Saturday, December 31, 2016

የቦብ ማርሊ ኣደባባይ ሊፈርስ ነው ። ሃውልቱም በቅርቡ ይነሳል ።


bob-marley-statue-addis-ababa
በቀድሞ ኢምፔሪያል ሆቴል ፊት ለፊት በስሙ በተሰየመው ኣደባባይ ላይ ተቀርጾ የሚገኘው የቦብ ማርሊ ሃውልት ሊፈርስ ነው
የአደባባዩ ኣለቦታው መገንባት የትራፊክ ፍሰቱን የተጨናነቀ በማድረጉ በሌሎች ስፍራ ሲደረግ እንደቆየው አደባባዩን ኣፍርሶ በትራፊክ መብራት ለመተካት እንደታሰበ እና ይህም እቅድ ወደ ተግባር ከመገባቱ በፊት ግን ፡ ተለዋጭ ቦታ እንዴት ይሰጠው እና በምን መልኩ ይነሳ በሚለው ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚነጋገር የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታውቋል ።
ይህ የቦብ ማርሊ ሃውልት መገንባቱን ተከትሎና እስከዛሬም ድረስ የሃውልቱን እዛ ቦታ መገኘት በሚደግፉና በሚቃወሙ የህብረተሰብ ክፍሎች መሃከል ብዙ ኣሉታዊና አወንታዊ አስተያየቶች ሲሰነዘሩበት የቆየ አጨቃጫቂ ሃውልት ነው ። ከቦብ ማርሊ የበለጠ ለዚች ሃገር ሰርተው በዋና መንገድ ላይ የተሰራ አደባባይ እና ሃውልት ይቅርና ትንሽ ጎዳና በስማቸው ያልተሰየመላቸው ሰዎች እያሉ ለሃገራችን ይሄ ነው የሚባል ፋይዳ ላልሰራ ሰው ለምን ሃውልት ይቆማል በሚሉት እና ድምጻዊውን እንደ የጥቁሮች ነጻ ኣውጭና የነጻነት ታጋይ አድርገው በሚቆጥሩት መሃከል ያለው ውዝግብ ሳይቆም ሃውልቱን ከስፍራው ለማንሳት መታቀዱ ታውቋል

Friday, December 30, 2016

​​ህወሓት ፀረ ወጣት!

ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌይ)

(ቃልኪዳን ካሳሁን)
በህወሓት የሚመራው መንግስት ኢትዮጵያና ህዝቦቹን በሃይል ከተቆጣጠረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በወጣቶች ላይ የሚያድርሰው በደል ተነግሮና ተፅፎ አያልቅም። በተለያዩ ጊዜያት ውስጥ ስርዓቱ በወጣቱ ክፍል ላይ እያሳደረ ያለው እንግልት ቀላል የሚባል አይደለም። በእንደዚህ ሁኔታ ውስጥ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ወጣቶች ስለሀገራቸውም ሆን ስለህዝባቸው ፍትህና ነፃነት እንዲሁም እኩልነት በሚያደርጉት ሰላማዊ ትግል ውስጥ ውድ ህይወታቸውን መሰዋዓት ያደረጉ፣ በየማጎሪያ ቤት ሆነው ዋጋ እየከፈሉ ያሉ፣ ሀገርንና ቤተሰቦቻቸውን ጥለው ተሰደው ስንት መከራና ስቃይ የሚፈራረቅባቸው እንዳሉ መዘንጋት የለበትም።
ይህ ስርዓት ስለህዝባቸውና ስለሀገራቸው ጉዳይ ያገባና የሚሉትን ወጣቶች ማሳደዱን ከቀን ወደቀን እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልሆነ ለዚህ ብዙ ማሳያዎች መግለፅ ይቻላል። ከተወሰኑ ወራት በፊት የህወሓትን አገዛ በቃኝ በማለት ህዝባዊ እንቢተኝነት ለማዳፈን የተጠቀመው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሰለባ የሆኑ አብዛኛው ወጣቶች እንደሆኑ የሚታወቅ ነው። አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ መከራና ስቃይ እየተቀበለ ያለው ወጣት ቀላል የሚባለ አይደለም።
ከአስቸኳይ ጊዜያ አዋጁ በፊትም ሆን በኋላ ጥቂት የማይባሉ ወጣቶች በህወሓት ማጎሪያ ቤት ሆነው ይህ ነው የማይባል ዋጋ እየከፈሉ ነው ያሉት። እነዚህ ወጣቶች ከስርዓቱ ጋር ተቀራርቦ መስራት አላቃታቸውም፤ ነገር ግን ስርዓቱ የለየለት ፋሺስታዊና አምባገነናዊ ስርዓት ስለሆነ ለስርዓቱ አለመገዛታቸው ትልቅ ዋጋ እያስከፈላቸው ይገኛል። እነዚህ ወጣቶች ስለሀገራቸውና ስለህዝባቸው ሲሉ ቀላል የማይባል አሻራ እያሳረፉ ይገኛሉ። በህወሓት ማጎሪያ ቤት ውስጥ ወድ ህይወታቸውን አሲዘው እንደሆነ ሁላችንም ልንረዳ ይገባል።
ህወሓት ፀረ ወጣት ነው! ሲል ለጎልማሳውና ለአዛውንቶች የተመቸ ስርዓት ነው ማለቴ አንዳልሆነ ልብ ልንል ይገባል። ህወሓት ፀረ ህዝብ፣ ፀረ ሀገር እንዲሁም ፀረ ታሪክ እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ህወሓት ፀረ ወጣት ነው ስል ስርዓቱን በሚቃወሙት ወጣቶች ብቻ ዙሪያ ተነስቼ አይደለም። ህወሓት ስርዓት አገልጋይ የሆኑ ወጣቶችንም በጥቅማጥቅም በመደለል ለስርዓቱ እንዲገዙ በማድረጋቸው ስለህዝብና ስለሀገር ያላቸው ስሜትና ሞራል እንዲጠፋ አድርገዋል፤ እያደረጉም ነው:: ለዚህም ነው ህወሓት ፀረ ወጣት ስርዓት እያልኩ ያለሁት።
የዛን ዘመን ጀግኖች አባቶቻችን ወጣት ሆነው ይቺህ ትልቅ ሀገር “ኢትዮጵያን” ያስረከቡልን እነሱም በዛን ዘመን ወጣት ሆነው ተዋግተው፣ ታግለው እንዲሁም ወድ ህይወታቸውን መሰዋት ከፍለው ነው አሁን የምንኖርባት ሀገር እንደ ሀገር እንድትጠራ ያደረጏት:: ህወሓቶች ስለ ነገው ሀገር ተረካቢ ወጣት ሳይሆን ጭንቀታቸው ስልጣናቸውን ከእጅ እንዳይወጣ ነው ጭንቀታቸው። ስለዚህ ህወሓትና ስርዓቱ ለዚህ ዘመን ወጣቶች ፀረ ወጣት ናቸው።
ዛሬም እንደሻማ እየቀለጡ ለሌላው ብርሃን እየሆኑ ያሉ ወጣቶችን እየተመለከትን ዝም ከማለት ከጎናቹሁ በመቆም እነሱም ሆነ እኛም በሰላምና በፍቅር የምንኖርባትን “ትልቁ ኢትዮጵያን” ከዚህ ፋሽስታዊና አምባገነናዊ ስርዓት ለማላቀቅ ዋጋ እየክፈለ ባለው ወጣቶች ስም እጅ ለእጅ ተያይዘን እንነሳ።
ጊ ዜ ው አ ረ ፈ ደ ም!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌይ

Thursday, December 29, 2016

በምስራቅ ሃረርጌ ቁምቢ በተነሳ ግጭት የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ | የኦሮሚያ ክልል ፕ/ት “የትናንሽ ጎሳዎች የድንበር ግጭት ነው” ሲል አጣጥሎታል

በምስራቅ ሃረርጌ ቁምቢ ወረዳ ዛሬ በሕወሓት መንግስት ጀነራሎች ይደገፋል እየተባለ የሚነገርለት የሶማሊ ክልል ልዩ ኃይል ፖሊስ በምስራቅ ሃረርጌ ሚኖ ወረዳ ከአካባቢው ነዋሪዎች እና ፖሊሶች ጋር በፈጠረው ግጭት የሰው ሕይወት መጥፋቱን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል::
እንደምንጮቹ ዘገባ በምስራቅ ሃረርጌ ቁምቢ ወረዳ ሚኖ ከተማና አካባቢው በነበረው ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ቢያንስ ከ10 የማያንሱ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ ተነግሯል:: ከምስራቅ ሃረርጌ ቁምቢ ወረዳ ነዋሪዎችም ሆነ ከሶማሊያ ልዩ ኃይል ወታደሮች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ቆስለዋል::
በአካባቢው የተነሳው ይኸው ግጭት ከክልሎች ድንበር መስፋፋት ጋር በተነሳ የማንነት ጥያቄ ነው ሲሉ ምንጮች ቢናገሩም የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ግን “የትንንሽ የጎሳዎች ጸብ ግጭት” ሲሉ መናገራቸው ተሰምቷል::
ምስራቅ ሃረርጌ ቁምቢ ወረዳ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ ውጥረቱ እንዳየለ ነው:: የሶማሊያ ክልል ወታደሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች በየፊናቸው ተፋጠው እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

በቁማችን ተሸጠን እያለቅን ነው | ሊነበብ የሚገባው ጥብቅ መረጃ

ለኢሃድግ ጽህፈት ቤት ለፓርላማ አባላት ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚመለከታቸው ሁሉ
የዛሬ 7 ዓመት ገደማ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንደተለመደው አንድ አገርን ለውጪ ሰው የመሸጥ ወንጀል ፈጽመዋል። ይኸውም የባህረኛ ማሰልጠኛ ተቋም በኢትዮጵያ ባህርዳር እንዲገነባ በሚፈቀድበት ጊዜ ለ30 ዓመታት የዚህ ዓይነት ትምህርት ቤት በአገሪቱ ሌላ ማንም እንዳይገነባና ይህ ኩባንያ ብቻ እንዲሆን አገሪቱን ግዴታ ማስገባታቸው ነው።
ጉዳዩ የሚመለከታቸው የበታች አካላት ይህንን ቢቃወሙም ማስፈራሪያ እየደረሳቸው የ30 ዓመቱ ጊዜ ወደ 15 ዝቅ እንዲል አስደርገዋል። ይህ ኩባንያ ይህ ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ ለፖሊስ እንኳን የማይፈቀድ እንደ ውሸት መመርመሪያ መሳሪያ እንዲያስገባ፣ የአገሪቱ ቀረጥ ከፋይ ያስገነባቸውን ትምህርት ቤቶችና ምርጥ ተማሪዎችን በመመልመልና ወደ ውጪ በመላክ ከፍተኛ የሆነ ጥቅም ከማጋባሱም በላይ፣ እነዚህን ልጆች በአብዛኛው በኢትዮጵያ ህዝብ ሃብት ለማሰልጠን አንድ ሚሊዮን ብር የሚያህል እዳ በማስፈረም በመሰረቱ ባሪያ ሆነው እንዲሰሩ ያስገድዳቸዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤት የወጡ ተማሪዎች ነጻነታቸውን ሙሉ በሙሉ ማጣታቸው ብቻ ሳይሆን በሄዱበት ቦታ ለመብታቸውና ለደህንነታቸው የሚቆረቆር ባለመኖር አስገድዶ እስከመደፈር የደረሱና ሰሚ ያጡ አሉ። ተማሪዎቹ በስነልቦና ላሽቀው እንዲወጡ አድርጎ እንዲያሰለጥን የተቀጠረው የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ስርዓት ወታደር የነበረ ሰው ነው። የዛሬው ሌላ አገሪቱን የመሸጥ ዝግጅት። ይህ አልበቃ ብሎ በዚሁ ዘርፍ ሌላ ወንጀል ዛሬ ሊሰራ ዝግጅቱ አልቋል። ይኸውም የኢትዮጵያ የመርከብ ስራና ሎጂስቲክ ድርጅትን ለቻይና መሸጥ ነው።
ይህ በተለይ ለምን አደገኛ የሆነ ነገር እንደሆነ ከዚህ በታች እንገልጻለን።
የኢትዮጵያ የመርከብና ሎጂስቲክ ድርጅት ምንም እንኳን የተወሰኑ መርከቦች ቢኖሩትም፣ ዋና ገቢው መርከቦች አይደሉም። ገቢውን በሚከተለው አማካኝነት ያገኛል። አንድ እቃ ወደ ኢትዮጵያ በሚገባበት ጊዜ ያንን እቃ ጭኖ የሚያመጣ ድርጅት ፈቃድ ያለው መሆን አለበት።
በኢትዮጵያ ፈቃድ ያለው ብቸኛ ድርጅት የኢትዮጵያ የመርከብ ስራና ሎጂስቲክ ድርጅት ብቻ ነው። ይህ በህግ የተቀመጠ ነገር ነው። ብቸኛ ድርጅት በመሆኑም ያለውድድር የፈለገውን ገንዘብ መጠየቅ ይችላል። ግን ይህ ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያ የመርከብ ድርጅት በቂ መርከቦች ስለሌሉት አንድ እቃ ለምሳሌ ከቻይና ወደ ኢትዮጵያ ሲጫን ሌላ የመርከብ ድርጅት ያንን እቃ ለመጫን የኢትዮጵያ መርከብ ድርጅት ፈቃድ መጠየቅ አለበት። ያንን ፈቃድ ለመስጣት ድርጅቱ ከጫኙ የመርከብ ድርጅት ኮሚሽን ይቀበላል።
ይህን ኮሚሽን ደግሞ እቃውን የጫነው ድርጅት ወደ ባለ እቃው፣ ባለ እቃው ደግሞ ያንን ሂሳብ ወደ ተጠቃሚው የኢትዮጵያ ህዝብ ያስተላልፋል። ያ ማለት እያንዳንዱ ወደ አገር ውስጥ ከሚገባ እቃ የኢትዮጵያ የመርከብ ድርጅቱ ምንም አገልግሎት ሳይሰጥ የኢትዮጵያን ህዝብ እየቀረጠ ይኖራል። በዚህም ምክንያት ድርጅቱ ከአመት ዓመት በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ትርፋማ እየተባለ ይነገራል። የድርጅቱ ሰራተኞች ደሞዝ ለምሳሌ በኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ በአውሮፓም የማይታለም ነው። እስከ አንድ መቶ ሺህ ብር 100 000 ብርና ከዛ በላይ የሚከፈላቸው ሰራተኞች አሉ። የሚያሳዝነው ነገር ይህ ድርጅት አሁን ተላልፎ ለቻይና ለመሸጥ ዝግጅቱ አልቋል። ያ ማለት የቻይና ኩባንያ በብቸኝነት የኢትዮጵያን ህዝብ እየቀረጠ እንዲኖር ሙሉ ፈቃድ ይሰጠዋል ማለት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ በንዲህ ዓይነት ሁኔታ መብቱ እየተሸጠ ነው። ይህንን ለማድረግ እንደተለመደው ቻይና ከፍተኛ የሆነ ጉቦ ለተወሰኑ ባለስልጣኖች እንደከፈለች ምንም ጥርጥር የለውም። ስለዚህ በቁማችን ከነልጅ ልጆቻችን ተሸጠን ከማለቅ የብኩላችንን ጩኸት ጩሁ ለማለት ተስፋ በመቁረጥ የጻፍነው ነው።

ከዳላስ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ውይይት መድረክ የቀረበ ጥሬ

ይድረስ ለመላው ዲያስፖራ ባላችሁበት፤ በአሜሪካ፤ በአውሮፓ፤ በአውስትራሊያ፤ በኤሽያ፤          ባፍሪካና፤ በመካከለኛው ምስራቅ የምትገኙ በሙሉ። እንኩዋን ለኢትዮጵያ ገና በአልና ለፈረንጆቹ አዲስ ዓመት አደረሳችሁ በማለት እኛ በዳላስ የምንገኝ የዳላስ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ውይይት መድረክ ( Forum ) ልባዊ ሰላምታችንን እናቀርባልን።
ይህ የዳላስ መወያያ መድረክ ( Forum ) አጠር ያለ መለክት ይዘንላችሁ ስንቀርብ በጥሞና እንድታዳምጡን በትህትና ከወዲሁ እንጠይቃለን። ወገኖች ሁላችሁም እንደምታውቁት ዛሬ አገራችን በመንታ መንገድ ላይ እንደምትገኝ ለናንተ መንገሩ አስፈላጊ አይመስለንም፤ የወያኔ ዘረኛው የወንበዴ ቡድን አገዛዝ የሕዝባችንን ሰቆቃ እያጠነከረ በግፍ ያለምንም ርህራሄ በተለያየ ወጣቱን ትውልድ እያሳደደ በማሰር፤ በመግደልና ለስደት በመዳረግ ላይ ይገኛል፤ ሕዝባዊ እንቢተኝነቱም የዚያኑ ያህል ተጠናክሮ ይህን የዘረኛ ቡድን መተንፈሻ እንዳሳጣው የማይካድ ሓቅ ነው። በተለያዩ አካባቢዎች ጀግና የኢትዮጵያ ልጆች በጎበዝ አለቃቸው እየተመሩ በአማራው ክልል የወያኔን ቡችሎች መውጫ መግቢያ እያሳጡዋቸው ነው። በውጭውም አለም ያለው ዲያስፖራም በተለያየ መልኩ፤ ሰላማዌ ሰልፍ በመውጣት ዲፕሎማሳዌ ውጥረቶችን በመፍጠርና ፒትሽን በማስፈርም ለተባበሩት መንግስትና ለሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችና ለተመሳሰሉ ድርጅቶች አቤቱታውን በማሰማት የወያኔን መንግስት እይተፋለም ነው።
ወያኔ ዛሬ አንድ ሐሙስ የቀረው የውንበዴ ጥርቅም በመሆኑ  የዚህን ዘረኛ መንግስት እድሜና ትንፋሽ ለማሳጠር ሁሉም በአንድነት ቆሞ በሁሉም ዓይነት ሁለገብ ትግል በማድረግ እድሜውን ማሳጠር ግድ ይላል።
ይህንኑ መሰርት በማድረግ የዳላስ ኢትዮጵያውያን የውይይት መድረክ ተወያይቶ የደረስበት ውሳኔ የዲያስፖራው ሕብረተሰብ ይጠቀምበታል ብለን ስለአሰብን ይህንን ቀላልና ለአንድ ጊዜ ብቻ ( ካስፈለገም ይቀጥላል ) በመጠቀም ወያኔ የሚስገበግበትን የውጭ ምንዛሬ ለአንድ ወር በማስቀረት ዋለቱ እንዲሳሳ ለማድረግ ያቅድነውን ዘመቻ እንድትካፈሉ እንጠይቃለን። ወገኖች ትግሉን በሁሉ አቅጣጫ ማጋጋል ስለሆነና የትግል ትንሽ ስለሌለ በንቀት የማይታለፍም ስለማይሆን ባለን አቅም ሁሉ ጠጠር በመወርወር ወያኔን ማቁሰል መቻል አለብን ይሄን መተግበሩ ደግሞ ማንኛውም ኢትዮጵያንና ወገኑን የሚወድ ኢትዮጵያዌ ግዴታ ነው።
እስከዛሬ ተሞከሮ አያውቅም ባንልም ትኩረት ያልትሰጠበትና በተግባር ላይ ያልዋለ የትግል ስልት እንደቀላል የተወስደ ቢኖር አንዱ የወያኔን የውጭ ምንዛሬ ማዳከም ነው፤ ወያኔ በየዓመቱ ከዲያስፖራው ብቻ ከአንድ ቢሊዬን ዶላር በላይ ( Billion ) እንደሚያገኝ የታወቀ ነው። ለዚህ መፍቴ ይሆናል ብለን የገመትነው ደግሞ በዚህ በአመት በዓል ወቅት እያንዳንዱ ዲያስፖራ ለዘመዶቹ የሚሆን ገንዘብ እንድምንልክ የታወቀ ሲሆን ይህም ገንዘብ በዶላር ተመንዝሮ ወያኔ ኪስ ይገብባል። በተጨማሪም የወገኖቻችን መግደያና የዘር ማጥፊይ መሳሪያ ታንክና ጥይት መግዣ ላይ ያውሉታል ይህ እየታወቀ ሰራችንን ባለመስራታችን ወያኔዎቹ ከጥይት መግዣ የተረፋቸውን ተከፋፍለው የኢትዮጵያ ሕዝብ በረሃብ ሲያልቅ እነሱ ግን በየአውሮፓው መንደላቀቂያ አድርገውታል።
ታዲይ እንደዚህም ሰንል በዚያች ደሃ አገር የሚኖሩትን ወግኖቻችንን ችግርና ረሃብ ረስተን ሳይሆን ድር ቢያብር አንበሳ ያሰር እንደሚባለው ሁሉ ለሁልጊዚ ሳይሆን ለአንድ ጊዜ ለአንድ ወር ብቻ ብናቆም ወያኔን በትንሹም ቢሆን ማቁሰሉ አይቀሬ ነው። ሌላው መታወስ ያለበት ጨርሶም አትላኩ ማለታችንም ሳይሆን በዌስተር ዩኒየን፤ መኒ ግራም፤ ባንክ ድራፍት ( western union, money gram, bank draft ) በመሳሰሉት አትላኩ ማለታችን ነው፤ ምክንያቱም ይህ ገንዘብ በቀጥታ ወያኔ ባንክ ወስጥ ገቢ ስለሚሆን ነው። በሌላ መንገድ ግን በማንኛውም ማድረስ ትችላላችሁ።
ስለዚህ የዳላስ ኢትዮጵያውያን መወያያ መድረክ ፎረም ይህንን ሃሳባችንን የአመቱ መጫረሻ የሚቀጥለው አመት መቀበያ ሪዞሉሽን ( Resolution ) እንድታደርጉልን በትህትና እንጠይቃልን   
በድጋሜ ይህ ጉዳይ በአገር ቤት ወስጥ በየአቅጣጫው ከወያኔ ጋር ለሚዋደቁ ጀግና የጎበዝ አልቆችና በጦር ግንባር የሚፋለሙ አርበኞቻችንን በምንም አይነት መልኩ አይምለከትም ለነሱ ከዚህ በፊት በሚደረገው መንገድ ሁሉ እንዲቀጥል አደራ እንላለን
ድል ለ ኢትዮጵያ ሕዝብ ሞት ለ ወያኔ

