Tuesday, May 31, 2016

እነ ብርሀኑ ተ/ያሬድ ያለቀጠሮአቸው ተገደው ፍርድ ቤት ቀረቡ


–ፍርድ ቤቱ የተክሳሽኦችን የመክላክያ ምስክሮች በምን ጭብጥ ላይ እንደሚመስክሩ ከምስክሮቹ ቀጠሮ አስቀድሞ እንዲገለፅ ጠይቃል
–ተከሳሾቹ ግርድ ቤቱን እና ማረሚያ ቤት ህገወጥ ጫናና ወከባ እየፈጠሩብን ነው ብለዋል
የክስ መዝገባቸው በከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት በመታየት ላይ የሚገኘው 4 ተከሳሾች ብርሀኑ ፤እየሩሳሌም፤ፍቅረማርያም እና ደሴ ፍርድ ቤቱ እንዲከላከሉ ብይን በሰጠባቸው ጉዳዮ ላይ የመከላከያ ምስክር ለማቅረብ ከግንቦት 30-ሰኔ 8 ክትሮ ተይዞላቸው የነበረ ቢሆንም ዛሬ ግንቦት 23 ቀን ያለቀጠሮዋቸው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተደርጋል
ተከሳሾቹ ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሌላቸው ለማረሚያ ቤቱ ሀላፊዎች የገለፁ ቢሆንም በማረሚያ ቤቱ የጥበቃ ሃላፊዎች ወከባና ግፍተራ እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችላል ተከሳሾቹ ፍርድ ቤት ከቀረቡም በሀላም ለፍርድ ቤቱ ይህንን ያስረዱ ሲሆን የፍርድ ቤቱም ዳኛም “ዛሬ ቀጠሮ ባይኖራችሁም ፍርድ ቤቱ ማጣራት ያለበት ጉዳይ ስላለ ነው የጠራናችሁ”በማለት የተከሳሾቹ መከላከያ ምስክሮች የሚመሰክሩበትን ጭብጥ ተከሳሾቹ ዛሬ ለፍርድ ቤቱ እንዲያስረዱ ጠይቀዋል ተከሳሾቹም ምስክሮቻቻ  ሚመስክሩበጽን ጭብ ጥ ምስክር ነጽ በሚሸፅበጽ እለት እንጂ ምስክሮቹ ከመቅረባቸው አስቀድሞ ለፍርድ ቤቱ የማሳወቅ ህጋዊ ግዴታ የሌለባቸው መሆኑን የገለፀ ሲሆን ዛሬ በፍርድ ቤቱ እየተጠየቁ ያለው ቅድመ ሁኔታ ግን ህጋዊ መሰረት የሌለው እና ፍርድ ቤቱም የሌሎች የገዢው ፓርቲ የአፈና መዋቅርት ተፅእኖ እንዳረፈበት የሚያሳይ ነው ብለዋል.
ተከሳሾቹ አያይዘው እንደገለፁትም ለምስክሮች የተዘጋጀው መጥሪያ በፍርድ ቤቱ ዳኛ ተፈርሞ ለምስክሮቻቸው እንዲሰጥ ማረሚያ በት ለሚገኙ ተከሳሾች ከደረሳቸው በሀላ በድጋሚ “በፍርድ ቤት ትእዛዝ ነው” በሚል ምክንያት መጥሪያዎቹን የተነጠቁ ሲሆን በማረሚያ ቤቱ ሀላፊዎች በኩልም መከላከያ ምስክሮቻቸውን በተመለከተ በተለይም የገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ባለስልጣናት ለምስክርነት ማስጠራታቸውን ተከትሎ ማስፈራርያና ወከባ እየደረሰባቸው ነው በመጨረሻም ተከሳሾቹ የምስክሮቻቸውን ጭብጥ ለፍርድ ቤቱ እንደማያሳውቁ በአፅንኦት የገለፁ ሲሆን የፍርድ ቤቱ ዳኛ “ከአነጋገራችሁ የምስክሮቹን ጭብጥ ለመረዳት ጭለናል በመሆኑም ይህኑኑ ጉዳይ መርምረን ለግንቦት 30-2008 ብይን እንሰጥበታለነረ “ በማለት ተከሳሾቹን በተጠቀሰው ቀን እንዲርቡ ትእዛዝ ሰጥተዋል::

በምስራቅ ጎጃም ጎዛምን ወረዳ አራት ሰው ተገደለ!! አደገኛ ውጥረት እንደነገሰ የአካባቢው ሰዎች ገለፁ፡፡


በምስራቅ ጎጃም ጎዛምን ወረዳ አራት ሰው ተገደለ!! አደገኛ ውጥረት እንደነገሰ የአካባቢው ሰዎች ገለፁ፡፡
በምስ/ጎጃም ጎዛምን ወረዳ ደንበል ቀበሌ ትላንት ግንቦት22/09/08 ዓ ም መለስተኛ የጦር ግንባር ሆኖ አረፈደ የወረዳው የፖሊስ ደህንነት ጨምሮ ሁለት ሚሊሻ የሞቱ ሲሆን ገዳዩም እራሱን አጠፋ ሲሉ ከወደ ጎጃም የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡===//

