ በቄለም ወለቃ ፥ በምእራብ ሸዋ መቂት ከተማ ፥ በሙገር ፥ በእንጭኒ ፥ በሸኖና በበርካታ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች መንገዶችን እየዘጉ ከወያኔ የምድር ጦር ጋር የሚደረገው ተጋድሎ ተፋፍማል።
በርካታ የወያኔና ስርአቱን የሚደግፉ ግለሰቦች ንብረት ዶግ አመድ የሆነ ሲሆን” አብዛኛው የወያኔ መከላከያ ሰራዊት የህዝቡን የሞት ሽረት ትግል መቃቃም የተሳነበት ሁኔታዎች ታይተዋል።
የተቀራችሁ የክልል ከተሞችም ህባዊ ትግሉን ከወንድሞቻችሁ ጋር በመቆም ወያኔን ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ተባብረን በማስወገድ ሀገራችንን ነፃ እናውጣት በማለት መልእክቴን አስተላልፋለሁ። /አባ ኮስትር በላይ/ አመሰግናለሁ
ድል ለወገኔ
ሞት ለወያኔ\

No comments:

Post a Comment