Wednesday, December 28, 2016

በቤኒሻንጉል ጭላንቆና ባኩጂ ቀበሌዎች የአማሮች አበሳ ቀጥሏል | እየታሰሩ እየተገረፉ ነው

(ዘ-ሐበሻ) ሕዝብን ከሕዝብ ጋር በማናከስ ተወዳዳሪነት የሌለው የሕወሓት መንግስት በቤንሻንጉል ሕዝብ በማስመሰል በአማራው ላይ የሚፈጽመውን ጥቃት አጠናክሮ ቀጥሏል:: በተለይ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በቡለን ወረዳ ስር ባሉት ጭላንቆ እና ባኩጂ ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖሩ አማሮች በስርዓቱ ጠመንጃ ታሸጋግራላችሁ; በአማራው ክልል እየተደረጉ ያሉትን ጦርነቶች ትደግፋላችሁ በሚል ግርፋት እና እስር እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተዘግቧል::
በጭላንቆና ባኩጂ ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖሩት እነዚሁ አማሮች አርሶ ከመብላትና በሰላም ከመኖር ውጭ ምንም የማያውቁ ሆኖ ሳለ ሆን ተብሎ ከመሬታቸው ለማፈናቀልና ተረጋግተው እንዳይኖሩ ለማድረግ ሆን ተብሎ የሕወሃት መንግስት ባሰማራቸው የቤንሻንጉል ተወላጆች እንዲገረፉ ንብረታቸውም እንዲዘረፍ በማድረግ ላይ ነው::
በትናንትናው ዕለትና በዛሬው ዕለት ብቻ ቁጥራቸው ከ25 የሚበልጥ አማራ ናችሁ የተባሉ ወጣቶች ታስረው ወዴት እንደተወሰዱ አይታወቅም የሚሉት የዜና ምንጫችን ንብረት ዘረፋውም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል::
በዚሁ በቤኒሻንጉል ክልል የሚኖሩ አማሮች ላይ ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው ሁሉ ወደ መጣችሁበት ሂዱ በሚል ጥቃት እየደረሰባቸው መሆኑን ዘ-ሐበሻ ሰሞኑን በተደጋጋሚ መዘገቧ አይዘነጋም::
በሌላ ዜና የአማራው ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በቻግኒ ከቤንሻንጉል ባለስልጣናት ጋር ስብሰባ ላይ እንደዋለና በስብሰባው ውስጥም የሕወሓት ሰዎች ሙሉ በሙሉ ተሳትፎ እንደነበራቸው የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል:: የዚህ ስብሰባ ዓላማ ሰሞኑን በጃዊ ሕዝብ ያነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ በክልሉ ይኖራል ተብሎ በተሰጋው የመሳሪያ ዝውውር ዙሪያ እንደሆነ ምንጮች አስታውቀዋል:: በቻግኒ ኢትዮጵያ ሆቴል በተደረገው በዚሁ ስብሰባ ላይ የቤንሻንጉል አስተዳደሮች በክልላቸው የመሳሪያ ዝውውር እንዳይኖር ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ከሕወሃት ሰዎች ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው የሚገልጹት ምንጮቹ በተለይም በክልሉ የሚኖሩ አማሮች ሕዝባዊ ዓመጹን እንዳይቀላቀሉት ጥብቅ ክትትል እንዲደረግባቸው ተመክሮባቸዋል::

በእነ ጉርሜሳ አያኖና በቀለ ገርባ መዝገብ በአንደኛ ክስ ላይ የቀረበ ምስክር ተሰማ | ምስክሮች በተከሳሾች ላይ ሳይሆን በክሱ ላይ ምስክርነት ሰጥተዋል (የፍርድ ቤት ውሎ ዘገባ)

በእነ ጉርሜሳ አያኖ መዝገብ በአንደኛ ክስ ላይ የቀረበ ምስክር ተሰማ
ምስክሮች በተከሳሾች ላይ ሳይሆን በክሱ ላይ ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡ 
በነጉርሜሳ አያኖ ( በቀለ ገርባ) መዝገብ ከአንድ ወር በፊት የአቃቢ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ቀጠሮ ተይዞ በነበረ ሲሆን የሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ሊመጡ ያልቻሉ የአቃቢ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ለታህሳስ 18 መቀጠሩ ይታወሳል፡፡ በጠዋቱ ችሎት ምስክሮቹ በመንገድ ላይ እንደሆኑ እና ምስክሮቹ ከሰአት እንዲሰሙ አቃቢ ህጉ በመጠየቁ የምስክር ማሰማቱ ሂደት ለከሰአት ተዘዋውሮአል፡፡ የጠዋቱ ችሎት ከማለቁ በፊት የተከሳሽ ጠበቃ አቶ ወንድሙ ተከሳሾች ከቤተሰብ የሚቀርብላቸውን ምሳ እንዲበሉ እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡ ዳኞችም ተከሳሾች በሚውሉበት ቀን ከቤተሰብ የሚቀርብላቸውን ምሳ እንዲበሉ በተደጋጋሚ ውሳኔ እንዳስተላለፉ አስታውሰው፡ ከማረሚያ ቤቱ ለመጡ ሃላፊዎች ምግብ ማግኘት መብት መሆኑን በመጥቀስ ለተከሳሾች ቤተሰብ የሚያቀርብላቸውን ምሳ በችሎት ውስጥ እንዲመገቡ በሃላፊነት እንዲያስፈፅሙ ነግረዋቸዋል፡፡
በከሰአቱ ችሎት አቃቤህግ ዘጠኝ ምስክሮች እንደቀረቡ ገልፆ በቅድሚያ በአንደኛ ክስ ላይ የሚመሰክሩለትን ሁለት ምስክሮች እንደሚያሰማ ተናግሮ የሚመሰክሩበትን ጭብጥ አስመዝግቧል፡፡
ሁለቱ ምስክሮች በመንግስት የሃላፊነት ቦታ ላይ የሚሰሩ ሲሆን በአቡነ ግንደበረት ወረዳ በኬ ቀላጤ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች/ከተማዎች በ2008 ዓም ስለተነሳው ረብሻ እና የተከሰቱት ሁኔታዎችን በአጠቃላይ እንደሚያስረዱ እንዲሁም የሁከቱ እና የብጥብጡ ተሳታፊዎች ውስጥ የኦፌኮ አባላት እንዳሉበት የኦፊኮ አባላት ፓርቲያቸውን እንደሽፋን በመጠቀም የኦነግን ተልእኮ ለማስፈፀም እንደሚንቀሳቀሱ የደረሳቸውን መረጃ በተመለከተ ያስረዱልኛል በማለት ጭብጡን አስይዟል፡፡
የተከሳሽ ጠበቆች አቃቤ ህግ ያቀረበው ጭብጥ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ አቅርበዋል፡፡ አቃቤ ህግ ያስመዘገበው ጭብጥ ጠቅለል/ሰፋ ያለ በመሆኑ ምስክሮቹ በማን ወይም በስንተኛ ተከሳሽ ላይ የቀረቡ መሆናቸውን እና የትኛውን ድርጊት ሲፈፅሙ የተመለከቱ እንደሆነ ዘርዘር ተደርጎ ጭብጡ እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል-የተከሳሽ ጠበቆች፡፡ ዳኞችም ተመካክረው የተከሳሾችን ሃሳብ ተቀብለው አቃቤ ህግ ጭብጡን ዘርዘር አድርጎ እንዲያቀርብ እንዲሁም ምስክሮች በስንተኛ ተከሳሽ ላይ የሚመሰክሩ መሆናቸውን በጭብጡ እንዲጠቅስ ውሳኔ ሰጥተው የነበረ ቢሆንም አቃቤ ህግ በበኩሉ ምስክሮች በየትኛው ተከሳሽ ላይ እንደሚመሰክሩ የመግለፅ ግዴታ እንደሌለበትና ያቀረበውን ክስ ያስረዱልኛል ብሎ ካመነ ማሰማት እንደሚችል ገልፇ፡ ከላይ የጠቀሰውን ጭብጥ ከ1-13ኛ የተጠቀሱ ተከሳሾች ላይ የቀረበውን 1ኛ ክስ ላይ የተገለፁ ድርጊቶችን የሚያስረዱ ምስክሮች እንደሆኑ ከዚህ በላይ ዘርዘር አድርጎ ማቅረብ እንደማይችል አስረድቷል፡፡ ዳኞችም የአቃቤ ህግ ግዴታ ክሱን ያስረዱልኛል ያላቸውን ምስክሮች ማሰማት እንጂ ጭብጥ ማስያዝ ግዴታ እንደሌለበት፤ ጭብጥ ማስያዝ በፍርድቤቶች በተለምዶ ሲሰራበት የመጣ አሰራር እንጂ ህግ ባለመሆኑ አቃቤህግ አንደኛ ክስን ያስረዱልኛል ያላቸውን ምስክሮች የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ወስነዋል፡፡

በአንደኛው ክስ ላይ የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡት የመጀመሪያው ምስክር ኢንስፔክተር ደበሎ አበበ ይባላሉ፡፡ በ2008 ዓም የፓሊስ አዛዥ ሆነው ግንደበረት ወረዳ ይሰሩ እንደነበሩ የገለፁት ምስክሩ፤ በአዲስ አበባ ልዩ ዞን ፊንፊኔ ዙሪያ ማስተር ፕላንን እና የጭልሞ ጫካ ተጨፍጭፎ መሸጡን በመቃወም ሰበብ የግንደበረት አጎራባች ወረዳ በሆነችው ደንዲ ወረዳ ጊንጪ ከተማ ህዳር 30 ቀን 2008ዓም ረብሻ እና ሁከት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ በጊንጪ ከተማ የተከሰተው ረብሻም ወደ እንሱ ወረዳ ይመጣል ብለው ሰግተው ስለነበር መረጃ የማሰባሰብ ስራ ይሰሩ እንደነበር ገልፀዋል፡፡ ከታህሳስ 1-4/2008 በግንደበረት ወረዳ በኬ ቀላጤ ከተማ ሁከት እና ብጥብጥ ተነስቶ “ ወያኔ አይገዛንም”፣ “ኦነግ ነው የሚገዛን”፣ “ኦሮሚያን ነፃ እናወጣለን”፤ “ይሄ መንግስት አየገዛንም” የሚሉ መፈክሮች እንዲሁም ዘፈኖች ይሰሙ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ የሁከቱ ተሳታፊዎች ፓሊስን እና መንግስትን ይቃወሙ እንደነበር እንዲሁም እጅና እጅን በማጣመር ምልክት ያሳዩ እንደነበር ገልፀው በነዚህ ቀናት ውስጥ መሳሪያ ይተኮስ እና ቦንብ ይወረወር እንደነበረ፣ ድንጋይ ይወረወር እንደነበረ፣ የወረዳ አስተዳደር ቢሮዎች፣ ፍ/ቤቶች፣ መኖሪያ ቤቶች እና መኪና እንደተቃጠሉ ፣ንብረቶች እንደተዘረፉ፣ 3ት ፓሊሶች እና 3 ሲቪሎች እንደተገደሉ አስረድተዋል፡፡
በረብሻው ከተሳተፉት ውስጥ የተወሰኑት በፍተሻ ወቅት የኦብኮ መታወቂያ በኪሳቸው እንደተገኘ እንዳሉ የገለፁ ሲሆን አብዛኛዎቹ በምርጫ 2007 ወቅት የተቃዋሚ ፓርቲን ሲደግፉ የነበሩ መሆናቸውን እንደሚያስታውሱ እንዲሁም አንዳንድ ተቃዋሚዎች እና ፀረሰላም ሃይሎች እየተደራጁ ወጣቱን እና ህብረተሰቡን እንደሚያነሳሱ ከፀጥታ ሃይሎች መረጃ እንደሚደርሳቸው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ምን አይነት መረጃ እና መረጃውን ከማን እደሚያገኙት በተከሳሽ ጠበቆች ለቀረበላቸው ጥያቄ ሳይመልሱ ቀርተዋል፡፡ የኦብኮ መታወቂያ ከተያዘባቸው ውስጥ የሚዯስታውሱት ስም ካለ ተብለው ሲጠየቁ የሚያስታውሱት ስም እንደሌለ የተናገሩ ሲሆን የኦብኮ መታወቂያ ቢጫ ከለር እንደሆነ እና በወረዳው የሚገኝ ሃላፊ ቲተር እና የፓርቲው ማህተም እንዳለበት አስረድተዋል፡፡
ምስክሩ በመዝገቡ ተካተው በችሎት ከነበሩት 22 ተከሳሾች በግንደበረት ተከስቶ ነበር ባሉት ሁከት እና ብጥብጥ ሲሳተፉ አይተዋቸው ከሆነ ተብለው በተደጋጋሚ ሲጠየቁ ተከሳሾቹን ማናቸውንም እንደማያቋቸው የገለፁ ሲሆን በወቅቱ በረብሻው የተሳተፉ እና ንብረት ያወደሙትን ግለሰቦችን ጉዳይ ይመረምሩ ስለነበር፡ ጉዳዩ ተጣርቶም እዛው በወረዳቸው ፋይል የተከፈተባቸው በመሆኑ ቢያዩአቸው በቀላሉ መለየት ይችሉ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
የመጀመሪያው መስካሪ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው ሲጨርሱ ሁለተኛውን ለመስማት ጊዜ ባለመኖሩ ምክንያት ነገ ጠዋት እንዲመሰክሩ ቀጠሮ ተይዟል፡፡
የትላንትናው የታህሳስ 18/2009 ችሎት መቅረፀ ድምፁ በመበላሸቱ ምክንያት እስከዛሬ 4ኛ ችሎት ይሰይምበት ከነበረው በተለምዶ አዳራሽ ከሚባለው እና ብዙ ታዳሚ ከሚይዘው ችሎት ተነስቶ ጠባብ ክፍል እና ጥቂት ታዳሚዎችን መያዝ የሚችል ችሎት ውስጥ ተሰይሟል፡፡ በርከት ያሉ የተከሳሽ ቤተሰቦች እና ችሎቱን ለመታደም መጥተው የነበሩም ቦታ ባለመብቃቱ ምክንያት ችሎት ሳይታደሙ ቀርተዋል፡፡ ችሎቱ ከማለቁ በፊትም የኦፊኮ ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ በችሎቱ መለወጥ ላይ ያላቸውን አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡ መቅረፀ ድምፁ ተበላሽቶ ነው የሚለውን ምክንያት እንደ ሰበብ እንጂ ትክክለኛ ምክንያት ነው ብሎ እንደማያምኑ ገልፀው፣ በቀጣይ ቀናት 4ኛ ችሎት ይሰየምበት በነበረው ችሎት ተሰይሞ ችሎቱን መከታተል የሚፈልጉት ታዳሚዎች ሁሉ መስተናገድ እንዲችሉ አቶ በቀለ ገርባ አቤቱታቸውን ለችሎት አሰምተዋል፡፡
ዳኞችም በፊት ይሰየሙበት የነበረው ችሎት መቅረፀ ድምፅ ስለተበላሸ እንጂ ሌላ ምንም ምክንያት እንደሌላቸው በነገው እለት ተስተካክሎ ቀድሞ ይሰየሙበት ወደነበረው ችሎት እንደሚመለሱ አስረድተዋል፡፡
በአንደኛ ክስ ላይ እንዲመሰክሩ የቀረቡ ቀሪ ምስክርን እና ሌሎች የቀረቡ ምስክሮችን ለመስማት ለታህሳስ 19/4/2008 ተቀጥሯል፡፡
የዜናው ምንጭ: የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ፕሮጀክት