ቀደም ባለ ጊዜ የመከላኪያ ሰራዊት አባል በመሆን ለ14አመት ሲያገለግል የቆየው እና በራሱ ፍቃድ ከነበረበት ኃላፊነት የለቀቀው አቶ ይሄነው ትርፌ ምክንያቱ በውል ሳይታወቅ በትላንትናው ዕለት ግንቦት 22/09/08/ዓ ም ከጠዋቱ 1ሰዓት መኖሪያ ቤቱ በወረዳው ፖሊስ ደህንነት እና ሁለት በታጠቁ የሚሊሻ አባሎች ተከቦ እጅ እንዲሰጥ ቢጠየቅም የለም-አይሆንም! አላደርገውም! ያለው አቶ ይሄነው ትርፌ በያዘው መሳሪያ ጦርነት ተከፍቶ እስከ እረፋዱ 6ሰዓት በቶክስ እሩምታ ጎዛምን ስትናወጥ አረፈደች በማለት የሚገልፁት የአካባቢው እማኞች የወረዳው ፖሊስ አዛዥ አቶ ግዛቸው ጨምሮ የሚሊሻ አባሉ አቶ ገደፋው ቢያዘኝ እንዲሁም ልጅ አየነ የተባሉት ታጣቂዎች ለሕልፈተ ሕይወት የተዳረጉ ሲሆን የሶስቱን መሳሪያ የጨበጠው አቶ ይሄነው ትርፌ በመጨረሻም እራሳቸውን በያዙት መሳሪያ እንዳጠፉ ከአካባቢው የአይን እማኞች በደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከጥቂት ሰዓት በኃላ ተጨማሪ ኃይል በቦታው ቢደርስም አራቱም ሰዎች በሕይወት አልነበሩም፡፡ በዚህ ወቅት አንድ ወታደር በሞተው አቶ ይሄነው ትርፌ ላይ ሁሉት ጥይት መተኮሱ ሁኔታ ያስገርማል ሲሉ የመረጃው ምንጭ ይናገራሉ፡፡ ጎዛምን በአሁኑ ሰዓት ውጥረት መኖሩ ስጋት ፈጥሮባቸው ይገኛል፡፡
Sintayehu Chekol
Hanan Ahmed's photo.

የዘመናዊ ባርነት ኑሮን ይገፋሉ ተብለው የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 411 ሺህ 600 ያህል ደርሷል፡፡


ዎክ ፍሪ ፋውንዴሽን የተባለው አለማቀፍ ተቋም፣ በ167 የዓለማችን አገራት ላይ ያደረገው ጥናት እንደሚለው፣ በዚህ አመት የዘመናዊ ባርነት ኑሮን ይገፋሉ ተብለው የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 411 ሺህ 600 ያህል ደርሷል፡፡
ከሰሃራ በታች ካሉ አገራት የዘመናዊ ባርነት ሰለቦች የሆኑ በርካታ ዜጎች ያሏት ቀዳሚዋ አገር ናይጀሪያ ናት – 875 ሺህ ዜጎቿን ባሪያ በማድረግ፡፡
ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ በ873 ሺህ 100 ሁለተኛ ስትሆን…
እኛ በ411 ሺህ 600 ባሪያዎች፣ ከአለም ሰላሳኛ ከአፍሪካ ሶስተኛ ሆነናል!..

የወያኔው አቶ ኢዜአ ከሞሮኮ የከብቶች ፎቶግራፍ ሲስርቅ ተያዘ:: ስርቆቱ በየአቅጣጫው ቀጥሏል።


ስርቆቱ በየአቅጣጫው ቀጥሏል።
እነዚህ ከታች የምትመለከቷቸው ወዛም ድልብ ከብቶች ከዘጠኝ ወራት በፊት ሞሮኮዋዊ ፕሮፌሰር አድናን ረማል ለቀንድ ከብቶች ጤንነት ለሚያደርግው ጥረት 100 ሺህ ዶላር ሽልማት ሲሸለም http://goo.gl/Z9fdds ድረ ገጽ ላይ የታዩ ናቸው። …ይሁንና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በወላይታ ሶዶ ዞን ገበሬዎች የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን በመጠቀማቸው ህይወታቸው ተቀየረ ሲል ይህንኑ ፎቶ ገጭ አድርጎታል። http://goo.gl/63cNvD ~> ስለ ስርቆት ለማውራት ቅድሚያ የራስን እጅ ማጥራት! – የትነበርክታደለ

በእርስ በርስ ጦርነት ድል ሃያ አምስት ዓመት ፉከራ


ይገረም አለሙ
Ginbot 20, 25th anv. ግንቦት 20፣ 25ኛ ዓመት
በእርስ በርስ ጦርነት ከሁለቱም ወገን የሚሞተው የአንድ ሀገር ልጅ ነው። አባትና ልጅ፤ ወንድምና ወንድም ከዛና ከዚህ ተሰልፈው የሚገዳደሉበት አጋጣሚም ይኖራል። ይህም በ17 ዓመቱ የርስ በርስ ጦርነት በግልጽ ታይቷል። ወያኔዎች ለድል የበቁት የኢትዮጵያን ሠራዊት ብቻ ሳይሆን ደርግን ተቃውመው ብረት

ከብጹዐን ጳጳሳት በቀር ካህናትና ቆሞሳት እንኳን የማይገቡበት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የመንግሥት ተወካይ እንዲገኝበት መጋበዙ የደረስንበትን የውርደት ደረጃ የሚያሳየን ነው፡፡

‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› ማለት ሊቀር ነውን? .. ዲ/ን ዳንኤል ክብረት……..
ቅዱስ ሲኖዶስ የፓትርያርኩን እንደራሴ ሹመት በተመለከተ ለመወያት የያዘው አጀንዳ የመንግሥት ተወካይ ባለበት እንዲታይ መወሰኑን ዛሬ ጠዋት ሰማን፡፡ ከብጹዐን ጳጳሳት በቀር ካህናትና ቆሞሳት እንኳን የማይገቡበት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ አማኝ ይሁን ኢአማኒ፣ ሙስሊም ይሁን ክርስቲያን የማይታወቅ የመንግሥት ተወካይ እንዲገኝበት መጋበዙ የደረስንበትን የውርደት ደረጃ የሚያሳየን ነው፡፡
በአንድ በኩል የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ወሳኝ አካል መሆኑን ስናስበው፤ በሌላ በኩል የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የሚደረገው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ነው፤ ውሳኔውም በሐዋርያት ሥራ እንደተገለጠው ‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› የሚባልበት ነው(የሐዋ. 15፣29) የሚለውን ስናየው ‹የመንግሥት ተወካይ ይኑርልን› የሚለውን ውሳኔ ኢሃይማኖታዊ ነው ያሰኘዋል፡፡ ለአንድ የሲኖዶስ ጉባኤ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት አልበቃው ብሎ ነው የመንግሥትን ተወካይ የሚጋብዘው? ‹ሱባኤ ይዘን፣ ጸሎት አድርገን፤ አንድ ገዳም ወርደን፣ ከእግዚአብሔር ጋር መክረን› አይደለም ይሉን አባቶቻችን፡፡ ‹የመንግሥትን ተወካይ ጋብዘን› ነው ያሉን፡፡ እንዲያውም ቀኖናው የሊቀ ጳጳሳቱ(ፓትርያርኩ) ጉዳይ ሲታይ ‹በመቀመጫቸው መካከል አንድ ወንበር አስቀምጠው፣ ቅዱስ ወንጌሉን በዚያ ላይ አኑረው፣ ሊቀ ጳጳሳቱ በፊታቸው ተቀምጦ፣ አንድነት ተነሥተው በሩን ዘግተው ይጸልዩ፤ የተሰበሰቡበትንም ጉዳይ በሥውር(በኅቡእ) ይመርምሩ› ነው የሚለው(ፍ.ነ. ዐ.168)፡፡ እንዴት ተደርጎ ነው የመንግሥት ተወካይ ባለበት የሚታየው? አግዚአብሔር ያየናል የሚለው ጠፍቶ ታዛቢ ቢያስፈልግ እንኳን የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ለታዛቢነት አይበቁም? ቅዱስ ጳውሎስ ‹በወንድሞች መካከል ሽማግሌ ሊሆን የሚችል አንድ አስተዋይ ሰው በእናንተ ዘንድ አይገኝምን?› (1ኛቆሮ. 6፣5) ያለው ለዚህ ጊዜ አይሆነንም?
በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ የመንግሥት ተወካይ እንዲገኝ መጋበዙ በአንድ በኩል የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና የሚነካ በሌላ በኩልም ሕገ መንግሥቱን የሚጥስ፤ በመጨረሻም ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የሚያፈርስ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ያለ ማንም ጣልቃ ገብነትና ታዛቢነት የራስዋን ጉዳዮች በራስዋ ሕግጋት፣ ቀኖናና ሥርዓት መሠረት የመወሰን መብት አላት፡፡ አባቶቻችን ከንጉሥ ሐርቤ ዘመን ጀምረው ከግብጽ ሲኖዶስ ጋር ሲሟገቱ የኖሩት ይህን ሉዐላዊነት ለቤተ ክርስቲያናቸው ለማስገኘት ነው፡፡ ጳጳሳትን ለማግኘት የግብጽ ሡልጣኖች መለማመጥ፣ የግብጽንም ፓትርያርኮች መለመን ሰልችቷቸው፡፡ ከግብጽ ቀድማ ክርስትናና የተቀበለች ሀገር፣ የራስዋን ጉዳይ ለመወሰን አለመቻሏ አስደናቂ ስለሆነባቸው፡፡ ከቤተ ክርስቲያንዋ ታላቅነትና ከሀገሪቱ ክብር ጋር ስላልተመጣጠነላቸው፡፡
ዛሬ ያ ሁሉ ተረስቶ መንግሥትን በገዛ ፈቃዳቸው ‹አንተ በመካከላችን ካልተገኘህ አንሰበሰብም› የሚሉ አባቶች መጡ፡፡ ቀደምት አበው ‹አንተ ከኛ ጋር ሁን› የሚሉት ፈጣሪያቸው ነበር፡፡ ዘመን ተቀየረ፡፡ በቀደመው ጊዜ ‹መንግሥት ለምን በጉዳያችን ውስጥ ይገባል?› ነበር ክርክሩ፡፡ ‹አሁን መንግሥት ከሌለ ይህንን አጀንዳ አናይም› የሚባልበት ዘመን ላይ ደረስን፡፡ የፓትርያርክ እንደራሴ ጉዳይ የሃይማኖት ጉዳይ ነው፡፡ እንደራሴውም የሚፈጽመው ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ነው፡፡ የሥልጣን ክልሉም በቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን ክልል ነው፡፡ ታድያ ለምንድን ነው መንግሥት ያስፈለገው? ይህንን ጥያቄ ፓትርያርኩ ጠይቀውት ይሆናል፡፡ እንደመከራከሪያ ቢያቀርቡት አይገርምም፤ ቢያሳዝንም፡፡ የምልዐተ ጉባኤው መቀበል ግን ሕመም ነው፡፡
መንግሥትስ ቢሆን ምን ብሎ ነው ተወካይ የሚልከው? ምናልባት ‹ጠሩኝ፣ ሄድኩ› ካላለ በቀር፡፡ ሕገ መንግሥታችን መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ በግልጽ እየደነገገ እንዴት አድርጎ ነው በቀኖናዊ ስብሰባ ላይ የሚገኘው? ውሳኔውንስ ከየትኞቹ የቀኖና መጻሕፍት ጋር ሊያገናዝብ ነው? በጉባኤው የሚኖረውስ ሚና ምን ሊሆን ነው? ምን ዓይነት ወኪልስ ነው የሚወክለው? በየትኛው ሥልጣንና ሕግ ነው የሚገኘው? የዚህ ዓይነቱ አሠራርስ መጨረሻው ምን ይሆናል? በጉባኤው ላይ የሚተላለፈው ውሳኔ የማን ውሳኔ ነው? ‹የእኛና መንፈስ ቅዱስ› ወይስ ‹የእኛና የመንግሥት›? መንግሥትም ጉዳዩን ሊያስብበት ይገባል፤ ‹ሲጠሩት አቤት› ሳይሆን ‹ሲጠሩት ለምን?› መሆን አለበት፡፡
የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ኤጲስ ቆጶስ በዚህ ዓለም መኳንንት ርዳታ አንዳይቆም ያዝዛል፡፡ በእምነቱና በእግዚአብሔር ቃል ብቻ እንዲጸና፡፡ (ፍትሐ ነገሥት፣ 176፤ረስጠብ 21) በዲድስቅልያም ላይ ‹ከቤተ ክርስቲያን ሹሞች በቀር ሕዝባዊ አይፍረድ› ይላል (ዐንቀጽ 71)፡፡ ታድያ በምን ሕግ ነው የመንግሥት ተወካይ ባለበት የቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤውን የሚያደርገው?
ዛሬ እንደዋዛ የሚከፈተው በር ነገ እንዝጋህ ቢሉት አስቸጋሪ ነው፡፡ አንድ አባት የመንግሥት ተወካይ ይገኝልኝ ባለ ቁጥር የሚፈቀድ ከሆነ፤ ነገ ደግሞ ወንድሜ ባለበት፤ እናቴ ባለችበት፤ ሐኪሜ ባለበት፣ ፖሊስ በተገኘበት ይሄ አጀንዳ ይታይ የሚል ነገር መስማታችን አይቀሬ ነው፡፡ ጋባዡም፤ ተጋባዡም ቆመው ሊያስቡበት ይገባል፡፡ መቼም እንደዘንድሮ የእንጦንስና ጳውሊ ራእይ በተግባር የታየበት ዘመን የለም፡፡

