Sunday, October 30, 2016

በአማራና በቅማንት ሕዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር ወያኔ መርዛም ፕሮፓጋንዳውን እየረጨ ነው።


በአማራና በቅማንት ሕዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር ወያኔ መርዛም ፕሮፓጋንዳውን እየረጨ ነው።
ምንሊክ ሳልሳዊ :- በኣማራ ክልል የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ኣጣብቂኝ ውስጥ የገባው የሕወሓት ኣገዛዝ በውማራና በቅማንት ሕዝቦች መካከል ግጭት በመፍጠር በመሃል ሰርጎ ገብቶ ኣማራውን ለመፍጀት የሚያስችለውን እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጉዳዩን በቅርበት ያዩ የኣይን እማኞች ገልጸዋል።
የሕወሓት ካድሬዎች ኮሌኔል ደመቀ የአማራን ጦር እየመራ የቅማንትን ህዝብ ሊያስጨፈጭፍ የነበረ ጠላት እንደነበር ለቅማንቶች እየነገሩ ሃሰተኛ መርዝ በመርጨት ኣርሶ ኣደሩን እያታለሉ እደሚገኙ በቦታው ደርሰው መርዘኛ ፕሮፓጋንዳው የሰሙ ተናግረዋል።እማኞቹ እንዳሉት ተመሳሳይ ስራዎችንም በጎንደር ዙሪያ ባሉ የቅማንት ማህበረሰብ በብዛት ባሉባቸው ቀበሌወች እንዲሁም በቆላማ ስፍራወች ጭምር አርሶ አደሩን ታርጌት አድርገው ቅስቀሳቸውን አጧጡፈውታል። የሕዝቦች ኣንድነት የሚያስበረግገው ወያኔ የሚረጨውን ክፉና ከፋፋይ ኣደገኛ መርዝ ለማክሸፍ እያንዳንዱ የኣከባቢው ተወላጅ የበኩሉን ሚና መጫወት ኣለበት ሲሉ እማኞቹ ተናግረዋል። (ምንሊክ ሳልሳዊ)

No comments:

Post a Comment