በቤኒሻንጉል ቡለን ወረዳ በአማራ ተወላጆች ላይ ግፍና በደል እየተፈጸመ መሆኑ ተገለጸ


ኢሳት (ታህሳስ 18 ፥ 2009)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን ወረዳ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ግፍና በደል እየተፈጸመባቸው መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ።
በአካባቢው የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች እስራትና ድብደባ የሚፈጸምባቸው የጦር መሳሪያ ታዘዋውራላችሁ በሚል መሆኑን ዕማኞች ለኢሳት ተናግረዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ክልል አጎራባች ወረዳዎች በተለይም የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ፕሮጄክቶች ባሉበት አካባቢ የተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ ለስርዓቱ ስጋት መሆኑን ይነገራል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች በአካባቢው የመንግስት ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ግፍና በደል ሲደርስባቸው ቆይቷል። በዚሁም ሳቢያ በርካታ ህጻናት ሴቶችና አባወራ የአማራ ተወላጆች እስከመፈናቀል ደርሰዋል። በተለይም ከ2005 ጀምሮ እየደረሰባቸው ያለው እስራትና ድብደባ እንዲሁም መፈናቀል የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) የሚመራው የአማራ ክልል ምንም አይነት ድጋፍም ሆነ የተቃውሞ ድምጽ አላሰማም። ይልቁንም፣ የክልሉ አመራር በቅርቡ ከተከሰተው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ከህወሃት ጋር ቁርኝት ያላቸው ጥቂት የትግራይ ተወላጆች ጉዳት ደርሶባቸዋል በሚል ይቅርታ የጠየቁበት ሁኔታ መኖሩ ነው የሚታወቀው። ለእነዚሁ የትግራይ ተወላጆች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉም አይዘነጋም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የአማራ ተወላጆች በተለይም በቡለን ወረዳ አለምበር በቁጅና ጭራንቆ ቀበሌዎች የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ከፍተኛ ስቃይና በደል እየደረሰባቸው መሆኑን ስማቸው እንዳይጠቀስ ያልፈለጉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ሰብላቸውንም እየተቀሙ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንደአካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ፣ ይህንኑ ግፍና በደል የሚፈጽሙ የክልሉ የቀበሌና የወረዳ አመራሮች ታጣቂዎች ናቸው። ትዕዛዙ የሚመጣው ደግሞ ከላይ በክልሉ በኩል ካሉ አመራሮች በኩል መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ይገልጻሉ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በአማራ ክልሎች አጎራባች ወረዳዎች በተለይም በጣና በለስ አካባቢ የስኳር ፕሮጄክቶች ባሉበት አካባቢ ከፍተኛ ውጥረት መኖሩ ይነገራል። በዚያ ስፍራ የነጻነት ሃይሎች ስርዓቱን መታገል መጀመራቸውም ነው የሚነገረው። ይህንኑ ለማስቆም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የአካባቢውን አመራሮች ሰብስበው የአካባቢው ጸጥታ ቁጥጥር እንዲደረግበት ጥብቅ መመሪያ ማስተላለፋቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በጣና በለስ ዙሪያ ስኳር ፋብሪካ ለመገንባት በሚል በህወሃት ጄኔራሎች የሚመራው የብረታብረትና ኢንጂነሪን ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) የልማት አካባቢውን ተቆጣጥሮት ይገኛል። በርካታ ወጣቶችን ከትግራይ ክልል በማስወጣት አሰማርቶ የሚገኘው ሜቴክ በጃዊና አካባቢ የተፈናቀሉ አርሶ አደሮችና ነዋሪዎች ተቃውሞ እያሰሙ በመሆናቸው አካባቢው ውጥረት ውስጥ ይገኛል። በአካባቢው የነጻነት ሃይሎች ጥቃት መሰንዘር በመጀመራቸው ሁለት ታንኮች ገብተው እንዱ መቃጠሉን በቅርቡ ዕማኞች ለኢሳት መናገራቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ የኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተዋል።

Minilik Salsawi sitt bilde.አገር የጋራ ነው።ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ የኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተዋል። የተለየ ወይንም ብቻውን የተቀደሰ ኢትዮጵያዊ የሚባል ነገር የለም። ኢትዮጵያዊ ሁሉም እኩል ነው። ማንም ከማንም በዜግነት አያንስም አይበልጥም። ግለሰቦችን ይሁን ድርጅቶች ራሳቸውን ልዩ ኢትዮጵያዊ ልዩ አገር አስተዳዳሪ፣ ልዩ የነጻነትና የመብት ታጋይ ልዩ አገልጋይ አድርገው የሚያስቡትን ነገር ማቆም ካልቻሉ በልፋት ላይ ትልቅ አደጋ አለው። እኛን ብቻ ስሙን። እኛን ብቻ እዩ። እኛን ብቻ አንብቡ።እኛ እንድምንልው ሁኑ። ለሃገር ሐሳቢ ሃገር ወዳድ እኛ ብቻ ነን ከኛ በላይ ላሳር እየተባለ ሌላውን ለማግለልና ለማንኳሰስ የሚደረገው ሩጫም ሌላው አደጋ ነው። ኢትዮጵያዊነትን ራሳቸው እንደሚያድሉት የእርዳታ እቃ አድርገው የሚያስቡ አደገኛ ቡድኖችንና ጀሌዎቻቸውን አገር የጋራ መሆኑን አስረግጠን ልንነግራቸው ይገባል። አገር የጋራ ነው። ወያኔ የሕዝብ ጠላት ነው። #MinilikSalsawi

900 ሚሊዮን ብር የወጣባቸው የቢሾፍቱ የከተማ አውቶቡሶች “እየታረዱ” ነው

ዋዜማ ራዲዮ- የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በግዳጅ ለአንበሳ አውቶብስ ከሸጣቸው 550 አውቶቡሶች ዉስጥ ግማሽ የሚኾኑት ከጥቅም ዉጭ ኾነው እየተጣሉ ነው፡፡ አንዳንዶቹም “ታርደው” የተወሰነ እቃቸው በሥራ ላይ ላሉ ቀሪ አውቶቡሶች መለዋወጫ እንዲውል እየተደረገ ነው፡፡
ከ20 ዓመታት በላይ በድርጅቱ ዉስጥ በሾፌርነት እንዳገለገሉ የተናገሩ አንጋፋ ሾፌር ለዋዜማ እንደተናገሩት ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ የሚገጣጥማቸው እነዚህ ከባድ አውቶብሶች ለ20 ዓመታት ያለምንም የጎላ ችግር አገልግሎት ይሰጣሉ ተብለው እንደተገዙ ይናገራሉ፡፡ ኾኖም ስድስት ወራት እንኳ አገልግሎት ሳይሰጡ ሞተራቸው እንዲወርድ የተደረጉ እንዳሉ እንደሚያውቁ ይናገራሉ፡፡
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ብቻ 143 አውቶብሶች ከጥቅም ዉጭ ኾነው ቆመዋል፡፡ አንዳንዶቹ በመለዋወጫ እጦት ነው የቆሙት ቢባልም ይህ እውነት እንዳልሆነ እኚሁ ሾፌር ይከራከራሉ፡፡ በርካታ ጊዜያት መለዋወጫ ነው እየተባለ ሪፖርት ይደረጋል፡፡ ብዙ ሚሊዮን ብር እየወጣ መለዋወጫ ከቻይናም ከቢሾፍቱም ተገዝቶ ያውቃል፡፡ የመለዋወጫ ጨረታ የማይወጣበት ወር አላስታውስም፤ ነገር ግን አውቶቡሶቹ ከእድሳት በኋላ ለጥቂት ወራት ብቻ አገልግሎት ሰጥተው በድጋሚ ይበላሻሉ፡፡ አንድ አውቶብስ ከተገዛበት ዋጋ በላይ ለመለዋወጫ እንደሚወጣለት ሁላችንም የድርጅቱ ሠራተኞች እናውቃለን ብለዋል፡፡ “በአገር ሀብት ለምን ይቀለዳል ብለን በድርጅቱ ለረዥም ዘመን ያገለገልን ሠራተኞች ተፈራርመን የቅሬታ ደብዳቤ ብናስገባም ምላሽ አላገኘንም” ይላሉ እኚህ ሾፌር ከፍ ባለ ሐዘኔታ፡፡
ከአምስት ዓመት በፊት ከመከላከያ ኢንጂነሪንግ 550 አውቶቡሶች በግዳጅ ግዢ ሲፈፀም መስተዳደሩ 900 ሚሊዮን ብር ወጪ እንዲያደርግ ተገዶ ነበር፡፡ ከ550ዎቹ የመከላከያ አውቶቡሶች ዉስጥ 100 የሚኾኑት ተጣጣፊ (አርቲኪዩሌትድ ባስ) እንደነበሩ ይታወሳል፡፡
እነዚህ ባለ ሁለት ተሳቢ አውቶብሶች በዚህ ከተማ መንገድ ለመንዳት አስቸጋሪ እንደሆኑ የተነገረ ሲሆን ሻተራቸው ወዲያዉኑ ስለሚተረተር፣ ወለላቸውም በቀላሉ ስለሚቀዳደድ ከ6 ወር በላይ አገልግሎት አይሰጡም፡፡ የአዲስ አበባ መስተዳደር የትራንስፖርት ችግርን በአጭር ጊዜ ለመቅረፍ ይረዳሉ ያላቸውን አውቶብሶች በ900 ሚሊየን ብር ወጪ ግዢ የፈጸመው ከአምስት ዓመት በፊት ነበር፡፡ በግዢው ሰነድ ላይ አውቶብሶቹ ከ15 እስከ 20 ዓመታት ምንም አይነት የጎላ ችግር ሳያጋጥማቸው በአስተማማኝነት አገልግሎት እንደሚሰጡ ሰፍሯል፡፡ ኾኖም ብዙዎቹ አሁን ላይ ከጥቅም ዉጭ ኾነው በአምቼ ጋራዥ ቆመዋል፡፡ አንዳንዶቹም አገልግሎት ለሚሰጡ ባሶች እቃቸውን “እየታረደ” እየተሰጠ ነው፡፡ ይህም ድርጅቱንም ለከፍተኛ ወጪ ዳርጎታል፡፡
አዲስ ዘመን ጋዜጣ በቅርቡ የከተማ አውቶቡስ ሥራ አስኪያጅንና የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የግዥና ሽያጭ ኃላፊን ጠቅሶ በሰራው ዘገባ ተበላሽተው ከጥቅም ዉጭ የኾኑ አውቶብሶች ቁጥር 195 ብቻ እንደሆነ ጠቅሷል፡፡ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ የግዥና ሽያጭ ኃላፊው ችግሩ ከአንበሳ አውቶቡስ ድርጅት አጠቃቀም የመነጨ ነው ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ የአንበሳ አውቶቡስ ሥራ አስኪያጅ አቶ አለምነው ጌትነት በበኩላቸው በኃላፊው ምላሽ የተበሳጩ ይመስላሉ፡፡ “ከአጠቃቀም አንጻር አገልግሎት ፈላጊው ብዙ ነው፤ ነገር ግን አውቶብሶቹ የጥራት ችግር እንዳለባቸው መካድ አይገባም፤ የጥራት ችግር ባይርባቸው ኖሮማ እንዴት ከ15 እስከ 20 ዓመት ሊያገለግሉ የተሠሩ አውቶቡሶች በአራት ዓመት ዉስጥ ይህን ያህል ይበላሻል?” ሲሉ በድፍረት ጠይቀዋል፡፡
ለዋዜማ አስተያየታቸውን የሰጡ አንጋፋ ሾፌር እንደሚናገሩት በሩብ አመት ብቻ 72 ሚሊዮን ብር ወጥቶ መለዋወጫ ግዢ እንደተፈጸመ እንደሚያውቁ ገልጠው ኾኖም በዚህ ሁኔታ ወደ ሥራ የተመለሱ አውቶብሶች ከ5 አይበልጡም ይላሉ፡፡ እነሱም ቢኾን በወራት ዉስጠ ተመልሰው እንደሚቆሙ ምንም ጥርጥር የለኝም ይላሉ፡፡ ” እንደኢህአዴግ መንግሥት ለአገር ሐብት ደንታ የሌለው አላየሁም” ሲሉም ቁጭት ያክሉበታል፡፡
ባለፉት ዓመታት በአንበሳ አውቶቡስ ሠራተኞች መካከል በተደረገ የመልካም አስተዳደር ጉባኤ ስለነዚህ አውቶቡሶች የጥራት መጓደል ከፍተኛ ትችት ከተራ ሠራተኞች ጭምር የቀረበ ሲኾን ኃላፊዎች በበኩላቸው ይሄ የምታነሱት ጉዳይ ከኛ አቅም በላይ ነው የሚል መልስ በደፈናው ሰጥተው አልፈዋል፡፡
እኔ እድሜ ዘመኔን ሙሉ የነደኋቸው የዳፍ አውቶብሶች የጎላ ችግር ሳይገጥማቸው ከ10 ዓመት በላይ አገልግለዋል፡፡ እንዴት ጥራቱ ያልተፈተሸ አውቶቡስ ሲገዛ መንግሥት ዝም ብሎ ያያል የሚሉት እኚህ ሾፌር በጓደኞቻቸው የሚነዱ አዳዲስ የተባሉ ቢሾፍቱዎች ብዙዎቹ የፍሬን ችግር ስላለባቸው ተደጋጋሚ በሰውና በንብረት ላይ አደጋ ማድረሳቸውን እንደሚያውቁ አስረድተዋል፡፡ ብዙ ሾፌር ቢሾፍቱ ሲሰጠው አልነዳም እንደሚልና የደመወዝ ቅጣት ስለሚጣልበት ብቻ ለመንዳት እንደሚገደድ እኚህ ሾፌር ያብራራሉ፡፡
በከተማዋ 1000 የሚጠጉ ቢጫ ታክሲዎች፣ አንድ መቶ አሊያንስ አውቶብሶች በቅርብ ወራት ዉስጥ ከቀረጥ ነጻ የገቡ ሲኾን በቀጣዮቹ አመታት አራት መቶ የአሊያንስ አውቶብሶች ወደ አገሪቱ ለማስገባት እየተሞከረ እንደሆነ በመገናኛ ብዙኃን ተነግሯል፡፡ ከዚህ ባሻገር ቁጥራቸው ከ10ሺ በላይ የሚኾኑ ሰማያዊ ሚኒባሶችን በማኅበራት በማደራጀት አዳዲስ አውቶቡሶችን ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡና የሚኒባስ አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ እንዲቀር ለማድረግ እየተሠራ ይገኛል፡፡
አንበሳ አውቶቡስ ከ73 ዓመታት በፊት የንጉሣዊ ቤተሰብ ንብረት ኾኖ የተቋቋመ ሲኾን በወቅቱ በ5 የወታደር አውቶብሶች በአምስት መስመሮች ሥራ እንደጀመረ ይነገራል፡፡ ከተቋቋመ ከ10 ዓመት በኋላም ድርጅቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፣ በንጉሣዊ ቤተሰብ፣ በመንግሥትና በታዋቂ ነጋዴዎች ሽርክና ተፈጥሮ በአክሲዮን ባለቤትነት ጅማ ከተማን ጨምሮ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የአንበሳ አውቶቡስ በግዳጅ ከመከላከያ የተገዙ በጥራታቸው ደካማ የኾኑ 550 አውቶብሶችን ጨምሮ 880 የሚኾኑ አውቶብሶች አሉት፡፡ ድርጅቱ በወር አንድ ሚሊዮን ብር ድጎማ እየተደረገለት እስከዛሬም ወደ ትርፍ አልተሸጋገረም፡፡ በዓመት በትንሹ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራን ያስመዘግባል፡፡  ዋንኛው የኪሳራ ምንጭ ኾኖ የቆየውም የአውቶቡሶች ተደጋጋሚ ብልሽት እንደሆነ ይነገራል፡፡

የውጭ ምንዛሪ ማዕቀብ እንዲደረግ ለትውልደ-ኢትዮጵያውያኑ ጥሪ ቀረበ

በውጭ ሃገር ያሉ የኢትዮጵያ የሲቪክና የፖለቲካ ድርጅቶች ለ3 ተከታታይ ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሃገር የመላክ ማዕቀብ ጥሪን አስተላለፉ።
17 የሚሆኑት የሲቪልና የፖለቲካ ድርጅቶች ኢትዮጵያውያን ለንግድም ይሁን ለቤተሰብ ድግማ የሚልኩት የውጭ ምንዛሪ እንዳይላክ ማድረግ በሃገሪቱ ያለውን አምባገነን አገዛዝ ለማድከም ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ መግለጫው አመልክተዋል።
ድርጅቶቹ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ምንዛሪው መላካቸውን ለ3 ወራት ካቆሙ በኋም ቢያንስ ለቀጣይ 6 ወራት ደግሞ የሚፈለገውን ገንዘብ አንድ ሶስተኛ እንዲቀንሱ ማድረግ በኢትዮጵያ ያለውን አገዛዝ ለማድከም ይረዳል ብለዋል።
የማዕቀቡ ጥሪ በተላለለፈበት የጊዜ ገደብ ለንግድም ሆነ ለቤተሰብ መላክ የግድ ከሆነ ለስርዓቱ በማይደርስበት መልኩ ቢሆን ተመራጭነት እንደሚኖረውም መክረዋል።
በውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚላከው የውጭ ምንዛሪ ከውጭ ንግድ ይበልጥ ለስርዓቱ ከፍተኛ ገቢ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታል።
በያዝነው የፈረንጆች አመት ማለትም በ2016 ብቻ በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ ከውጭ የተላከው የውጭ ምንዛሪ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚጠጋ በህወሃት/ኢህአዴግ በሚመራው መንግስት በቅርቡ የወጣው መረጃ ላይ ተገልጿል።