ኮለኔል ጎሹ ወልዴ (ወታደር፤ምሁር፤ዲፕሎማት)




  • 0
     
    Share

አብዮታዊዉ የደርግ መንግስት የሶሻሊስትን መንገድ ያስጠኑትን የቀድሞ ወዳጆቹን በተለያየ መንገድ ካገለለ በሗላ ልጓሟን እንደበጠሰች በቅሎ ግራ ሲጋባ ነበር ኮለኔል ጎሹ በመብራት ተፈልገዉ የመጡት። ምንም እንኳን የደርግ ዘመን የጨለማ ዘመን ቢሆንም ሰዉ በዘሩ መጠቃቀሙ የሚታሰብ ስላልነበረ ኮለኔል ጎሹም ዘራቸዉ ከግምት ሳይገባ በችሎታቸዉ ብቻ ተለክተዉ የሚገባቸዉን ወምበር አገኙ። ኮለኔል ጎሹ  ስልጣን ከተረከቡ በሗላ ኢትዮጵያን በታላቅ ክብር በየአለሙ መዲና ሲወክሉ፤ ኢትዮጵያን ከክፉ ጠላቶች ያለእረፍት ሲከላለከሉ ከቆዩ በሗላ  የደርግ መንግስት ስራዉ ሁሉ መረን የለቀቀ ከመሆኑም በላይ የምእራብ ሀገሮችም አይንህ ላፈር ስላሉት  ሊመከር  የማይችል መሆኑን የተገነዘቡት ኮለኔል ጎሹ ከሚያጓጓ ወምበራቸዉና ክብራቸዉ በታሪክና በህዝብ  ተወቃሺ ላለመሆን እንደእኔዉ ሳይወዱ በግድ ሀገራቸዉን ጥለዉ ተሰደዱ። ማንም ጤናማ አስተሳሰብ ያለዉ ዜጋ በወቅቱ ከዚህ የተለየ ምርጫ አይወስድም ነበር ።
ኮለኔል ጎሹ እንደሳቸዉ ትዉልድ በጥሩ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ ታንጸዉ ለሀገራቸዉ አንድነትና ለባንድራቸዉ የማሉ መኮንን ነበሩ።  ከዉትድርና ተቋሙ በብቃትና በጥራት የፈጸሙ  ለመሆናቸዉ  አዉሮፓ በነበርኩበት ጊዜ በአንድ ስብሰባ ከአስልጣኛቸዉ ከጄነራል ነጋ ተገኝ አፍ  ሰምቻለሁ ተከታታይ ስራቸዉም ይህንኑ ያንጸባረቀም ነበር።ኮለኔሉ በወቅቱ የአዉሮፓ ጉዟቸዉ ወያኔን በሀይል ለመናጥ ያዘጋጁትን ድርጂት ለማስተዋወቅ ነበር።  በዚሁ  ስብሰባ ኮለኔል ጎሹ ከተናገሩት መሪ ቃል “ይህ ወጣት ምንም ማድረግ ቢያቅተዉ ስለ ሀገሩ እንዴት መቆጨትና መናደድ ያንሰዋል” ብለዉ የተናገሩት ለረጂም ጊዜ የመወያያ አርስት ሁኖ ሰንብቷል። በእርግጥም ጥሩ አባባል ነበር።
ኮለኔል ጎሹ ወታደር ፤ ምሁር እና ዲፕሎማት ናቸዉ  በዋሉበት ቦታ ሁሉ ድምቀት  የተሞላባቸዉ ፡ በቆሙበት ቦታ ረትተዉ ፤ተደምጠዉ፤ ተደንቀዉ ፤መክተዉ የሚመለሱ ታላቅ ኢትዮጵዮጵያዊ ነበሩ። አንባቢ ለአንድ አፍታ በስዩም መስፍን እግር የባድሜንና ሌሎች ለሻቢያ የተሰጡትን መሬቶቻችንን ክርክር ኮለኔል ጎሹ ይዘዉት ቢሆን ኑሮ ብሎ በምናቡ ያስብ። ስዩም መስፍን ከጠበቅነዉ በላይ ተሰጠን ብሎ ህዝቡን አስጨብጭቦ እሱም አጨብጭቦ በዛ በተዛባ ድርድር ምክንያት የ70 ሺህ ኢትዮጵያዊ ህይወት ተቀጠፈ ወላድ በየቤቱ ይላቀሳል አዝማቾቹ እነ ስዩም መስፍን ስብሀት ነጋ እና ሌሎቹም በየቤቱ ይስቃሉ። ስለዚህ ጉዳይ ታሪክ ወደፊት በሚገባ ያወጣዋል። በስዩም መስፍን ስንገረም ሌላዉ ትያትረኛ  ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም የ9 አመት ልጂ 8 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ አደረገችልን ብሎ ባለም ያሳቀብንን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስተራችንንም ከኮለኔል ጎሹ አንጻር አንባቢ ደምሮ ይመልከትልን :: ታድያ ወደ ጉዳዬ ስመለስ ኮለኔል ጎሹ አገልግሎታቸዉን በብቃት፤በድፍረት  እንዲሁም ፕሮፌሺናል ኤቲክስ በሚፈቅደዉ መስፈርት በጥራት የተወጡ ዜጋ እንደነበሩ  ኢትዮጵያን እንዲህ ያለ ችግር በገጠማት ጊዜ ጉዳዩን እሳቸዉ ይዘዉት ቢሆን ኑሮ ዉጤቱ ሌላ ይሆን ነበር።
ኮለኔል ጎሹ በእዉቀት ደረጃም በሁለት እጂ የማይነሱ ምሁር እንደነበሩና እስከ አሁንም አስመዝገበዉ ያለፉት ነጥብ ያልተደፈረ መሆኑን እናዉቃለን ከሚሉ ሰዎች ይደመጣል። ወደ ሗላም ወደ ባህር ማዶ ተሻገረዉ ከስመ ጥሩዉ ዬል ዩኒቨርስቲም አድናቆት የተቸራቸዉ እንደነበረ ድርሳናት ያሳያሉ። ከዉትድርና ትምህርት ባሻገር በህግ የረቀቀ እዉቀትና ችሎታ ያላቸዉ ኮለኔል ጎሹ እራሳቸዉን ከአንድ አርእስት ወደ ሌላዉ አርስት በመወረወር በተነሳዉ ነጥብ ሁሉ በሳል አስተያየትን  ሰጥተዉና አስተምረዉ የሚመለሱ ዜጋ በመሆናቸዉ ለዲፕሎማቲክ ስራ ተቀራራቢ ሰዉ ሊገኝላቸዉ የማይችሉ ኢትዮጵያዊ ነበሩ።
ኮለኔሉ በዲፕሎማሲያዊ ስራ እና ለህዝብ ይፋ ካልወጣዉ አስተዋጽዋቸዉ ሌላ ምን ሰርተዉ ነበር  ብሎ መጠየቅ የዜጋ መብት ነዉ ኮለኔል ጎሹም የህዝብ ሰዉ በመሆናቸዉ ይህ ቅር የሚላቸዉ አይመሰለኝም።
የትግራይ ነጻ አዉጭ ድርጅትና ሻቢያ አገሪቱን ከተቆጣጠሩ በሗላ ሊደርስ የሚችለዉ አደጋ ቀደም ሲል ስለገባቸዉ ጠንካራ ድርጅት አቋቁመዉ ኢትዮጵያን ከነዚህ ክፉ ጠላቶች ለማዳን ጥረት አድርገዉ ነበር:: ታዲያ እንደ ኮለኔል ጎሹ፤ፖል ትዋት፤ኢንጂነር ቅጣዉ፤ኮለኔል ታደሰ  አይነት ዜጋ የሚመራዉ ድርጅት ፈተናዉ ብዙ በመሆኑ የኮለኔል ጎሹንም ድርጅት የኢትዮጵያ ጠላቶች ከዉስጥና ከዉጭ ተረባርበዉ በለጋነቱ ጣሉት የኮለኔል ጎሹም ሀሳብ ዉጥን ብቻ ሁኖ ቀረ እንደ አንድ መሪ ግን የሚቻላቸዉን አደረጉ በዚህ ሊመሰገኑ ይገባል።
ኮለኔል ጎሹ አገር ከፈረሰ በሗላ በእጂጉ ከሚታወቁበት ትልቁ ስራቸዉ የአሜሪካን ሴናተር በጠራዉ ስብሰባ ላይ ከሻቢያና ከወያኔ ጋር  ያደረጉት ፍልሚያ ነበር።  ይህ ህዝብ የጣለዉን መንግስት ጣልን ብለዉ በለስ ቀንቷቸዉ  ሸብ ረብ በሚሉበትና እንደ መንትዬ ልጆች  ሻቢያ የጀመረዉን ወያኔ በሚጨርስበት የስብሰባ ስርአት ያደረጉት ንግግር በታሪክ ዘወትር ሲታወስ ይኖራል። ኮለኔል ጎሹ ብቻቸዉን ያለአንዳች ረዳት ይህን የበታኝ መንጋ  ሲለበልቡት አብረዋቸዉ የተቀመጡት ትንፍሺ ሳይሉ ወጥተዉ ሂደዋል የዛን ቀን ሁኔታቸዉም ከአንዱ የአፍሪካ ሀገር ለታዛቢነት የመጡም አስመስሏቸዋል። ምክንያቱም በለስ ከቀናዉ ሀይል ጥቅም አይጠፋም በሚል ምክንያት በስብሰባዉ ላይ አድፍጠዉ ተቀምጠዉ ነበር:: በሗላም እንደ አምቦ ወንድሞቻችን የኢትዮጵያ ህዝብ ጨክኖ ወያኔንና ሻቢያን እንዳይፋለም አንዴ ጊዜ ስጧቸዉ አንዴም የኛዉ ናቸዉ እያሉ ሲያጃጂሉን ከርመዉ ዛሬ ዉቃቤ ርቋቸዉ ከአንዱ ጎል ወደ ሌላዉ ጎል እራሳቸዉን እየለጉ እለተ ሞታቸዉን ይጠብቃሉ።
ታዲያ አድር ባይነትን ባእጂጉ የተጠየፈዉ  ጀግናዉ የኢትዮጵያ ልጅ ጎሹ ወልዴ ግን በዛን ስብሰባ ብቻዉን ግዳይ ጥሎ ገብቷል።
ጎሹ በዛን ቀን በሰራዉ ስራ ስሙና ተጋድሎዉ ሀገሩን በሚወድ ዜጋ እስከ ወዲያኛዉ ሲታሰብ ይኖራል።  ዛሬ ነገር አልፎ ቀላል ቢመስልም በዛን በቀዉጢ ጊዜ አባሎቻቸዉ መረን በወጡበት ዘመን ደፍሮ ሀገሩን ብቻዉን  መክላከሉ ሀገሩን በሚወድ ዜጋ ዘወትር ሲታሰብ ይኖራል። እንደዉም የእዉቀቱን ጥልቀት የተረዳዉ የስብሰባዉ ሊቀ መንበር ምን ብናደርግ ይሻላልም ብሎ ሀሳብ ጠይቆ ጎሹም ጥራት ያለዉ መልስ ሰጥቶ ነበር።