የመሳይ ከበደና የሬኔ ለፎርት ወግ >

የአድዋ ጦርነት፤ የአፍሪቃ ሰብአዌነት፤ ለሰው ልጅ ሕሊናዌነት
[ማሳሰቢያ፡ በዚህ አርዕስት ላይ የምንወያየው የአድዋ ጦርነት ለአፍሪቃዉያን ሰብአዌንትና ለሰው ልጅ ሕሊናዌነት ያደረገዉን መስተዋጽኦ ነው። የአድዋ ጦርነት ወይም የአፂ ሚንልክ ታሪክ እዚህ ሊጻፍ እንደማይቻል ለአንባቢ በቅድሚያ ማሳወቅ ተገቢ ነው።  የአድዋ ጦርነት በውጭ አገር የታሪክ ሊሂቃን በመጠኑ ተጽፏል። ግን ታሪክ በአገሩ ሊቃን ሲጻፍ የተልየ መልክ ይሰጠዋል፤ ይህም ማለት ጸሐፊዉ ከሕብረተሰቡ አካል ስለወጣ ባህሉን፤ ዘየዉን፤ አስተሳሰቡን፤ አመለካከቱን፤  አኗኗሩን፤ በአጠቃላይ ሕሊናዉነቱን በቅጡ ያንጸብርቃል፤ ለምሳሌ እንግሊዝ የአገሩን ታሪክ የውጭ ሰው እንዲነካበት አይፈልግም፤ በዩነበርሲቲም ውስጥ ታሪክ እንዲያጠኑ የሚመለመሉ ተማሪዎች በአጠቃላይ ትምህርታቸው ከፍተኛ ዉጢት ያላቸዉን ተማሪዎች ነው። ከውጭ የመጡ ተማሪዎች የሚነገራቸው የራሳቸዉን ታሪክ እንዲማሩ እንጂ ስለ እንግሊዝ አገር ተምረው የእንግሊዝን ታሪክ እንዲጽፉ አይደረግም።  የእንግሊዝ ታሪክ እነሱ እንደሚሉት  በጣም የተከበረና የተለየ ነው፤ “የታላቁ የእንግሊዝ ታሪክ” ተብሎ በክፍተኛ ደረጃ ይቀመጣል፤ “ታላቋ ብሪታንያ” ትባላለች፤ “ፅሐይ በእንግሊዝ ግዛት አትጠልቅም”” ይላሉ። ይህም ማለት አንድ ሶወስተኛዉን የዓልም ክፍልን በቅኝ ግዛታቸው ስለአደረጉ እንግሊዝ አገር ጀምበር ስትጠልቅ ቅኝ ግዛቷ ላይ ትወጣለች። የሊላዉን አገር ታሪክ በፈለጉት ዓይነት ጽፈው ለቅኝ ተገጆቻቸው ያስተምራሉ፤ ለዚህ ነው “የታሪክ አባቶቻችን” እየተባሉ የሚጠሩት፤ ይህ አይነት አባባል እኛም አገር የተለመደ ነው፤ጥገኝነቱም  የጠበቀ ስለሆነ እነሱ ያሉትና የጻፉት ከአልሆነ  በዚህ አይነት ቢቀርብ  ተቀባይነት አይኖረዉም፤ትልቅ ያለመታደል ነው፤ ለዚህም መረጃ የሚሆነው የሚሰጠው አስተያየት ነው ። እንግዲህ እዚህ ጽሑፍ ላይ የምንመለከተው ምኒልክንና አድዋን በአንድነት አድርገን ነው። ምኒልክ ከአድዋ ተነጥሎ ሲታይ ብዙ በደል እንደሰራና ሕዝብን በኃይል አስገድዶ እንደገዛ “የታሪክ አባቶቻችን” በምንላቸው የተጻፉትን በማየት  “አድዋ የአፍሪቃ ድልና አለኝታ” የሚለዉን እንገድፈዋለን። “የከፋፍለህ ግዛ” የፖለቲካ ስልት ክግንዛቤ ስለአላስገባነው አገር፤ ሰንደቅ ዓላማ፤ አንድነት የሚለዉን ማሰሪያ አንቀጽ ተሰባብሮ እንዳለነበረ ሆኗል፤  ይህንን በተመለከተ በዚህ ጽሑፍ ዉስጥ ያስከተለዉን ጉዳት እንመለከታለን።
ይህንንም “ሁኔታ” የምንመለከተው ከታሪክ ቀንጨብ እያደረግን ነው፤ ለአደዋ ጦርነት ዋና መንስኢ የሆነው በክፍል ሁለት ላይ እነደተጻፈው የ1884-5  አፍሪቃን ለመከፋፈል በተደረገው የበርሊን ጉባኢ ነበር። በዚህ ጉባኢ ላይ ተካፋይ የነበረችው ኢጣልያን በወቅቱ ምንም የቅኝ ግዛት የሊላት አገር ስለነበረችና ግዛቷን በጋሪባልዲ አማካይነት ታላቋን ኢጣልያንን መንግሥት በ1860 ስለአስተባበረች የቅኝ ግዛት ባለቤት መሆን አስፈላጊ ከመሆኑም በላይ ሲሲልና በስተደቡብ የሚገኘዉን ሕዝብ አንድ ስላደረገች በቂ ኃይል ስለአገኘች ነበር። በወቅቱ የነበረው  የኢጣልያንን የቅኝ ግዛት ፍላጞትን እጅግ ክፍ ያደረገው የቢልጅያን ንጉሥ ሊዮፖልድ ነበር፤ አንድ ግለሰብ ከአንድ ትንሽ አገር ተነስቶ ትልቅ የቅኝ ግዛት አፍሪቃ ዉስጥ ሲመሰርት እንዲት ታላቋ ኢጣልያን የቅኝ ግዛት አይኖራትም  በማለትና ከሊሎች አውሮፓውያን አገሮች በመፎካከር ነው።  ሊላው ከፋፍለህ ግዛ [Divide et imperia] የተባለዉን የአውሮፓውያን ዕቅድ ስራ ላይ አውለው በጥንታዌነቷ ታዋቂ የነበረችዉን የሮማን ግዛት መልሶ  በተምሳሊቷ ታላቋን የኢጣሊያን ንጉሠ ነገሥት  መንግሥት ለማቋቋም ነበር። አውሮፓውያኖች የራሳቸዉን ጎሳዎች አስተባብረው አንድ አገር፤ አንድ ሰንደቅ ዓላማ ፤ በጎሳ ሊከፋፈል የማይችል ሕብረት ከፈጠሩ በኋላ [Divide and conquer”] አፍሪቃን በጎሳ ከፋፍለው ለነሱ ታላቅነት ተገዥ ለማድረግ እንደሆነ ግልጽ ነው። ይህን “ሁኔታን” የአፍሪቃ ወገኖች ግንዛቢያችው ዉስጥ ስሊለ በጎሳ መለያየቱን እንደ በጎ ስራ አድርገው ይመለከቱታል፤ የኢትዮጵያ የዘውግ አቀኝቃኞች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ለጎሳቸው ተቆርቋሪ ሆነው የሚያካሂዱት የፖለቲካ  ትልቅ ነገር የሰሩ የሰሩ እየመሰላቸው ነው። የፕሮፌሰር መሳይ ከበደ “ወግ” ከዚህ አያልፍም፤ ፍልስፍናቸዉም “የዘውግ አመሰራረት ስር ነቀል ስለሆነ ሊቀለበስ አይችልም” ነው የሚሉት፤ ይህ የመለስና የኢሳያስ ራዕይ ነው። እንግዲህ በዚህ ውይይታችን የምንመለከተው የአፍሪቃን የጎሳ መለያየትና የአውሮፓን ሕብረት መፍጠር ይሆናል። ውይይታችን መልካም እንዲሆንና ለመማር ጥሩ “ሁኔታ” ለማመቻቸት የምንሰጠው አስተያየት በተሰጠው መልዕክት ላይ እንጂ በመልከተኛው ላይ መሆን የለበትም፤ አንባቢ አስተያየት ለመስጠት ፍጹም የሆነ መብት አለው፤ ውይይቱ  ግን አንባቢው በስጠው  አስተያየት ላይ ከአቶኮረ ዉጢት አልባ ሆነን መማማር አንችልም፤ የወያኔ ዋናው ስራው ተሽቀዳድሞ በመጀመሪያ አፍራሽ  አስተያየት መስጠት ነው። ለዚህ አፍራሽ አስተያየት አንባቢ ቦታ መስጠት የለበትም ፤ ይህ የተባለበት ምክናያት በሁለተኝው ክፍል ላይ የተሰጠዉን በማየትና በርከት ያሉ አንባቢዎች በላኩሉኝ መልእክት መሰረት ነው፤ መልካም ውይይት]።
መቅድም
ታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚሉት የአድዋ ጦርነት የተከሰተው ኢትዮጵያና ኢጣልያን በተፈራረሙት ውሎች ምክናያት አይደለም፤ የዉሎቹ ፊርማ ሰበብ ነው እንጂ  ለጦርነቱ ምክናያት አልነበረም ፤ዉል ተፈረመ አልተፈረም ኢጣላያን የግድ ቅኝ ግዛት አፍሪቃ ዉስጥ ማግኝት ስለአለባት ጦርነቱ አይቀርም ነበር፤ ለዚህም በመረጃነት መቅረብ ያለብት  የ1884/85 በርሊን ላይ በተደረገው ጉባኢ ላይ ማን ምን ማግኝት እንዳለበት የተደረገው ስምምነት ነው። ይህ ከተባለ በኋላ ታሪኩ ቅደም ተከተሉን ይዞ ይቀርባል። የሚኒልክና የአድዋ ጦርነት ታሪክ ብዙ ቅድመ “ሁኔታዎች” ስለአሉት በአጭሩ ይጠቀሳሉ፤ እዚህ ላይ አንባቢ ታሪኩን በቅጡ እንዲመለከተው የታሪኩን አቀማመጥ በቅድሚያ ማስረዳት አስፈላጊ ነው። ታሪክ ፈጣሪ አለው፤ ያ ታሪክ ፈጣሪ አስቦበትም ሆነ ሲያስብበት፤ በአጋጣሚም ሆነ በስሊት “ሁኔታው” ሲመቻች የታሪክ ሂደቱ ይጀምራል፤ በሂደቱ እያለ ታሪክ ሊሆን አይችልም፤ መድረሽዉም ምን እንደሆነ ስለማይታወቅ ታሪካዌ ሂደቱን ሳይጨርስ ሊጻፍ አይችልም፤ ታሪክነቱ የሚታወቀው ቢያንስ ከሶወስት ትውልድ በኃሏ ነው። ለምሳሌ ዶሮዋን ተመልከት፤ እንቁሏሏን እንደጣለች ጯጩቶቻ አይፈለፈሉም፤ የሚፈለፈልበትን “ሁኔታ” ታመቻቻለች፤ ፉጡራዌ ሂደትን ተከትላ የፈለፈለችውን  እንቁላል የሚያስፈልገዉን ሙቀት በመስጠት ጯጩቹ  እንዲፈለፈሉ ታደርጋለች፤ ይህ ፉጡራዌ ሂደት ነው፤ አንባቢ በድጋሜ መመልከት ያለብት “ሁኔታን” ነው፤ ዶሮዋ የምትወልደዉን እንቁላል በየግዜው ከተበላባት ጯጩቾቻን የምታገኝበት “ሁኔታ” አይኖርም፤ “ሁኔታ” ወሳኝ ነው። በተጨማሪ አንባቢ በትኩረት ማወቅ ያለበት የታሪኩን  የአጻጻፍ ዘዴ ነው። ሁለት ዓይነት ታሪክ አለ፤ በተለምዶ የሆነ ያልሆነዉን ተጽፎ ታሪክ ሆኖ ሲቀርብ የሚያስክትለው ጥፋት ከፍ ያለ ነው፤ ታሪክ የሕብረተሱቡ ያለበትን “ሁኔታ” የአለፈዉን ስሕተት የሚያበት መስተዋት ስለሆነ ከዚህ ታሪክ ከአልሆነ ታሪክ የሚያገኝው ትምህርት ሳይሆን ጥፋትን ነው። የሁለትኛው  ታሪክ አጻጻፍ በታሪክ ጸሐፊዎች ሲጻፍ ልዩ ቦታ ይኖረዋል፤ የታሪክ ቧለሟዩም ትልቅ ኃላፊነት ስለአለበት የተከሰቱትን “ሁኔታዎች” ከነባር ቅርስ ጋር እያመሳከረ አፈ ታሪኩና ንግርትን እያገለለ ምክናያቶችን እየመረመረ የሕብረተሰቡን ሕሊናዌነት ከነባር “ሁኔታ” ጋር እያገናዘበ በጽሑፍ ይመዘግባል፤ ቅድመ “ሁኔታ” እንዲት እንደተፈጠረና ለሕብረተሰቡ ያስገኘውን ጥቅም ወይም ጉዳት በሂሳብ ተሰልቶ በሚዛን ተመዝኖ ይቀርባል፤  ለዚህ ነው “ታሪክ የሕብረተስብ መስተዋት” ነው የተባለው፤ ደግሞም “ስህተቱን ከታሪክ ያልተማረ ሕበረተሰብ መጨረሽው ጥፋት” ነው የሚባለው። እዚህ ላይ  ከፕሮፌሰር መሳይ ከበደና ከሚስተር  ሬኔ ለፎርት ጋር ትንሽ  ቆይታ ከአደረግን በኋላ ወደ ሚኒልክና አድዋ  ጦርነት እንገባለን፤ ከፕሮፌሰሩ ጋር መወያየት ያስፈለገበት ጉዳይ እሳችውና የዘውግ አቀኝቃኞች ሚኒልክን የሚመለከቱት በተለምዶ የሚነገርዉን አፈ ታሪክና ጥራት በሊለው የዘውግ ፍልስፍናን መሰረት በማድረግ ነው፤ ነገር ግን ቅድመ ሁኔታን ተወያይተን እስምምነት ላይ የማንደርስበት ምንም ምክናያት አይኖርም፤ ግን ሚስተር ለፎርትን እዚህ ውይይት ላይ ማቆየቱ አግባብ አይደለም፤ ምክናያቱም ጽሑፋቸው ከኢትዮጵያ ታሪክም ሆነ የፖለቲካ “ሁኔታ” ጋር ምንም ግንኙነት ስለሊለው ነው፤ ጽሑፋቸው ምናልባት ለብጎ አድራጊ አገሮች ወይም  ለልማት ገንዘብ አበዳሪ ባንኮችና  [ለዓለም ባንክ] ለአትራፊ ነጋዴዎች  ያለዉን “ሁኔታ” ሊያስረዳ ይችል ይሆናል፤ ስለዚህ እዚህ ላይ  ሚስተር ለፎርትን እንሰናበታቸውና ውይይታችን ከፕሮፌስሩና አክራሪ ብሕሬተሰበኞች ከሆኑ ወገኖቻችን ጋር ይሆናል፤ በተረጋጋ መንፈስና ቅን በሆነ ልቦና ከተወያየን  በኃሏ በታሪካዌ ሂደት አንድ አገር፤ አንድ ሰንደቅ ዓላማ፤ አንድ በሒር የሚባልበት “ሁኔታ” ሊፈጠር ይችላል፤ የውውይቱን መነሻና መድረሻ  ስለማናውቀው በትዕግስት እንጠብቀው። ከሁሉ አስቀድመን ለዉይይታችን ከታሪክ እየተቀነጠቡ የሚቀርቡትን ታሪካዌ “ሁኔታዎች” የሚመረምር መላ ምት እንመለከታለን፤ የመላ ምቱ መሰረት ቋንቋ ነው፤ ቋንቋው በሚገባ ስለዳበረ “ልብ ወለድ” ወይም “አፈ ታሪክ” ወይም “ንግርት” ወይም እንደ “ተረት” የሚነገሩትን ከመረጃ ጋር የሚቀርቡትን ታሪካዌ ሂደትን ለይቶ ለማየት ያስችላል፤ ለምሳሌ በዚህ ድረ ገጽ ላይ ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ እንዲት እንደገባ የሚመረምር በቋንቋ የዳበረ መላ ምት እንመልከት፤