በዛን ቀን ኮለኔል ጎሹ ባሳየዉ ወታደራዊ መንፈስ፤ የነገር አወራረድ፤ የሃሳብ ብስለት፤ የቋንቋ ጥራትና የታሪክ እዉቀት  የተገረመዉ ሴናተር በተመስጦ ሲመለከተዉ ደናቁርቱ ባላንጣዎቹ ደግሞ በክንድ ጠምዝ ምልልስ የጀግናዉ ጎሹን ወልዴን ሀሳብ ሊመክቱ ሲታገሉ በእጅጉ ያሳዝኑ ነበር። በዛን ቀን በተሰራዉ ስራ ኮለኔል ጎሹ ያለምንም ተቀናቃኝ እራሱን  ከታላላቁ ጎራ ቀላቅሏል። ያም ስራዉ ተቀራራቢነቱ ለሀገራቸዉ ታላቅ ስራ ሰርተዉ ካሸለቡት ዜጎች እንደ አንዱ ሊሆን ይገባዋል።  ድልንና ታላቅ ስራን  የምንመዝነዉ እንደ ዘመኑ በመሆኑ ጀግናዉ ጎሹ ወልዴም በዛን ቀን በሰራዉ ስራ ታሪክ እስከ ወዲያኛዉ ሲያስታዉሰዉ ይኖራል።  (እዚህ ላይ ነሸጥ አድርጎኝ አንተ ብያለሁ መቼም ጀግና እርሶ አይባልምና)
እንግዲህ ከአንድነት ሐይሎች ሰፈር ኮለኔል ለመገለላቸዉ  ምን  ምክንያት ሊሰጥበት ይችላል? በእርግጥ ዘመኑ የጨረባ ተዝካር የሆነበት፤ ከአዋቂ ይልቅ ተናጋሪ የተደመጠበት፤ ከአንድነት ይልቅ ልዩነት የተመረጠበት ፤ያለዉን ከመያዝ መበተን የተያዘበት፤ ከሀቅ ይልቅ  ትርፍ በሚያመጣ ነገር ላይ ማተኮር የተመረጠበት በመሆኑ ይህ ደግሞ ለኮለኔል ጎሹ ስብእና የሚስማማ ባለመሆኑ ዳር ሁነዉ መመልከትን መርጠዉ ይሆናል የሚል ግምት አለኝ። ትላንት በካድሬነት ሲያገልግሉ የነበሩ የሶሻሊስት ደቀ መዛሙርት ዛሬ ተገልብጠዉ የዘዉግ አስተዳደር ለኢትዮጵያ መፍትሄ ነዉ ብለዉ የሚሰብኩትንም ላለማየት ፈልገዉም ይሆናል ወይም ደግሞ ኤርትራ በሀይል ተገንጥላ ስትሄድ ፓርላማ ቁጭ ብለዉ ሲያጨብጭቡ ከነበሩ ፓርላሜንታሪያንም ጋር በአንድ መድረክ ላለመቀመጥም መንፈሳቸዉ ተጠይፎም ሊሆን ይችላል። ወይም ደግሞ 100,000 ጦር ኢሳይያስ አፈወርቀ ላይ አዝምቶ ዛሬ ኢሳይያስ አፈወርቅ የኢትዮጵያ ወዳጂ ነዉ የሚለዉን ላለመስማት ፈልገዉም ሊሆን ይችላል። ምሁር ተብየዎችም ኢትዮጵያ የማትጠቀምበት እምቅ ሀብት አላት ኑና ዉሰዱ ብለዉ የጥንት አፍራሺ ጓደኞቻቸዉን መታረቂያ ያደረጉት ስብሰባም ሳይመቻቸዉ ቀርቶ ይሆናል።
እንግዲህ ዛሬም እንደ ትላንቱ ለሌላ ጥፋት በየቦታዉ በሚደረገዉ ስብሰባም መገኘት ያልፈለጉበት ታሪክ እራሱን ሲደገም ድንጋይ አላቃብለም ብለዉም ሊሆን ይችላል።  ከዚህ ታክኮ የዘር ድርጅቶች በየምክንያቱ በራቸዉን ሲያንኳኩም የለም ይህ እኔን አይመለከትም ዘሬ ኢትዮጵያዊ ነዉ በጽናት እስከ ኢትዮጵያዊነቴ በክብር እንደ አንድ ወታደር እሞታለሁ ብለዉ እንደሚመልሱም ጥርጥር የለኝም። የተለያዩ የሚዲያ ተቋማትም ጎትተዉ  ባልፈለጉትና በማይመቻቸዉ  አርእሰት አስገብተዉ እንዲያዘላብዷቸዉ ሳይፈቀዱም ቀርተዉ ይሆናል።
ኮለኔል ጎሹ ኢሳይያስን ነጻ አዉጣኝ ብለዉ ያልተማጠኑ፤ለኢትዮጵያ የሚጠቅመዉ በዘር መከፋፈሏ ነዉ ከኢትዮጵያዊነት በላይ ዘራችን ቅድሚያ ሊሰጠዉ ይገባል ታሪካችንም  100 አመት አይበልጠዉም ከሚለዉ ዘመን አመጣሺ በሺታ ተከልለዉ መቀመጣቸዉ መልካም ቢሆንም ለተተኪዉ ትዉልድ የሚጠቅም ብዙ ደጎስ ያሉ መጻፍቶችን ቢያስነብቡን በሪፈረንስ መልክ አጠገባችን ይቀመጥ ነበር የሚል እምነት አለኝ። ለማንኛዉም በኔ በኩል መልካም ጤንነትና እድሜ እየተመኘሁ ከግራ ቀኝ የሚላተሙ የእርሶ ዘመን ሰዎችም የኢትዮጵያዊነትና አንድነት ማተባቸዉን ጠብቀዉ በክብር ወደማይቀረዉ ለመሄድ ቢዘጋጁ መልካም ነዉ እላለሁ።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ንብረትነቱ የመንግስት የሆነ በጎሮ ከተማ የሚገኝ የመሳርያ መጋዘን ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋይቶ ወደመ። (ፎቶዎች)


ንብረትነቱ የመንግስት የሆነ በጎሮ ከተማ የሚገኝ የመሳርያ መጋዘን ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋይቶ ወደመ።(ፎቶዎች)ger1ger
ger

ger1ger
ger

ኢትዮጵያውያን ምን እስኪፈጠር ነው የምንጠብቀው?



  • 658
     
    Share
~ 2.4 ሚሊዮን የአማራ ክልል ተወላጆች በህዝብ ቆጠራ ወቅት ጠፉ
~ ከ125 በላይ ህፃናት በጋምቤላ ክልል በሙርሌዎች ተዘረፉ
~ የእምነት ነፃነት በመጠየቃቸው ብቻ የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው እስራት፣ ግርፋት፣ ግድያና እንግልት ዛሬም ቀጥሏል።
~ ላለፉት 25 ዓመታት በስርቱ ተላላኪዎች የተቃጠሉ ገዳማትና ቤተክርስቲያን ቁጥር ቀላል አይደለም።
~ ከ2000 በላይ ከብቶች በሙርሌዎች ተዘረፉ
~ ከ225 በላይ የጋምቤላ ተወላጆች በሙርሌዎች ተገደሉ
~ ከ400 በላይ የአኟክ ተወላጆች በህወሃት/ኢህአዴግ ተወላጆች በጠራራ ፀሃይ ተገደሉ
~ ከ200 በላይ ዜጎች ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ በህወሃት/ኢህአዴግ የፌደራልና የመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ
~ ከ10 ዓመት በኋላ በሚደረገው ህዝባዊ ቆጠራ የጉራጌ፣ ኦሮሞ፣ አማራና የሌሎችም ዜጎች ቁጥር ቀንሷል
~ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ከ80ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን አለቁ
~ ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ አያሌ ኢትዮጵያውያን ሶማልያ ውስጥ ሰላም ለማስከበር በሚል ተልከው ተገድለዋል። የቀድሞ ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ስንት ሰው እንደሞተ ለመግለፅ ፓርላማ ውስጥ ተጠይቀው የማሳወቅ ግዴታ የለብኝም ብለው እንቢ ማለታቸው የሚታወስ ነው።
~ አማራ ክልል ውስጥ ወላድ እናቶችን ክትባት በመስጠት እንዳይወልዱ ተደርገዋል። ያረገዙትም እንዲያስወርዳቸው ተደርገዋል።
~ ለሃገራችን የሚጠቅሙ አያሌ ኢትዮጵያውያን በሰበብ አስባቡ በእስር ቤት ታግደው ይገኛሉ።
~ ስርዓቱ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ምቹ ባለማድረጉ ምክንያት አያሌ ኢትዮጵያውያን ለስደት ተዳርገዋል። ያሰቡበት ያልደረሱትም የበረሃ ሲሳይ ሆነዋል። ሌሎችም በሜደትራኒያን ውቅያኖስ ተወስደዋል። በየበረሃው በባዕዳን ተደፍረው ለእብደት የተደራጉትና ለዘላለም የህሊና ጠባሳ እስረኛ የሆኑ ብዙ ናቸው። የዱር አራዊትና የአሳ መብል የሆኑትም ብዙዎች ናቸው።
~ 28 ኢትዮጵያውያን በISIS አንገታቸውን ተቀልተው ተገድለዋል።
~ ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ ኢትዮጵያውያን በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው Xenophobia እስከነ ህይወታቸው ከጎማ ጋር በመጠፈር ተቃጠለው ተገድለዋል። እሚከራከርላቸው አጥተው በየቀኑ የሚገደሉትም ቁጥር ስፍር የላቸውም።
~ የመን ውስጥ በተቀሰቀሰው የርስበርስ ጦርነት በስደተኛ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአየር መደብደባቸው የሚታወስ ነው።
~ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መግቢያ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዋናው ቅጂ ተሰርቆ ወጥቷል።
~ በጎንደር በኩል ለሱዳን 160 ኪሎ ሜትር መሬት ወደ ውስጥ ተላልፎ ተሰጥቷል
~ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 25 ዓመታት ወደብ አልባ ተደርጋለች
~ ላለፉት 25 ዓመታት የተገደሉትና የታሰሩ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር በውን የሚታወቅ አይመስለኝም። በቅርብ ጊዜ በተፈጠረው ተቃውሞ እንኳን ከ200 በላይ የኦሮሞ ተወላጆች ተገድለዋል፣ ከ3000 በላይ ታስረዋል፣ አያሌዎች ተደብድበዋል፣ ለስደት ተዳርገዋል።
~ በየአረብ ሃገራ በእህቶቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይና በደል ለሁላችንም ግልፅ ነው
~ የማንነት ጥያቄ ባነሱት የወልቃይት ጠገዴ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ኢ-ሰብዓዊ ተግባር የሚዘገንን ነው።
~ ሌላም ሌላም……..
…,……………………..……..
ይህ ሁሉ በደል አልበቃ ብሎ ምን እስኪያደርጉን ነው የምንጠብቀው??