እንግዲህ  አንባቢ እስከ አሁን  ድረስ በአደረገው የውውይት ጉዞ በቂ የሆነ ታሪካዌ ግምገማና “ሁኔታን” መርማሪ [ሐታቲ] መላ ምት ስለ አዳበረ ከዚህ በላይ የተጻፈዉን “ሐተታ” [ምርምር] “ሐትቶ” [መርምሮ]  በዋቢነት የቀረበውን ጽሑፍ ክርስትና ወደኢትዮጵያ ለመግባቱ መነሻ “ታሪክ” መሆኑንና ያለመሆኑን ሊመረምር [የሐትት] በቂ “ችሎታ” ይኖረዋል ብዮ እገምታለሁ፤ ይህ ግምት ነው፤ሊሆንም ላይሆንም ይችላል፤ እዚህ ላይ ዉይይታችን ከፍ ባለ ደረጃ እንዲያድግ በማለት “ሐተተ” የሚለዉን የግዕዝ ቃል ግሥ  እርባታዉን ማሳየት ለአንባቢው ምርምር ይረደዋል፤ እንግዲህ  “ሐተተ” የሚለዉን አርእስት ወስደን የግሡን እርባታ [እርባ ግሥ] እንመልከት፤ “ሐተተ” [መረመረ] “የሐትት” [መረመረ] “ይሕትት” [ይመረምር] “ሐቲቶት” [መመርመር] “ሐታቲ” [የመረመረ] “ሐታቲያን” [የመረመሩ] “ሐታቲት” [የመረመረች]  “ሐታቲያት” [የመረመሩ] “ሕቱት” [የተመረመረ] “ሐታቲ” [መርማሪ] እያለና በገቢር በተግብሮ እያሰረ በአር ዕስት ተከፍሎ በአዕማድ ተጠቅሎ በዕቢይ በንዕስና በደቂቅ አንቀጽ እየገባ “ሁኔታን”  የሚመረምር የግሥ እርባታ ነው። ቋንቋው በሚገባ ዳብሯል፤ አገር ፤ መንግሥት ፤ ሕብረተሰብ  ትምህርት ቤት ፤ ቤኖር ከዚህ የበለጠ “ሁኔታን” መርማሪ መሳሪያ የለም። ከዚህ በላይ የተጻፉቱን “ቅድመ “ሁኔታዎች” አሉ ብለን በመጠኑ ምርምራችንን እንቀጥል፤ ክርስትና ወደኢትዮጵያ ገባ በተባለብት ዓመት [334 ዓ.ም] ነበረ የተባለዉን በዕብይ አንቀጽ እንመዝግባቸው፤  “አገር” ፤ “ወደብ”  ፤ “ቤተመንግሥት” ፤ ቤተ መጻሕፍት” ነበሩ እንበል፤ በአንጻሩ ደግሞ በንዕስ አንቀጽ ደረጃ “ነጋዴ”  “ወጣቶች”  “ሽፍቶች” ነበሩ እንበል፤ እንግዲህ በዓብይና በንዕስ አንቀጽ ያሉትን ስንመረምር “በገቢርና”  “በተገብሮ” የተደረጉትን  ያለምንም ስህተት ማግኝት እንችላለን፤ ኢትዮጵያ የሚባል አገር አለ፤ ወደብ ከአለ የግድ የባሕር ኃይል አለ ማለት ነው፤ በወደቡ ላይ የሚተላለፍ ንግድ ከአለ ፅጥታ አስካባሪ አካል አለ፤ እንግዲህ በዋነኛነት የምናየው “ቤተመንግሥቱንና” ቤተ “መጻሕፍት” ነው፤ እዚህ ላይ ጥያቄው በምን አይነት “ሁኔታ” ነው እነዚህ ሆለት የሶርያን ወጣቶች የቤተመንግሥትና የቤተ “መጻሕፍት” ሃላፊ የሆኑት? በተለይ “መጽሐፍት” ቤቱ የሚነግረን በጽሑፍ የተጻፉ ጽሑፎችን የያዘና ታላቅ የሥነ ጽሑፍን ዕውቀት የተከማቸበት ቦታ መሆኑን ነው፤ ወጣቱ ፍሬሚናጦስ [Frementius] በምን ዕውቀቱ ነው ለዚህ ስራ የተመረጠው? ቋንቋዉን አይችልም ፤ ስለ ቤተ መጻሕፍት ቤትም የሚያቀው ነገር የለም ። በምን “ሁኔታ” ነው ፍሬሚናጦስ [Frumentius] አንድ የባሕር ኃይልና ወደብ ያለው አገር የቤተ መንግሥቱ ዋና አማካሪና ደግሞም የወጣቱ ንጉሥ እንደራሴ ሊሆን የቻለው? ይህንን “ሁኔታ” ሊፈጥር የሚችል ምክናያት አይኖርም፤ በተጨማሪ ለታሪኩ መጀመሪያ እንዲሆን የተሰጠው ቀን 334 ዓ.ም የተባለው ዘመን የፈጠራ እንጂ በዕውነት በዘያ ዘመን አንድ ሃይማኖት ተቀባይነት አግኝቶ  በአንድ ዘመን ወይም ዓመት ግዜ የነበረዉን ቤተ መቅደስ በከመ ቅስፈት ቤተ ክርስቴያን ብሎ ሊለዉጥ አይችልም፤ ስለዚህ በመረጃነት የቀረበው የልብ ወለድ “ታሪክ” እንጂ “ሁኔታ” ፈቅዶ በተግባር የሆነ “ታሪክ” አይድለም። ነባር ቅርስ እያለ ምን አልባት ሳይሆን  አይቀርም በሚል መላ ምት የተጻፈ ታሪክ ነው። እዚህ ላይ ክርስትና መግባቱንና ያለመግባቱን ሳይሆን በምን አይነት ሁኔታ እንደገባ ማወቅ አስፈላጊ ነው ምክናያቱም የሕብረተሰቡ ታሪክ ስለሆነ። መነሻ ፤ መንደርደሪያ፤ መድረሻ የሊለው ታሪክ ሊሆን አይችልም፤ የሕበረተስቡንም ሕሊናዉነት ምን እንደሆነ አይገልጽም፤ ከክርስትና በፊት ለብዙ ዘመናት መቅደስ ያለው አገር፤ ሥነ  ጽሑፉ ዳብሮ በመጻሕፍት ቤት የተለያዩ ጽሑፎችን ያከማቸ ሕብረተሰብ በአንድ ሶርያን ወጣት አማካይነት ክርስትናን ተቀበለ ለማለት ያስቸግራል [ሙሉ ታሪኩን ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ይመልክቱ–የጥንታዌት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አቅጭር ታሪክና ስነ ሥርዓት፤ ክፍል አራት  December 19, 2016]
እዚህ ላይ ሰፋ ያለ  መግለጫ የተሰጠበት ምክናያት የኢትዮጵያ ታሪክ “ተረት” ነው፤ ከመቶ ዓመት በፊት ኢትዮጳያ የምትባል አገር የለችም ነበር፤ “ሚኒልክ በኃይል የደቡቡንና የሰሚኑን ሕዝብ ቀጥቅጦ”  የፈጠራት አገር ነች በማለት ንግርትና አፈ ታሪክ እንደ ታሪክ ሆኖ የሚጻፍበትና  የሚነገርባት አገር ስለ ሆነች ነው፤ በእንደዚህ አይነት “ሁኔታ” ላይ ሆኖ ታሪክን ከነባር ቅርስ ጋር እያገናዘቡ ለመጻፍ አስቸጋሪም ቢሆንም ጢኔኛ ሆኖ ለሚወለደው ትውልድ ማሳወቅ ታሪካዌ ግዲታ ነው፤ የዘውግ አቀኝቃኞችና ጥገኛነትን አክራሪዎች የታሪካችንን መላ ምት የተለየ መለኪያ ያስፈልገዋል፤ የታሪክ አባቶቻችን አላሉትም” እያሉ እንድሚያዋዱቁት አውቀን ከባሕላችን በመነጨውና በቅጡ በዳበረው ቋንቋችን ለልጅ ልጆቻችን የታሪክ ቅርሳችንን እናስቀምጣለን። እንግዲህ የመላ ምታችንን ብቁነት ከአስተካክልን በኃላ የምኒልክንና የአድዋን ቅድመ “ሁኔታውች”  ከታሪክዌ ሂደት ላይ ቀንጠብ እየተደረገ ይቀርባል።
ምኒልክና አድዋ የቅድመ “ሁኔታዎች” ዉጢት ናቸው። የሰሎሞናዌ ሥረወ መንግሥት በዛጓው ቢተ አገዛዝ ከተወሰደ ከመቶ ዓመት በኃላ በይኩኖ አምላክ በ1270 ዓ ም  ተመልሶ ሲመሰረት የኢትዮጵያ ግዛት ከአትበራ እስክ ፑንት መሆኑን ነባር ቅርስ ይመስክራል፤ በአፈ ታሪክ የሚነገርለት ፕሬሰተር ጆን [Prester John] የሚባል ንጉሥ እንደ ነበር በሞላ አውሮፓ ይነገር ነበር፤ ነገር ግን ይህ ንጉሥ  የኢትዮጵያ ወይስ የሕንድ  ይሁን በእርግጠኝነት የሚታወቅ ነገር የለም፤ ንግርት ነው፤ ሆኖም ይኩኖ አምላክ በ1270 እስከ 1277 በአለው ግዜ ዉስጥ ከክርስቲያን ተጋዲያዎች [Crusaders] ጋር ለመገናኝት ሞክሮ እንደነበር ይነገራል፤ ከንግርት በላይ ምንም ተጨባጭ ቅርስ የለም። ነገር ግን አምደ ጽዮን [1314—44] ግዛቱን እስከ ቀይ ባሕር አስፋፍቶ በቁጡጡሩ ስር እንደነበር የሚያስረዳን በቂ መረጃው ልጁ ሰይፈ አዕራድ [1344—77] ከክርስቲያን ተጋዳዮች ግንኙነት አድርጎ ኢትዮጵያዊያኖችን በኢየሩሳሊም  በቂ ድጋፍ ለመስጠት አስፍሮ እንደነበርና ይዞታዉም በኢትዮጵያ ቅርስነት እስከ አሁን ድረስ እንዳለ መሆኑን ነው። የኢትዮጵያ ግዛትም ከንጉሥ ዳዌት እስከ ዘርዓ ያዕቆብ ድረስ ተስፋፍቶ እንደነበር ታሪክ ይነግረናል፤ ነገር ግን በልብነድንግል ዘመነ መንግሥት [1508-40] የኢትዮጵያ ግዛት ቀስ በቀስ እየቀነሰ ሂደ፤ ለዚህም ዋነኛ ምክናያቱ በዳዌትና  በልጁ ዘርዓ ያዕቆብ ግዜ የአንድ ሰንበት የሁለት ሰንበት ጥያቄ በቤተ ክርስቲያኑ ዉስጥ ለብዙ ግዜ ሲያከራክር ስለነበረና ደግሞም የኢትዮጵያ መንግሥት ከክርስታያን ተጋዳዮች ጋር መተባበርና በኢየሩሳሌም ዉስጥ ድጋፍ ሰጭ ኃይል ማስቀመጥ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ የእስልምና እምነት አስፋፌዎች አሳሳቢ ጉዳይ ሆኖ ስለ አገኝት የኢትዮጵያን ግዛት ቀይ ባሕርን፤ ኢርትራን፤ ጂቡቲን፤ በአጠቃላይ የሕንድ ውቃያኖስ አዋሳኝ የሆኑትን ወደቦች በመያዝ እስልምና ወደ መሐል አገር እንዲገባ በማድረግ ለግራኝ መሐመድ መነሳት ትልቁን መስትዋጽኦ አድርገዋል። እዚህ ላይ ለአንባቢ ሳይጠቀስ የማይታለፍ ታሪክ ቢኖር ለእስልምና ሃይማይኖት መቋቋም ኢትዮጵያ ትልቁን ሚና መጫወቷን ነው፤ በመጀመሪያ ነቢዩ መሐመድ በሕጻንነቱ ወላጆቹ ስለሞቱ እንደ እናት ሆና ያሰደገችው ባሕርዋ የምትባል ሲት ነበረች፤ ታሪኩ እንዲህ ነው፤ በዘመኑ የአረብያን ግዛት ኢትዮጵያ ታስተዳድር ነበር፤ ነገር ግን የባሕር ወደቧና የጦር ኃይሏ በሮማን መንግሥት ኃይል እየቀነሰ ስለመጣ የግድ የአረብን ግዛት መተው ስለነበረባት ኢትዮጵያውታ ባሕርዋ ጥቂት ከቀሩት  ኢትዮጵያዉያን አንዷ ነበረች፤ በዚህ አጋጣሚ የስድስት ዓመቱን ወጣት እንደ እናት ሆና አሳድገዋለች፤ በኃሏም ለአቅመ አዳም ደርሶ ነብይ ሲሆን በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ተደርጎለታል፤ ይህውም የየጎሳው ባላባቶች ነቢዩን በማሳደድ ላይ በነበሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት እምነቱን በነጻነት እንዲከተል አድርጋለች፤ ነቢዩም የእስልምና ሃይማኖቱን ሲመሰርት በተነሳው ጦርነት ምክናያት በመጀምሪያ እስልምና የተቀበሉትን ለደሕንነታቸው ብሎ የላካቸው ወድ ኢትዮጵያ ነው፤ ይህ አፈ ታሪክም ንግርትም አይደል፤ እውነተኛ ታሪክ ነው፤ ለዚህም በመረጃነት ሊቀርብ የሚገባው ነቢዩ ለተከታዮቹ ኢትዮጵያ ባለውለታና ታላቅ ታሪካዌ አገር ስለሆነችና ለሰው ልጅ ሁሉ ተምሳሌት ነችና እንድትነኳት በሎ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ለስምንት መቶ ዓመት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ኢትዮጵያን አልነኩም፤ ይህንን የማያውቅ የአስልምና ሃይማኖት አባት አይኖርም።
እንግዲህ አንባቢ ይህ ውይይት በተሟላ ታሪክ  ላይ ሳይሆን ቀንጠብ እየተደረገ የቀረበ  የዘውግ አቀኝቃኞችንና የጽንፈኛ ብሒረተሰበኞችን ወግ ለማስተካከል  መሆኑን ማወቅ ግዲታ ነው፤ የዘውግ አቀኝቃኙን ፕሮፌሰርና አክራሪ ብሒረተሰቦኞችን አስተካክላለሁ ማለት ዘበት ነው፤ ከዚያም አልፎ በሰማይ ላይ እንዳለችው ላሟን መሆን ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያን አንድ ሕብረተሰብ እንደ ተለያየ  ሕብረተሰበዎች አድርገው ስለበከሉት ሕዝብ ይህንን አፈ ታሪክና ተረት በታሪክ አምድ አድርገን  ለማስተዋወቅና ለማስተካከል ነው፤ ሰሚና አንባቢ ከተገኝ የሕብረተሰባችንን አንድ ነት ለማዳን የተደረገ ሙክራ ነው። ደግሞም ከዚህ በፊት እንደተጠቀሰው ምን ይታወቃል በውይይት የማይፈታ ነገር የለም፤ ምናልባት ተቀራርበን  ታሪካችን በዉጭ ኃይል እንደተጻፈው ሳይሆን እውነተኛዉን ታሪካችንን መሰረት አድርገን ቅሪታችንን  እንፈታው ይሆናል፤ እዚህ  ላይ ትልቁን ጥንቃቄን ማደረግ ያለብን አሁን ባለው ሥርዓት ተጠቃሚዎችና ጥገኝነትን በሚያጠብቁ  ልሂቃን እንዳንወናበድ ነው።  በምንባቡ እንዳንሰላች የሶወሰትኛው ክፍል እዚህ ላይ ይቆማል። ከላይ እንደተጠቀሰው የሚስተር ሬኒ ለፎርት ወግ እዚህ ላይ ስልተጠናቀቀ የአራተኝው ክፍል አርዕስት የሚሆነው “የመሳይ ከበደና የጽንፈኛ ብሒረተሰበኞች ወግ”  ይሆናል። በአራተኛው ክፍል የምንወያይበት አርስዕስት “የቀይ ባሕር መወሰድ፤ የእስልምና ሃይማኖት መስፋፋት፤ የግራኝ መሐመድ መነሳት፤ የኢትዮጵያ ግዛት መፈራረስና የልብነ ድንግል መንግሥት መዳከም፤ የዘመን መሳፍንት ዘመን፤ የሚኒልክ ዘመነ መንግሥት ይሆናል። በተጨማሪ ብዙ ክፍሎች ስለሚቀሩ አስተያየቶች ቢቆዩ ይመረጣል፤ ሆኖም እዚህ በቀረበው ላይ መስተካከል አለበት የሚሉት ከአለ ለመማር ስለሆነ ይጠቅማል ብዮ እገምታለሁ። ትምህርታዌ ውይይት እንዲሆንልን እመኛለሁ።

ኦባማ ለናታንያሆ የላኩት የስንብት ስጦታ | ሊታይ የሚገባው የሳዲቅ አህመድ ትንታኔ

የአሜሪካ ድምጽን በድምጽ የመሻር አቋምን በዜሮ? 38 ቢሊዮን ዶላር ያልበቃዉ የእስራኤል እሮሮ? በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የመፍትሄ ሐሳብና መመሪያ 2334 ይታይ ይሁን ተቀይሮ?
በሳዲቅ እህመድ 
አረብ ከሆነችዋ ፍልስጤም ጎን ለጎን አይሁዳዊቷ አገር እስራኤል ትዋቀር ዘንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በኅዳር 20/1942 (November 29, 1947) ድምጽ ሰጥቶበታል።ከ69 አመታት በሗላ በታኅሣሥ 14/2009  የተባበሩት መንግስታት የጸጥታዉ ምክር ቤት ቀደም ሲል የነበረዉን ዉሳኔ ዳግም ለማቆየት ድምጽ ሰጠበት።መመሪያ (የመፍትሔ ሐሳብ) 2334 ይፋ መደረጉን በማጤን ሐሳባቸዉን የሰጡት ሐዓሬት በመባል ለሚታወቀዉ የእስራኤል ጋዜጣ የሚጽፉት ጊዲኦን ሌቪ “ባለፉት አመታት ዉስጥ ከነበረዉ የተስፋ መቁረጥና የጨለማ ባህር ተፈንጥቆ የወጣ የተስፋ እስትንፋስ!” ሲሉ ገልጸዉታል። 
እስራኤላዊዉ ጸሃፊ ጊዲኦን ሌቪ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታዉ ምክር ቤት ይፋ ያደረገዉ መመሪያ በቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አመራር እክል ሊገጥምነዉ እንድሚችል እያመላከቱ የስራ ዘመናቸዉን በመጨረስ ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ኦባማን “ይህንን በስንብት ወቅቶ ላይ ያደርጋሉን?” ስንል በቁጣ መጠየቅ አለብን ይላሉ። እንደ ጊዲኦን ሌቪ አገላለጽ ኦባማ ይህንን ቀደም ሲል ሊያደርጉ ይገባ ነበር። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቤንያሚን ናትንያሆና ካቢኒያቸዉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታዉ ምክር ቤት ያወጣዉ መመሪያ ተገቢ እንዳልሆነ የተቃዉሞ ድምጽ በሚያሰማበት ወቅት የእስራኤል ሚዲያዎች መመሪያዉ ጸረ እስራኤል ነዉ ሲሉ የፕሮፓጋንዳ ስራ ላይ እንደሚሰማሩ አሳዉቀዋል ጊዲኦን ሌቪ። 
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰጥታዉ ምክር ቤት በታኅሣሥ 14/2009 ያወጣዉ የመፍትሔ ሐሳብ ለእስራኤል ከወትሮዉ የተለየ ነበር። እስራኤል በሐይል በያዘቻቸዉ የፍልስጤም ይዞታዎች ላይ የምታደርገዉን መስፋፋት አዉግዟል። እስራኤል የምታደርገዉ ሰፈራ ህገወጥ ነዉ ሲልም አረጋግጧል።ማንኛዉም የመስፋፋትና የሰፋራ እንቅስቃሴ እስራኤል ታቆም ዘንድ አሳስቧል።እስራኤል ለብቻዋ የምታደርገዉን የድንበር መስፋፋትና የምስራቅ እየሩሳሌምን ወደራሷ መጨመሯን ዉድቅ አድርጎታል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታዉ ምክር ቤት ለሚያወጣቸዉ መመሪያዎችና ደንቦች ደንታ ቢስ እንደሆነች የምትታወቀዋ እስራኤል የዘንድሮዉ ዉሳኔን እንደስጋት ተመልክታዋለች። ቀደም ሲል አሜሪካ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቷን ተጠቅማ ማንኛዉንም እስራኤልን የሚቆርቁር ነገር ከማለዘብ አልፋ ታከሽፍ እንደነበር ይታወቃል። በዘንድሮዉ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታዉ ምክርቤት የድምጽ አሰጣጥ ሒደት ላይ አሜሪካ ድምጸ ተአቅቦ በማድረጓ ማሌዥያ፣ቬንዝዋላ፣ሴኔጋልና ኒዉዝላንድ ያቀረቡት ረቂቅ ሐሳብ አስራ አራት ለዜሮ በሆነ ከፍተኛ ድምጽ በማለፉ የእስራኤል ባለስልጣናት ከጎናቸዉ ያልቆሙትን ፕሬዝዳንት በራክ ኦባማ በግልጽ እስከመዛለፍ መድረሳቸዉን ለማወቅ ተችሏል። 
አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ኦባማ ለናታንሆ የሰጡት የስንብት ስጦታ ሲሉ ተሳልቀዉባቸዋል። አይሁዳዉያን ለሰላም በሚል መጠሪያ ለፍልስጤማዉያን መብት የሚከራከሩ ቡድኖች ዉሳኔዉን ተገቢ ሲሉ አድንቀዉታል። ለኦባማ አመራር ተገቢዉን ክብር የማይሰጡት ናታንያሆ በጸጥታዉ ምክር ቤት የእስራኤልን የመስፋፋትና የሰፈራ ተግባር ህገወጥ ብለዉ ድምጽ ከሰጡ አገራት ጋር የሚኖረዉ የስራ ግንኙነት በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴራቸዉ በኩል የላላ እንደሚሆን አሳዉቀዋል።
የጸጥታዉ ምክር ቤት ያወጣዉን መመሪያ በማርቀቁ ረገድ ግብጽ ተሳታፊ ነበረች። ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለግብጹ የመፈንቅለ መንግስት መሪ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልሲሲ ስልክ በመደወላቸዉ ሳቢያ ግብጽ ረቂቁን ማቅረቡን ትታ  አፈግፍጋለች። በአገሩ ብሎም በአረቡ አለምና በሙስሊሙ አለም ተወዳጅ ያልሆነዉ የጄኔራል አልሲሲ መንግስት ያደረገዉ ማፈግፈግ የበለጠ እንዲጠላ አድርጎታል። በጠቅላይ ሚኒስቴር ነጂብ ረዛቅ የሚመራዉና በርካታ አገራዊ ፈተናዎችን እየተጋፈጠ ያለዉ የማሌዥያ መንግስት የግብጽን ቦታ በመተካት የፍልስጤማዉያን አጋር ሆኗል። 
በአይሁዳዉያን አሜሪካዉያን የዲፕሎማሲና የፖለቲካ ጥቅም አስከባሪዎች (Lobbying) አማካኝነት አሜሪካን ወዳሽት አቅጣጫ ትመራ የነበረቸዉ እስራኤል በኦባማ የስራ ዘመን ማብቂያ ወቅት አልተሳካላትም።ከምርጫ ዘመቻ ( Presidential Campaign) ግብረሐይላቸዉ ዉስጥና ሁለት ግዜ ፕሬዝዳንት እስኪሆኑ ድረስ በካቢኔያቸዉ ዉስጥ አይሁዳዉያን አሜሪካዉያንን በቁልፍ ቦታ ያስቀመጡት ኦባማ የሚያደርጉት ምርጫ ባለመኖሩና የታሪካቸዉን ምእራፍ (legacy) ለማሳረግ  በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዉስጥ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑትን ሳማንታ ፓወር አዘዉ አሜሪካ ባልተጠበቀ መልኩ ከእስራኤል ሳትወግን ድምጸ ተአቅቦ አድርጋለች። አዲሱ የጸጥታዉ ምክርቤት መመሪያና የመፍትሔ ሐሳብ ተግባራዊነት በሒደት የሚታይ ቢሆንም ለእስራኤል የእግር እሳት የሆነባት ”እንዴት እንደፈራለን?” የሚለዉ የበላይነት ስሜት እንደሆነ እየተስተዋለ ነዉ። አንዳንድ የእስራኤል ዜጎች ከሙስሊም አባት የተወለዱትን በራክ ሁሴን ኦባማ “ሁሴንነቱ መጣበት” በማለት ማብጠልጠል ጀምረዋል። 
አዲሱ የጽጥታዉ ምክር ቤት 2334 የመፍትሔ ሐሳብና መመሪያ እስራኤል በሐይል የያዘቻቸዉን የፍልስጤም ይዞታዎች ተገቢ አለመሆኑን አይደሉም ያትታል።እስራኤል በአይሁድ ሰፈራ ስም የምታደርገዉን መስፋፋት ህገወጥ ነዉ ብሎ ይደመድማል።
የእስራኤል መንግስት ለአለምአቀፍ ህጎች ተገዢ ሊሆን ቀርቶ…አለም አቀፍ ህግ እንደሚመለከተዉ  ማስመሰል ባቆመበት፣ የፍልስጤማዉያንን መሬትን በግልጽ መስረቁን ህጋዊ አስመስሎ ሲሰራ፣ የእስራኤል ካቢኔ አባላቶች የሁለት ግዛቶች መፍትሔን በመተዉ በዉስጧ የአረብ ዜጎች ያሏትን አንዲት እስራኤል ለማዋቀር እምደሚሹ ሲናገሩ፣ ስልጣኑን ሊያስረክብ ሳምንታት የቀሩት የኦባማ ካቢኔ እና አለም አቀፉ ማህበረሰብ እኛም የፍልስጤም ጉዳይ ያገባናል በማለት የላኩት መልእክት ነዉ ሲሉ ማይክል እስካፈር ኡመርማን የተባሉ ጸሃፊ  የጽጥታዉ ምክር ቤት 2334 የመፍትሔ ሐሳብና መመሪያ አስመልክቶ ከእስራኤል ሐሳባቸዉን በጽሁፍ አስፍረዋል። 
ማይክል ኡመርማን አክለውም እስራኤል በዌስት ባንክ የምታደርገዉን መስፋፋትና ህገወጥ ተግባር አስመልክቶ ከአዉሮፕያዉያን አገራት የሚደርስባትን ጫና ለመመከት ምእራባዉያኑን አንፈልግም ከሩስያ፣ከቻይና፣ከህንድና ከተወሰኑ የፍሪካ አገራት ጋር እተባበራለሁ የሚል ፖሊሲን ተግባሪ መሆን መጀመሯን ይገልጻሉ። እስራኤል ፖሊሲዋን ብትቀይርም አለም በእስራኤል የመስፋፋት ሰፈራ ላይ ያለዉ አቋም የሚቀየር አለመሆኑን አመላክተዋል።የጸጥታዉ ምክርቤት አዲሱ መመሪያ እስራኤልን በጣሙን ሊያሰጋት ከሚችልበት ምክያቶች አንዱ አለምአቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (https://www.icc-cpi.int/)ከእስራኤል ሰፈራና መስፋፋት በተገናኘ መልኩ  እስራኤል የጦርነት ወንጀል ፈጽማለች የሚል የክስ ፋይል ሊከፈትባት መቻሉ ነዉ። ይህ ደግሞ የእስራኤል ፖለቲከኞችና የጦር መኮንኖች የወንጀል ምርመራ እንዲደረግባቸዉ የሚያስችል በመሆኑ ለእስራኤል ባለስልጣናት የሚመች አለመሆኑን ጸሃፊዉ ኡመርማን ከእስራኤል ገልጸዋል።
እስራኤል ለሚቀጥሉት አስር አመታት ወታደራዊ አቅሟን የበለጠ ታደራጅ ዘንድ ከኦባማ ካቢኒ 38 ቢሊዮን ዶላር ተመድቦላታል። ይህንን ታላቅ የእርዳታ አሃዝ አሜሪካ ለሌላ አገር በታሪክ ሰጥታ የማታውቀዉ መሆኑን ተንታኞች ያስረዳሉ። በአመት ለእስራኤል 3.8 ቢሊዮን ዶላርን ያጸደቀዉ የኦባማ አስተዳደር የስልጣን ዘመኑ ሊገባደድ ሳምንታት ሲቀሩት በጸጥታዉ ምክር ቤት በኩል ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቱን ሳይጠቀም በድምጸ ተአቅቦ ከእስራኤል ጋር አለመቆሙ “ኦባማ ከጀርባ ወጉን” ብለዉ የእስራኤል ባለስልጣናት እንዲማረሩ አድርጏቸዋል። 
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቤንያሚን ናታንያሆ ተኮሳትረዉና ተቆጥተዉ “ለረጅም ግዜ ከወዳጃችን አሜሪካ ጋር የምናደርገዉን ሰፈራ አስመልክቶ የሐሳብ ልዩነት አለን፣ ይህንን የሐሳብ ልዩነት ግን አብረን ልንፈታ ይገባ ነበር፣ወዳጅ ወዳጅን ጸጥታዉ ምክር ቤት አይወስድም፣በጸጥታዉ ምክር ቤት በኩል መፍትሔ እንደማይመጣ ተነጋግረናል፣ ቢሆንም ግን ከሚቀጥለዉ የትራምፕ አመራርና ፓርላማ ዉስጥ ካሉ እንደራሴ ወዳጆቻችን ጋር አብረን በመስራት እናስተካክለዋለን” ብለዋል። 
ብዙ አሜሪካዉያንና ለሰላም የሚታገሉ አይሁዳዉያን አሜሪካ እስከመቼ የእስራኤል ሞግዚት ሆና ትቀጥላለች? እስከመቼ የቀረጥ ከፋዮች ገንዘብ ላንዲት አገር ይርከፈከፋል?እስከመቼ አገራችን አሜሪካ በዲፕሎማሲና በደህንነት ጉዳዮች ለእስራኤል ስትል ፈተናን ትጋፈጣለች? በማለት ይናገራሉ።እስራኤል ዉስጥ ያሉ የናታንያሆ ተቀናቃኞች በበኩላቸዉ የቀኝ ክንፍ አክራሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስቴር አገራቸዉን በዲፕሎማሲና በጽጥታ ጉዳይ አጣብቂኝ ዉስጥ እየከተቱ መሆኑን በስጋት ያስረዳሉ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታዉ ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላት አሉት። አምስት ታላቆች በመባል የሚታወቁት ዩናይትድ እስቴትስ፣ሩስያ፣ቻይና፣እንግሊዝና ፈረንሳይ ሲሆኑ ሌሎች ቋሚ ያልሆኑ አስር ተለዋጭ አባላት አሉት። የነዚህን አባላት ድምጽ አንቀበልም ያሉት የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢንያሚን ናታንያሆ እስራኤል በዌስት ባንክ የምታደርገዉን ህገወጥ ሰፋራ አስመልክቶ ድምጽ ከሰጡ 12 አገራት ጋር ያላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዉስን እንዲሆን አዘዋል ሲል ሲል ሲ.ኤን.ኤን የእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናትን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ይህም እርምጃ እስራኤልን ከአለም አቀፉ የዲፕሎማሲ መድረክ እራሷን በራሷ የበለጠ እንድታገል የሚያደርግ መሆኑን እስራኤላዉያን ሳይቀሩ ቢያስረዱ የእስራኤል ባለስልጣናት አሻፈረን ብለዉ ዛቻቸዉን ቀጥለዋል።
የህዝብ ብዛቷ ስምንት ሚሊዮን የሆነው እስራኤል እንደምን ከአለም ጋር ተናቁራ የዜጎቿን ደህንነት ታስጠብቃለች? የሚለዉ ጥያቄ ሁሌ የሚነሳ ቢሆንም የቀኝ ክንፍ አክራሪ የሆነዉ የናታንያሆ መንግስት ለአለም መንግስታትና ለአለምአቀፍ ህጎች ደንታ ቢስ መሆኑን እያሳየ ነዉ። አሜሪካዊዉ ጋዜጠኛ ቤን ዋይት አለም በእስራኤል ላይ ያለዉን አቋም ማጠንከር ይገባዋል ጥንካሬዉ በንግግር ብቻ ሳይሆን በተግባርም መሆን አለበት በማለት ጽፏል። ቤን ዋይት ቀጣዩና አዲሱ አመት እስራኤል  አገር አልባ በሆኑት ፍልስጤማዉያን ላይ በዌስት ባንክና በጋዛ ሰርጥ እያደረገቸዉ ያለዉ ወታደራዊ አፈና 50 አመት ይሞላዋል ሲል እያስረዳ አንዲት አፈንጋጭ አገር በዘረኝነትና ከፋፍሎ በመግዛት የምታደርገዉ ጭቆና መቆም አለበት ሲልም ያስረዳል።
ሐአሬት የሚባሌዉ የእስራኤል ሊበራል ጋዜጣ በታህሳስ 18/2009  ባወጣዉ ርእሰ አንቀስ ናታንያሆ እስራኤልን ወደታች እያዘቀጧት ነዉ ብሏል።ናታንያሆ ያለዉን የዉይይት መስመር በሙሉ እየዘጉ ነዉ ያለዉ ጋዜጣ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ የገጠማቸዉን የጸጥታዉ ምክር ቤት ዲፕሎማሲያዊ ሽንፈትን ጠቅሶ ግትር የሆኑት ናታንያሆ ከሌሎች አገራት ጋር ያለዉን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየደረመሱ መሆኑን አስረድቷል። ከእስራኤል ጋር ወዳጅ የሆኑ አገራት በድፍረት የእስራኤልን ህገወጥ ሰፈራና መስፋፋት በመቃወም ድምጽ መስጠታቸዉ
ሐአሬት እየገለጸ ናታንያሆ ዲፕሎማሲያዊ አሰራርን ትተዉ አለም አቀፋዊ ህግን አደገኛ በሆነ መልኩ ችላ እያሉ መሆኑን በርእሰ አንቀጹ ላይ ገልጿል።
አያሌ አመታትን ያስቆጠረዉ የፍልስጤምና የእስራኤል ግጭት የሟቾች ቁጥር የሚቆጠርበት ቢሆን እንጂ እልባት አላገኘም። በሁሉም አቅጣጫ ያሉ የሰላም ድምጾች ሲታፈኑ ይስተዋላል። የዲፕሎማሲና የፖለቲካ ጫናዎች መሰረታዊ ለዉጥ አላመጡም። በሁለት ጎራ ያሉ ሐይላት እኔ ትክክለኛ ነኝ በማለት ፍልሚያ ዉስጥ ይገኛሉ። እስራኤል በምታደርገዉ የመስፋፋትና የሰፈራ ፕሮግራም ፍልስጤማዉያንን እያፈናቀለች ካገራቸዉና ከቀዬ አቸዉ እንዲሰደዱ ማድረጉን ተገቢ አድርጋ እየቀጠለች ባለችበት ወቅት አለም አቀፉ ማህበረሰብ በጸጥታዉ ምክር ቤት በኩል በቃሽ የሚል ዲፕሎማሲያዊ ጫና ለማስደር ሞክርሯል።
በጠቅላይ ሚኒስቴር ናታያሆ የሚመራዉ መንግስት የጸጥታዉ ምክርቤት የመፍትሔ ሐሳብን አሻፈረኝ በማለት በተለያዩ አገራት ላይ ጣቱን እየጠቆመ ነዉ። ባንድ ወቅት ጥቁሩን የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ቸል በማለትና ያለ አሜሪካዉ ቤተ-መንግስት እውቅና ዋሽንገተን ዲሲ መጥተዉ በዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ቀላዋጭነት ንግግር ያደረጉት ቤን ያሚን ናታንያሆ ከጥቁሩ ፕሬዝዳንት ጋር የጎሪጥ እንደሚተያዩና እንደማይስማሙ በስፋት ይዘገባል። በኦባማ ካቢኒ ለአስር አመታት የጸደቀላቸዉን 38 ቢሊዮን ዶላር ሳይበቃቸዉ አሜሪካን በጸጥታዉ ምክርቤት ያላትን ድምጽ በድምጽ የመሻር መብት በምርቃት እፈልጋለሁ ያሉት ቤን ያሚንንናታያሆ ለግዜዉ ምርቃቱን አላገኙትም። ያገኙት ነገር ቢኖር የኦባማ የስንብት ስጦታ ነዉ። ናታንያሆ አሻፈረኝ ብለለዉ እየዛቱ ነዉ። የቲዊተሩ ዲፕሎማትና አዲሱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ቃለ መሃላ የምፈጽምበት ጥር 12/2009 ይድረስ እንጂ ሁናቴዎች ይቀየራሉ በማለት ኦባማን ማብጠልጠል ጀምረዋል።
እምቢተኛዉ ቢን ያሚን ናታንያሆ ድምጽ በሰጡ አገራት ላይ ጣት መጠቆማቸዉን ቀጥለዋል።ለመሆኑ በአለም ህዝብ ላይ እስከመቼ በእብሪት ይዛታል? የሚል ጥያቄ እየተነሳ ነዉ። በርግጥ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታዉ ምክር ቤት የመፍትሔ ሐሳብና መመሪያ 2334 ተግባራዊ ይሆናልን? በሒደት የሚታይ ይሆናል። ሳዲቅ አህመድ ነኝ! ልብ ያለዉ ልብ ይበል።

የቦብ ማርሌ አደባባይና ምሥለ ቅርፅ ዕጣ ፈንታ ላይ ሊመከር ነው


ለአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ፍሰት እንቅፋት በመሆናቸው መፍረስ አለባቸው ተብለው ከተለዩት አደባባዮች መካከል አንዱ የሆነው፣ የሬጌው ሙዚቃ ንጉሥ ቦብ ማርሌ ምሥለ ቅርፅ ያረፈበትና በስሙ የሚጠራው አደባባይ ዕጣ ፈንታ ላይ ሊመከር ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማን የትራፊክ መጨናነቅ ለማቃለል ይፈርሳሉ ተብለው ከተለዩና

አድማ/በአሜሪካ~አቦንሽ/ዘፋኝዋ ከሙዚቃ እና ከንግድ የመገለልዋ-ሚስጥር! ~~ዜናነህ መኮንን~


Abonesh Adinew
አቦንሽ/ዘፋኝዋ ከሙዚቃ እና ከንግድ የመገለልዋ-ሚስጥር!
~~ዜናነህ መኮንን~
ያቦነሽ እንባ .ዋሽንግተን .ሜርላንድ እና ቨርጅንያ እንደውሃ ፈስዋል…
ምን አደረኳቸው ?ምናለ ሰርቼ ልጆቼን ባሳድግ?
አቦንሽ ታነባለች .ባጠገብዋ ያሉ የሙያ አጋሮች .ሰምተው ማዘን ነው .እንድያውም ሸሿት .ከስዋ ጋር መታየት አርጩሜውን አካል ህሊናቸው ሰጋ..
(ኢይዮጵያዊነቴ ሲያስጠቃኝ የት አል ባንዲራ ተጠምጥሞ አገሬ አገሬ የሚሉት )
ጨነቃት .ጠበባት .ብሶትዋን እንክዋ የሚሰማት በምድረ አሜሪካ በየስቴቱ (ኧረ ማልዱኝ )ጩኅትዋ በረከተ…
ከዘፈንዋ .ከክለብዋ የገባ ውግዝ የማርያም ጠላት እራሱ ወያኔ ነው ተባለ..
መንገድ ላይ የሚያውቋት እያዮ ያልፍዋትል
በደጀሰላሙም እንዲሁ .. በስልክ ደውለው (ሰላም ያላልኩሽ ታውቂው የል የውጩን ኑሮ .የሆነ ነገር ሳስብ ነው እንዴነሽ ተብሎ ወጉ ይቀጥላል )
ሰው ፈርቶ እራሱን እየዋሸ እንዲኖር አስገድደውታል .የድያስፖራ ማፍያዎች
(ወያኔ -ወያኔ ! )ስድብ ማግለያ በቃ የጭራቅነት መግለጫ ሆነ!
አቦነሽ ኧረ (ምንም የማላውቅ መሃይም ምን አድርጊ ነው የሚሉኝ) የዘወትር አባባልዋ ነው…
አንድ ቀን በጥላሁን ገሰሰ ቤት~~~
________
እግሩ ልይ ወድቃ (ጋሼ ምን አደረኳቸው
አሳደሙብኝ በኔ መዝናኛ ሰው እንዳይገባ አደረጉ
ጋሼ አሳድገኅኛል ታውቀኛለህ የት አባቴ የማውቀውን ፖለቲካ ነው?)
ጥላሁን ገሰስ .አደመጣት .ምንም ማድረግ አንደማይችል ተረዳ .አንዳድ አርቲስቶች ሙያውን ከዘመኑ ትኩሳት ጋር ቀይጠውታል
አብርዋት አዘነ…..
ጥላሁን ጥሩ አድማጭ ነው .ላውጋ ካለ ያኔውን ክስተት ከነማን ጋር የያሳለፉትን ነው
ዛሬ ጥበብ በትኩሳት ላይ ነው ሊረዳው አልቻለም ..በውስጣቸው ክፋት .ምቀኝነት ሴራ በስመ የጥበብ ሰው ሃላፊነት ሊሸከሙ የሚችሉ መኖሩን አጠራጠረው….
እቦነሽ ደጀሰልም ገብታ አሁንም ታነባለች
~ከሰው መገለል
~እዳ
~የልጆችዋና የስዋ የወደፊት እጣ
በማታውቀው የራስ ምታት እና አንጀት መኮሳተር እክብል አዘውታሪ ሆነች..
በስሜትዋ ላይ ከፍተኛ ጥቃት ደረሰ .ከምትወደው ሙዚቃ ተፋታች የሌሎችንም ስራ ማዳመጥ አቆመች.
ተደጋጋሚ መዝሙር ታደምጣለች እናም
ደጀሰላም ያዘወተረው እግርዎ ወደ ኦርቶዶክስ ዘማሪነት ጥሎ ወደማይጥለው አባትዋ ቤት ገባች..
ለምን ይህ ሁሉ አድማ?~~~
ከለታት አንድቀን አገርዋ ገብታ በዜና ማሰራጫ ቃለ መጠየቅ ሰጠች
ወደ አሜሪካ ስትመለስ .የአዲስ አበባን ለውጥ .የመኪና መንገዶች .ይህንፃዎችን (አድንቀሽ አውርተሻል )በሚል አድማ ተደረገባት
እውነት የተሰማህን በነፃነት መግለፅ አትችልም ..አቦነሽ ጥቃት ከተፈፀመባት አንድዋ ናት
የዘገባው ተልእኮ….
ዴሞክራሲን ዲፌንድ ለማድረግ ነው
የግለሰቦች መብት የሚሉ አጠገባቸው ያለን መብት መጣስ እንኳ ጥብቅና ያልቆሙ ናቸው..
በድያስፖራ…
~የዜና ማሰራጫዎች
~አክቲቪስቶች
~ድርጅቶች
~የሃይማኖት ተቋም አጠገባቸው ያለን የመብት መጣስ ትክክል አይደለም አይሉም.
ይቺ አገር .አገር ውሸት ነው~
መደምደምያ….
በአንድ ጉባየ ባደረኩት ንግግር የኛ አገር ወዳድነት አሮጌ ብልትን ለመፈተሽ ነው ያልኩበት ጊዜ አለ….
አጠገብ ያሉ በደሎች ትኩረት ይሻሉ.
ቸር ይግጠመን~
ዜናነህ መኮንን✍🏿
አድማ/በአሜሪካ~~

Egypt warns Ethiopia . ግብጽ ኢትዮጵያን አስጠነቀቀች።

#Egypt warns #Ethiopia . ግብጽ ኢትዮጵያን አስጠነቀቀች።
የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በሀገር ውስጥ የተነሳውን ህዝባቂ አመጽን ተከትሎ በተደጋጋሚ የግብጽ መንግስት እጅ አለበት ሲሉ መደመጣቸው ይታወቃል። ለዚህም የግብጽ መንግስት ምላሽ ይስጠን ሲሉ የሰነበቱ ሲሆን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ምንም መረጃ ሳትይዝ የግብጽን ስም ማጥፋቱና ታቁም ብሏል።
በካይሮ የሚኖሩ ስደተኞችን ፎቶ እያቀረቡ ግብጽ የምትረዳቸው ብሎ መናገር የአለማቀፍ ህጎችን አለማክበር ነው ሲል ያተተው መግለጫው ስደተኞች በሚኖሩበት ሀገር የራሳቸውን ፖለቲካ የማንጸባረቅ ሙሉ መብታቸው ነው ብሏል።

Tuesday, December 27, 2016

ጉራጌዎቹ የአማራ ድምጾች፡ ታላላቆቹ አሊ ሁሴንና ዶክተር ያእቆብ ኃ/ማርያም | አቻምየለህ ታምሩ

ከታች ፎቷቸው የታተሙት ሁለት የጉራጌ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን አቶ አሊ ሁሴንና ዶክተር ያእቆብ ኃይለ ማርያ ይባላሉ። ሁለቱ ደግ ሰዎች ግፍና በደል የህይወቱ አካል ለሆነው ድምጽ አልባ አማራ የእድሜ አጋሮቻቸው የሆኑት የአማራ ገበሬ ልጆች ካደረጉት በላይ በመጮህ ስለ አማራ መገደል፣ መፈናቀል፣ መሰደድ፣ ስለተፈጽመበት የዘር ማጥፋትና እልቂት አጋጣሚው በፈቀደው ቦታና ሰዓት ሁሉ ሳይታክቱ የአማራ ሙሉ ድምጽ በመሆን ድንቅ ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።

አቶ አሊ ሁሴን ካናዳ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ናቸው። የኢህአፓ ታጋይ ሳሉ «አማራ ነህ» ተብለው ሞቃዲሾ በስደት ላይ ሳሉ የአማራን ግፍና በደል ተቀብለዋል። አቶ አሊ ይህንን ግፍና በደል ዶክመንተሪ ሰርተው፤ መጽሀፍ ጽፈውና በተለያዩ ቦታዎች ንግግር በማድረግ ለአለም ሁሉ አሳውቀዋል።
እነ መለስ ዜናዊና ሌንጮ ለታ ሞቃድሾ ጽህፈት ቤት ከፍተው ኢትዮጵያን ሲያጠቁ በሲያድ ባሬዋ ሶማሊያ እስር ቤቶች ውስጥ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይና አማርኛ አስተርጓሚ ሆነውም ይሰሩ ነበር። አቶ አሊም ከደርግ እስር ሸሽተው ወደ ሶማሊያ ተሰደው ሚቃዲሾ እስር ቤት በገቡበት ወቅት በነመለስ ዜናዊና ሌንጮ ለታ ጥቆማ «አማራ ነህ» ተብለው በተለየ እስር ቤት እንዲታሰሩ ተደርገው የተፈጸመባቸውን ግፍ፤ በሌሎች «አማራ ናቸው» በተባሉ ላይ የተካሄደባቸውን አሰቃቂ ጭፍጨፋ፤ በሴት እህቶቻችን ላይ የደረሰውን ከአእምሮ በላይ የሆነ ዘግናኝ ጭካኔ ዝርዝር በሰሩት ዶክመንታሪና በመጽሀፋቸው ነግረውናል። በተለያየ ጊዜ በሰጡት ቃለ መጠይቅም አቶ አሊ ሶማሊያ ውስጥ «ሸለምቦት» በተባለ ቦታ «የአማራ» ተብሎ በተከለለው እስር ቤት ውስጥ ስለተፈጸመው ግፍ ዛሬም ድረስ ህመሙ እየተሰማቸው ይናገራሉ።
እኒህ የአማራ ባለውለታ ላለፉት ሰላሳ በላይ አመታት ስለ አማራ ሲጮሁ ኖረዋል። ከነቤተሰቦቻቸው በአማራ ላይ የተፈጸመውን ግፍና በደል ተናግረው አይደክሙም! «ኢትዮጵያዊ ነኝ» በማለታቸው «አማራ ነህ» ተብለው የደረሰባቸው ግፍና በደል የአማራ ድምጽ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል! በየተገኙበት መድረክ ሁሉ አጥንታቸው ድረስ የሚሰማቸውን የአማራ ግፍና በደል ከፍ አድርገው ይናገራሉ! በደልና ግፍ የህይወቱ ገጽታ የሆነው አማራ ይነሳ ዘንድም ከአመታት በፊት እንዲህ ሲሉ ተቀኝተዋል፤
የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ ነበረ ተረቱ፣
ምነዋ ዘንድሮ ተወጊው ሲረሳ ወጊ አለመርሳቱ፤
ከዚያም አልፎ ተርፎ የተወጊው ጉዳይ የከበደው ነገር፣
በደሉን ረስቶ የወጋውን ጩቤ ልሶ ስሞ ማደር!
ከዚህ በተጨማሪ አቶ አሊ ሐረር ውስጥ አማራ ከነነፍሱ በተጣለበት የማይሞላ ገደል ስም “እንቁፍቱ” የሚልና “ፈርዶበት አማራ!” በሚል ርዕስ አስደማሚ ግጥሞች ጽፈዋል። አቶ አሊ ዛሬም ስለ አማራ ግፍና በደል መናገራቸውን አላቆሙም። በሚኖሩበት ካናዳም የኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኞች አንድነት ኮሚቴ የሚል ማህበር መስርተው የሕሊና እስረኞች ድምጽ ናቸው።
ሌላኛው የጉራጌ ተወላጅ የአማራ ድምጽ አዲስ አበባ የሚኖሩት ታዋቂው የዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ ዶክተር ያእቆብ ኃይለ ማሪያም ናቸው። ዶክተር ያቆብ ኃይለማርያም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሩዋንዳ የተካሄደውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማስቻል አቋቁሞ በነበረው አለም አቀፍ ፍርድ ቤት ላይ በዋና አቃቤ ህግነት ያገለገሉት የአለም አቀፍ ህግ ምሁር፤ ለአገራችን ችግሮች ብዙ የመፍትሄ ሃሳቦች ያቀረቡና አሰብ የኢትዮጵያ ወደብ መሆን እንደሚገባት አለም አቀፍ ሕግን በማጣቀስ «አሰብ የማን ናት» በሚል ርዕስ መጽሃፉ አሰናድተው በአሰብ ዙሪያ ያለውን ብዢታ ያጠሩ አገር ወዳድ የህግ ሊቅ ናቸው።

“እውን የአማራው ትግል #ኢትዮጵያዊነትን_ከአማራው ውስጥ #የማጥፋት_የወያኔ_ሴራ_ነውን?” መልስ ለሰርፀ ደስታ (ከአያሌው መንበር) ሳተናው By ሳተናው

ሰርፀ ደስታ በረጅም ፅሁፉበርካታ ጉዳዮችን ነካክቶ ግንዛቤ እንይዝ ዘንድ አስነብቦናል።እንደዚህ ተንተን ያለ ፅሁፍ ምናልባትም የሰዎችን ብዥታ ወይ ያጠራዋል አልያም የፀሃፊውን ወገንተኝነት ከየት እንደሚሆን ከፅሁፉ እንድንረዳ ያስችለንና የወገነበትን አካል አቋም እንድናውቅ ይረዳናል።
(ከተነተናቸው ውስጥ ኦነግ፣ግ7፣የአማራ ህዝብ ትግል፣ ኢትዮጵያዊነት…ይገኙበታል)
ይህንን እንደመግቢያ ካልኩኝ እኔ የአማራ ትግልን የሚመለከተውን የአማራ ብሄርተኝነት ጉዳይ ግን በገባኝና በማምንበት በኩል ትንሽ ልበል።
ከሰርፀ ጋር አንድ የሚያደርገን የአማራ ህዝብ ከየትኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ የበለጠ መበደሉን ሁላችንም ማመናችን ነው።የገለፀበት መንገድ ይለያይና ቁስሉም የእኛን ያህል አይመመው እንጅ እርሱም ይህንን አልካደም።መልካም ነው።
እንግዲህ ለግልፀኝነት ይረዳ ዘንድ እኔ በገባኝ መልኩ የአማራውን ተጋድሎና የብሄርተኝነት እንቅስቃሴ ለመግለፅ ልሞክር።
ዋናው የአማራ ህዝብ ተጋድሎ መነሻም በሰነድ ጠላቴ ነህ በሚል የተዘጋጀን የአንድ መንግስት አቋም መቃወም፣ በህወሃትና ተባባሪዎቹ እየተፈፀመ ያለን የዘር እልቂት በማስቆም ህልውናንውን ማስቀጠል፣ በውሸት ታሪክ ፀሃፊያን የተፃፉ መፅሃፍትን በእውነት ፉርሽ ማደረግ፣ በፖርቲዎች የፕሮግራምና ቅስቀሳ ውይይት የሚታዩ የአማራን ህዝብ እና የቀድሞ የኢትዮጵያ መሪዎችን ወንጀለኛ የማድረግ አባዜ ስህተት መሆናቸውን ማሳየት፣ በአፈ ታሪክ እየተነገረ ያለውን መሰረት አልባ የአማራን ህዝብ እንደ ጨቋኝ የመቁጠር ውንጀላና ክስ ውድቅ አድርጎ የአማራን ህዝብ አሁን ብቻ ሳይሆን ቀደም ብሎም ያጣውን መብቱን አስከብሮ የሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እና ሌሎችም ናቸው።
ህጋዊ በሚመስል መልኩ የዘር ማጥፋት እወጃ ተደርጎበት ዘሩን ማስቀጠል እንደሌለለበትና በሂደትም ይጠፋ ዘንድ መውለድ እንኳን እንዳይችል እየተደረገ ያለ ህዝብ ማን ነው ቢባል መልሱ እጅግ ቀላል ነው።ይህንን መዋጋትም እንዳለብን ማመን አጠያያቂ አይመስለኝም።ጥያቄው የሚሆነው በየት በኩልና የትኛው ይበልጥ አዋጭ ነው የሚለው ነው።
እንደ አንድ የአማራ ወጣት ይህንን እጅግ አደገኛ የተጠና አካሄድ ማስቆም ቀርቶ መከላከል እንኳን መሞከር የሚቻለው በግለሰብ ሳይሆን ሁሉንም በስነ ልቦና ባህልና ታሪክ አማራ ነህ እየተባለ የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆነን አርሲ ያለ አማራ ከወልቃይቱ፣ የጅጅጋውን አማራ ከራያው ጋር በማስተሳሰር ወደ አንድ ጥላ ስር በማምጣት የብሄርተኝነት ስራን በመስራት እንጅ በአንድ ለአምስት በጎጥ በማደራጀት አይደለም ብየ አምናለው።ወይንም ደግሞ ስለዚህ ጉዳይ ብታወራው ፊልም የሚመስለውን ኢትዮጵያዊ በማሰባሰብ ይሳካል ብየም አላምንም።
እየተሰራ ያለው ስራ ይህ ነው ብየም አምናለው።ይህም ውጤት አምጥቷል።የአማራን ህዝብ በአንድ ጥላ ስር የማሰባሰብ የብሄርተኝነት እንቅስቃሴ ቀድሞ የተጀመረና በህወሃት የተንኮል ሴራ የከሸፈ ቢሆንም ባለፉት ሁለት አመታት ግን በተለይም አማራ በመሆናቸው ራሳቸው፣ ቤተሰቦቻቸው አልያም ጎረቤቶቻቸው እየደረሰባቸው ያለው መከራ ዕረፍት የነሳቸው ምሁራንና ወጣቶች በሰሩት ያለሰለሰ ጥረት ውስጥ ውስጡን በሀገር ቤት የመንግስት ተቋማትና በነዋሪው ዘንድ በተደረገ የእውነተኛ መረጃና ማስረጃ ማዳረስ ተግባር ባለፊት ወራቶች ለተካሄደው የአማራ ተጋድሎ ውልደት ምክንያት ሆኗል።
እናም ሰርፀ እንዳለው የአማራ ህዝብ ትግል ኢትዮጵያዊነትን የማጥፋት ወይም የጎሳ ፖለቲካን የማራመድ አባዜ ያለበት ትውልድ ስብስብ አይደለም።ይልቁንም አማራ በመሆኑ የስቃዮች ሁሉ ስቃይ የደረሰበት፤ መፍትሄውም ጠንካራ የአማራ ማህበረሰብን በመፍጠር መክቶ ጠላትን ማስወገድ ነው ብሎ የሚያምን ነው።በእርግጥ አንተ እንዳልከውና እንደምትፈልገው ኢትዮጵያ እየተባለ ሲዘፈን እምባው ከአንተ ቀድሞ የሚመጣው ላይሆን ይችላል።ምክንያቱም እኛ እየኖርንበት ባለው ሀገርና ስርዓት በልበ ሙሉነት ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ይኸው ህዝብ ሁኖ ሳለ በደሉ ለምን እዚህ ህዝብ ላይ ከፋ የሚልን ጥያቄም መጠየቅ ጀምሯልና።አንተ ደግሞ እየተገደለም፤ ዘሩም እየጠፋ ኢትዮጵያዊ ነኝ ይበል ያልክ ትመስላለህ።ይልቁንስ የዚህን ህዝብ ትግል አድማሱን አስፍቶ እንዴት በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል ማድረግ ይቻላል? የሚል ጥያቄ ብታነሳ መልካም ነው እልሃለው።
ከዚያ ውጭ ቅማንት አማራ አይደለም፣አገው አማራ አይደለም ወዘተ የሚል መሰረተ ቢስ ትርክትም አካተሃል።አዎ በደም ቆጠራ ከሄድክ ላይሆን ይችላል።እኛ የምናራምደው ግን የስነ ልቦና አብሮነት መለኪያ የጤናማ ብሄርተኝነት እንጅ አንተ እንዳልከው በዘረመል የተመሰረተ የኔጋቲቭ ብሄርተኝነት አይደለም።እንዲያውም አደጋ የሚሆነው የአማራ ስነልቦና ያለውን ህዝብ ራሱ ሳይጠይቅ እንዳንተ አይነቱ ግን ቅማንት ነህ ብሎ ሲገፋው ነው።የአማራ ህዝብ እኮ (አገው አማራ፣ ቅማንት አማራ፣አርጎባ አማራ…)አንድ ህዝብ ነን ብሎ ነው ወልቃይት ላይ የተነሳን የማንነት ጥያቄ ደግፎ ቻግኒ ላይ የሚገኝ አገው አማራ “ሞት ቢደገስልንም እልንፈራም” በማለት ወልቃይት አማራ ነው ያለው።”አንተ የአማራ ወጣት ሆይ ሞትን ብትፈራ” ….ብሎ የክብር ሰንደቁን ከፍ አድርጎ ሲያውለበልብ እኮ ነው ደብታትቦር ላይ ጀግናው የአማራ ወጣት በህወሃት ሳራዊት የተሰዋው።የባንዳነት ስራ በተደራጀ የአማራ ተጋድሎ ይከሽፋል ፤ ወልቃይት አማራ ነ ው ብሎ ስወለጣ እኮ ነው በርካታ የባህር ዳር ወጣት የጥይት ራት የሆነው።ምናልባት ፎቶና ቪዲዮ ካስፈለገም በዘርፍ በዘርፉ ላያይዝልህ እችላለው።
ሌላው ወልቃይት የጠየቀው ጎንደሬነትን እንጅ አማራነትን አይደለም (አማራጭ ስላጣ ነው ላልከው) እንግዲህ ይህንን እንዲመልሱት የምተወው ለእነ ኮሎኔል ደመቀ ይሆናል።ምክንያቱም በህይወት አሉና።እስከዚያው ግን የ13 ደቂቃ ቪዲዮ ዩቱብ ላይ ተመልከትና ህዝቡን ሲያስተምር ምን እንደሚል ተመልከተው(ለግንዛቤ እንዲህ ይላል…ባህላችን አማራ፣ቋንቋችን አማርኛ፣ስሜታችን አማራ፣ፈቃደኝነታችን ደግሞ ከአማራ ህዝብ ከጎንደር በጌምድር ጋር ነው ይላል)
እያደረግን ያለነው የአማራ ህዝብ ትግል እንጅ የአማራ ነገድ የዘረ መል ትግል አይደለም።በነገራችን ላይ አንድ ትልቁ ነገር ከዚህ በፊት አማራ የለም በማለት አማራ እንዳይሰባሰብና እንዳይደራጅ ትልቅ ስራ ሰርተው ነበር።አሁን አማራ እያለ የለም ማለታቸው አሳፋሪ መሆኑን ከታሪክ ማስረጃ እንስከ ነባራዊ ሁኔታው ሲቀርብላቸው ደግሞ የአማራውን መኖር አመኑና የአማራውን መሰባሰብ ግን የነገድ ትግል ነው በማለት አሁንም ሌላ ነገር ይዘው ብቅ አሉ።እነዚህ የህልም እንጀራን የሚጋግሩ አካላት ለእኔ ቦታ አልሰጣቸውም።ምክንያቱም ለሺህ አመታት የኖረን ህዝብ ያለምንም ማስረጃ በደረቀ ብዕሩ አማራ የሚባል ህዝብ የለም ብሎ የተነሳ አካል ዛሬ የአማራን ትግል በጤነኝነት ሊያየው የሚችል አለመሆኑ ግልፅ ነውና።ቀድሞውንም ቅን አስተሳሰብ የለውም።
ከዚህ በተረፈ ግን ኢትዮጵያን ለፈጠረ ህዝብ ኢትዮጵያዊነትን ሊያጠፋ ተነሳ ማለት ምፀትም ንቀትም ነው።አማራ የሚባል የለም የሚል አስተሳሰብ ተገዥ የሆነ ደቀመዝሙር ለእኔና መሰሎቸ ኢትዮጵያዊነትን ሊያስረዳኝ አይችልምና።ይልቅስ ኢትዮጵያን የመሰረተ ህዝብ ዛሬ አደጋ ተጋርጦበታልና ይህንን ህዝብ ታድገን እንዴት ሀገራችን እንታደጋት የሚለው ቁልፍ ጥያቄ ነው።በዚህ መስመር ካልመጣችሁ ከመንገዳችን ዘውር በሉ ነው እያልን ያለነው።
በዚህ መሰረት ፀሃፊው በርካታ ጉዳዮችን በገባውና በሚያምንበት ዘርዝሯል።የኦነግን የኦሮሞ እንቅስቃሴና ኢትዮጵያዊነትን፣ የግንቦት 7ን ሀገር ውስጥ ገብቶ አለመታገል እና የአማራን ህዝብ ትግል ዳስሷል።የፀሃፊው በግ7 ጠንካራ ትችቶችን አልሰነዘረም።ለምን።በክረምቱ የአማራ ትግል ሀገር ቤት አልገባም? ብሎ ነው ያለፈው።ግን ኦነግን እንደተቸው ሁሉ ብዙ መሞገቻ ሀሳብ ማንሳት ይገባው ነበር።ህወሃት ላይም እንዲሁ።በሌላ በኩል የአማራን ትግል ከኦነግ የተገንጣይነት አስተሳሰብ ጋር እኩል በተመሳሳይ ጎን ለጎን የሚሄድ አስመስሎ ነው ያቀረበው።ስለዚህ የግለሰቡን ፅሁፍ ባከብረውም መነሻውና መድረሻው ግን ኢትዮጵያን መታደግ አይደለም ብየ እንድገመግም እገደዳደለው።
አንድ ሚዛናዊ ህሊና ያለው ሰው የአማራን ህዝብ ትግል ከኦነግ አስተሳሰብ ጋር ሊያገናኘው አይችልም።ሁለቱ እጅግ የተለያዩና ተፃራሪም ናቸውና።የአማራ ትግል የኦነግን የትግል መስመር ብቻ ሳይሆን ኦነግን ራሱንም ይታገለዋልና።ምክንያቱም ኦነግም፣ ሻዕቢያም እንደ ህወሃት አማራ ላይ የራሳቸው ያሳረፉት ዘመን ተሻጋሪ ጠባሳ እና የተጣመመ እይታ አላቸውና።የአማራ ህዝብ ትግል (አማራ ተጋድሎ) በወያኔ እንደሚመራ ወይም የወያኔ አጀንዳ ነው ለማለት ወይም ኢትዮጵያዊነትን ይፃረራል ለማለት መጀመሪያ የአማራን ህዝብ ትግል ምንነት ማወቅ ይጠይቃል።በእርግጥ ፀሀፊው ይህ ጠፍቶት አይመስለኝም።
ለማንኛውም በዚህ ሰዓት ለኢትዮጵያዊው አማራ ኢትዮጵያዊነትን ማስተማር ሳይሆን የሚቀድመው አደጋ ውስጥ ላለው ለኢትዮጵያ ፈጣሪው አማራ እንዴት እንድረስለት የሚለው ነው።
(በነገራችን ላይ እንዲያው የተሰማኝን ለመግለፅ እንጅ ለአማራ ወጣት ታሪካዊ ሰንደቅ አላማውን ይዞ እየሞተ ላለ ህዝብ ኢትዮጵያዊነትን ለማስተማር የሞራል ብቃት የለኝም።ሌላውም እዚህ ላይ ጊዜ ባያጠፋ እመክራለው)
ድል ለአማራ ህዝብ ሞት ለጠላቶቹ!!!
ቸር ይግጠመን

እውን የአማራው ትግል ‘ኢትዮጵያዊነትን ከአማራው ውስጥ የማጥፋት’ የወያኔ ሴራ ነውን? መልስ ለሰርፀ ደስታ – (ከአያሌው መንበር)

(ከተነተናቸው ውስጥ ኦነግ፣ግ7፣የአማራ ህዝብ ትግል፣ ኢትዮጵያዊነት…ይገኙበታል)
ይህንን እንደመግቢያ ካልኩኝ እኔ የአማራ ትግልን የሚመለከተውን የአማራ ብሄርተኝነት ጉዳይ ግን በገባኝና በማምንበት በኩል ትንሽ ልበል።
ከሰርፀ ጋር አንድ የሚያደርገን የአማራ ህዝብ ከየትኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ የበለጠ መበደሉን ሁላችንም ማመናችን ነው።የገለፀበት መንገድ ይለያይና ቁስሉም የእኛን ያህል አይመመው እንጅ እርሱም ይህንን አልካደም።መልካም ነው።
እንግዲህ ለግልፀኝነት ይረዳ ዘንድ እኔ በገባኝ መልኩ የአማራውን ተጋድሎና የብሄርተኝነት እንቅስቃሴ ለመግለፅ ልሞክር።
ዋናው የአማራ ህዝብ ተጋድሎ መነሻም በሰነድ ጠላቴ ነህ በሚል የተዘጋጀን የአንድ መንግስት አቋም መቃወም፣ በህወሃትና ተባባሪዎቹ እየተፈፀመ ያለን የዘር እልቂት በማስቆም ህልውናንውን ማስቀጠል፣ በውሸት ታሪክ ፀሃፊያን የተፃፉ መፅሃፍትን በእውነት ፉርሽ ማደረግ፣ በፖርቲዎች የፕሮግራምና ቅስቀሳ ውይይት የሚታዩ የአማራን ህዝብ እና የቀድሞ የኢትዮጵያ መሪዎችን ወንጀለኛ የማድረግ አባዜ ስህተት መሆናቸውን ማሳየት፣ በአፈ ታሪክ እየተነገረ ያለውን መሰረት አልባ የአማራን ህዝብ እንደ ጨቋኝ የመቁጠር ውንጀላና ክስ ውድቅ አድርጎ የአማራን ህዝብ አሁን ብቻ ሳይሆን ቀደም ብሎም ያጣውን መብቱን አስከብሮ የሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እና ሌሎችም ናቸው።
ህጋዊ በሚመስል መልኩ የዘር ማጥፋት እወጃ ተደርጎበት ዘሩን ማስቀጠል እንደሌለለበትና በሂደትም ይጠፋ ዘንድ መውለድ እንኳን እንዳይችል እየተደረገ ያለ ህዝብ ማን ነው ቢባል መልሱ እጅግ ቀላል ነው።ይህንን መዋጋትም እንዳለብን ማመን አጠያያቂ አይመስለኝም።ጥያቄው የሚሆነው በየት በኩልና የትኛው ይበልጥ አዋጭ ነው የሚለው ነው።
እንደ አንድ የአማራ ወጣት ይህንን እጅግ አደገኛ የተጠና አካሄድ ማስቆም ቀርቶ መከላከል እንኳን መሞከር የሚቻለው በግለሰብ ሳይሆን ሁሉንም በስነ ልቦና ባህልና ታሪክ አማራ ነህ እየተባለ የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆነን አርሲ ያለ አማራ ከወልቃይቱ፣ የጅጅጋውን አማራ ከራያው ጋር በማስተሳሰር ወደ አንድ ጥላ ስር በማምጣት የብሄርተኝነት ስራን በመስራት እንጅ በአንድ ለአምስት በጎጥ በማደራጀት አይደለም ብየ አምናለው።ወይንም ደግሞ ስለዚህ ጉዳይ ብታወራው ፊልም የሚመስለውን ኢትዮጵያዊ በማሰባሰብ ይሳካል ብየም አላምንም።
እየተሰራ ያለው ስራ ይህ ነው ብየም አምናለው።ይህም ውጤት አምጥቷል።የአማራን ህዝብ በአንድ ጥላ ስር የማሰባሰብ የብሄርተኝነት እንቅስቃሴ ቀድሞ የተጀመረና በህወሃት የተንኮል ሴራ የከሸፈ ቢሆንም ባለፉት ሁለት አመታት ግን በተለይም አማራ በመሆናቸው ራሳቸው፣ ቤተሰቦቻቸው አልያም ጎረቤቶቻቸው እየደረሰባቸው ያለው መከራ ዕረፍት የነሳቸው ምሁራንና ወጣቶች በሰሩት ያለሰለሰ ጥረት ውስጥ ውስጡን በሀገር ቤት የመንግስት ተቋማትና በነዋሪው ዘንድ በተደረገ የእውነተኛ መረጃና ማስረጃ ማዳረስ ተግባር ባለፊት ወራቶች ለተካሄደው የአማራ ተጋድሎ ውልደት ምክንያት ሆኗል።
እናም ሰርፀ እንዳለው የአማራ ህዝብ ትግል ኢትዮጵያዊነትን የማጥፋት ወይም የጎሳ ፖለቲካን የማራመድ አባዜ ያለበት ትውልድ ስብስብ አይደለም።ይልቁንም አማራ በመሆኑ የስቃዮች ሁሉ ስቃይ የደረሰበት፤ መፍትሄውም ጠንካራ የአማራ ማህበረሰብን በመፍጠር መክቶ ጠላትን ማስወገድ ነው ብሎ የሚያምን ነው።በእርግጥ አንተ እንዳልከውና እንደምትፈልገው ኢትዮጵያ እየተባለ ሲዘፈን እምባው ከአንተ ቀድሞ የሚመጣው ላይሆን ይችላል።ምክንያቱም እኛ እየኖርንበት ባለው ሀገርና ስርዓት በልበ ሙሉነት ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ይኸው ህዝብ ሁኖ ሳለ በደሉ ለምን እዚህ ህዝብ ላይ ከፋ የሚልን ጥያቄም መጠየቅ ጀምሯልና።አንተ ደግሞ እየተገደለም፤ ዘሩም እየጠፋ ኢትዮጵያዊ ነኝ ይበል ያልክ ትመስላለህ።ይልቁንስ የዚህን ህዝብ ትግል አድማሱን አስፍቶ እንዴት በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል ማድረግ ይቻላል? የሚል ጥያቄ ብታነሳ መልካም ነው እልሃለው።
ከዚያ ውጭ ቅማንት አማራ አይደለም፣አገው አማራ አይደለም ወዘተ የሚል መሰረተ ቢስ ትርክትም አካተሃል።አዎ በደም ቆጠራ ከሄድክ ላይሆን ይችላል።እኛ የምናራምደው ግን የስነ ልቦና አብሮነት መለኪያ የጤናማ ብሄርተኝነት እንጅ አንተ እንዳልከው በዘረመል የተመሰረተ የኔጋቲቭ ብሄርተኝነት አይደለም።እንዲያውም አደጋ የሚሆነው የአማራ ስነልቦና ያለውን ህዝብ ራሱ ሳይጠይቅ እንዳንተ አይነቱ ግን ቅማንት ነህ ብሎ ሲገፋው ነው።የአማራ ህዝብ እኮ (አገው አማራ፣ ቅማንት አማራ፣አርጎባ አማራ…)አንድ ህዝብ ነን ብሎ ነው ወልቃይት ላይ የተነሳን የማንነት ጥያቄ ደግፎ ቻግኒ ላይ የሚገኝ አገው አማራ “ሞት ቢደገስልንም እልንፈራም” በማለት ወልቃይት አማራ ነው ያለው።”አንተ የአማራ ወጣት ሆይ ሞትን ብትፈራ” ….ብሎ የክብር ሰንደቁን ከፍ አድርጎ ሲያውለበልብ እኮ ነው ደብታትቦር ላይ ጀግናው የአማራ ወጣት በህወሃት ሳራዊት የተሰዋው።የባንዳነት ስራ በተደራጀ የአማራ ተጋድሎ ይከሽፋል ፤ ወልቃይት አማራ ነ ው ብሎ ስወለጣ እኮ ነው በርካታ የባህር ዳር ወጣት የጥይት ራት የሆነው።ምናልባት ፎቶና ቪዲዮ ካስፈለገም በዘርፍ በዘርፉ ላያይዝልህ እችላለው።
ሌላው ወልቃይት የጠየቀው ጎንደሬነትን እንጅ አማራነትን አይደለም (አማራጭ ስላጣ ነው ላልከው) እንግዲህ ይህንን እንዲመልሱት የምተወው ለእነ ኮሎኔል ደመቀ ይሆናል።ምክንያቱም በህይወት አሉና።እስከዚያው ግን የ13 ደቂቃ ቪዲዮ ዩቱብ ላይ ተመልከትና ህዝቡን ሲያስተምር ምን እንደሚል ተመልከተው(ለግንዛቤ እንዲህ ይላል…ባህላችን አማራ፣ቋንቋችን አማርኛ፣ስሜታችን አማራ፣ፈቃደኝነታችን ደግሞ ከአማራ ህዝብ ከጎንደር በጌምድር ጋር ነው ይላል)
እያደረግን ያለነው የአማራ ህዝብ ትግል እንጅ የአማራ ነገድ የዘረ መል ትግል አይደለም።በነገራችን ላይ አንድ ትልቁ ነገር ከዚህ በፊት አማራ የለም በማለት አማራ እንዳይሰባሰብና እንዳይደራጅ ትልቅ ስራ ሰርተው ነበር።አሁን አማራ እያለ የለም ማለታቸው አሳፋሪ መሆኑን ከታሪክ ማስረጃ እንስከ ነባራዊ ሁኔታው ሲቀርብላቸው ደግሞ የአማራውን መኖር አመኑና የአማራውን መሰባሰብ ግን የነገድ ትግል ነው በማለት አሁንም ሌላ ነገር ይዘው ብቅ አሉ።እነዚህ የህልም እንጀራን የሚጋግሩ አካላት ለእኔ ቦታ አልሰጣቸውም።ምክንያቱም ለሺህ አመታት የኖረን ህዝብ ያለምንም ማስረጃ በደረቀ ብዕሩ አማራ የሚባል ህዝብ የለም ብሎ የተነሳ አካል ዛሬ የአማራን ትግል በጤነኝነት ሊያየው የሚችል አለመሆኑ ግልፅ ነውና።ቀድሞውንም ቅን አስተሳሰብ የለውም።
ከዚህ በተረፈ ግን ኢትዮጵያን ለፈጠረ ህዝብ ኢትዮጵያዊነትን ሊያጠፋ ተነሳ ማለት ምፀትም ንቀትም ነው።አማራ የሚባል የለም የሚል አስተሳሰብ ተገዥ የሆነ ደቀመዝሙር ለእኔና መሰሎቸ ኢትዮጵያዊነትን ሊያስረዳኝ አይችልምና።ይልቅስ ኢትዮጵያን የመሰረተ ህዝብ ዛሬ አደጋ ተጋርጦበታልና ይህንን ህዝብ ታድገን እንዴት ሀገራችን እንታደጋት የሚለው ቁልፍ ጥያቄ ነው።በዚህ መስመር ካልመጣችሁ ከመንገዳችን ዘውር በሉ ነው እያልን ያለነው።
በዚህ መሰረት ፀሃፊው በርካታ ጉዳዮችን በገባውና በሚያምንበት ዘርዝሯል።የኦነግን የኦሮሞ እንቅስቃሴና ኢትዮጵያዊነትን፣ የግንቦት 7ን ሀገር ውስጥ ገብቶ አለመታገል እና የአማራን ህዝብ ትግል ዳስሷል።የፀሃፊው በግ7 ጠንካራ ትችቶችን አልሰነዘረም።ለምን።በክረምቱ የአማራ ትግል ሀገር ቤት አልገባም? ብሎ ነው ያለፈው።ግን ኦነግን እንደተቸው ሁሉ ብዙ መሞገቻ ሀሳብ ማንሳት ይገባው ነበር።ህወሃት ላይም እንዲሁ።በሌላ በኩል የአማራን ትግል ከኦነግ የተገንጣይነት አስተሳሰብ ጋር እኩል በተመሳሳይ ጎን ለጎን የሚሄድ አስመስሎ ነው ያቀረበው።ስለዚህ የግለሰቡን ፅሁፍ ባከብረውም መነሻውና መድረሻው ግን ኢትዮጵያን መታደግ አይደለም ብየ እንድገመግም እገደዳደለው።
አንድ ሚዛናዊ ህሊና ያለው ሰው የአማራን ህዝብ ትግል ከኦነግ አስተሳሰብ ጋር ሊያገናኘው አይችልም።ሁለቱ እጅግ የተለያዩና ተፃራሪም ናቸውና።የአማራ ትግል የኦነግን የትግል መስመር ብቻ ሳይሆን ኦነግን ራሱንም ይታገለዋልና።ምክንያቱም ኦነግም፣ ሻዕቢያም እንደ ህወሃት አማራ ላይ የራሳቸው ያሳረፉት ዘመን ተሻጋሪ ጠባሳ እና የተጣመመ እይታ አላቸውና።የአማራ ህዝብ ትግል (አማራ ተጋድሎ) በወያኔ እንደሚመራ ወይም የወያኔ አጀንዳ ነው ለማለት ወይም ኢትዮጵያዊነትን ይፃረራል ለማለት መጀመሪያ የአማራን ህዝብ ትግል ምንነት ማወቅ ይጠይቃል።በእርግጥ ፀሀፊው ይህ ጠፍቶት አይመስለኝም።
ለማንኛውም በዚህ ሰዓት ለኢትዮጵያዊው አማራ ኢትዮጵያዊነትን ማስተማር ሳይሆን የሚቀድመው አደጋ ውስጥ ላለው ለኢትዮጵያ ፈጣሪው አማራ እንዴት እንድረስለት የሚለው ነው።ድል ለአማራ ህዝብ