ኢትዮጵያዊያን ሯጮች በካናዳ ኦታዋ ማራቶን ድል ቀናቸው by ኢትዮአዲስ ስፖርት


ኢትዮጵያዊያን ሯጮች በካናዳ ኦታዋ ማራቶን ድል ቀናቸው!
ዘገባ – በናታ
rutu
በካናዳዋ ኦታዋ የጎዳና ላይ የማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊያን በሁለቱም ጾታዎች ድል ቀንቷቸዋል። እ.ኤ.አ. በ1975 የተጀመረው ታሪካዊው የኦታዋ የሩጫ ውድድር በማራቶን ክብረወሰኑ የተያዘው በኢትዮጵያዊያን አይበገሬ ሯጮች ሲሆን በወንዶች የማነ ጸጋዬ 2:06:54 በመግባት የክብረወሰኑ ባለቤት ሲሆን በእንስቶች ደግሞ ትእግስት ቱፋ 2:24:30 በመግባት የስፍራው የእንስቶች ቁንጮ ናት።
በዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ማኅበር የወርቅ ደረጃ በተመደበው በፈታኙ የማራቶን ሩጫ ውድ ድር ላይ ኢትዮጵያዊያኑ አንጸባራቂ ድል አስመዝግበዋል። ይህም ከማራቶን ድሎች እየራቀች ለነበረችው ኢትዮጵያ ተስፋ ፈንጣቂ የድል ብስራት ነው። እሁድ እለት በተካሄደውና ሞቃታማውን የአየር ሁኔታ ታግለው ድል ማስመዝገብ የቻሉት አትሌቶቻችን በወንዶች ምድብ ዲኖ ሰፊር 2:08:14 በሆነ ሰዓት በቀዳሚነት ሲገባ እሱን በመከተል የ19 ዓመቱ ወጣቱ ተስፈኛው ሹራ ኪታታ 2:10:04 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ ኬንያዊው ዶሚኒክ ኦንዶሮ 2:11:39 በሆነ ሰዓት ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።
በእንስቶች ምድም ደግሞ ድንቋ ራጭ ኮረን ጃለላ ስምንቱን ኪሎ ሜትሮች ብቻዋን በመሮጥ በአንደኝነት አጠናቃለች የገባችበትም ሰዓት 2:27:06 ሲሆን እስዋን በመከተል አበሩ ማከሪያ፣ ሰቻሌ ደላሳ እና ማክዳ አብደላ ከሁለተኛ እስከ አራተኛ የአገርዋ ልጆች በመግባት ሜዳሊያውን ኢትዮጵያዊያን ጠራገው ወስደውታል። አበሩ ማከሪያ 2:29:51 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ፣ ሰቻሌ ደላሳ 2:32:46 በሆነ ሰዓት በመግባት ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ፈጽመዋል።

የሞቅታና የሆታ ፖለቲካ ያከስራል – ግርማ ካሳ


የሞቅታና የሆታ ፖለቲካ ያከስራል – ግርማ ካሳ
የኢትዮጵያ ፖለቲክ በጣም ፈታኝ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በጣም ከባድና አስቸጋሪ ባህል ነው ያለን። ትላንት የካብነዉን ሰው ዛሬ እንዘረጥጠዋለን። አንድ ሰው የተለየ ሐሳብ ካቀረበ ወይንም ከተቸኝ እንደ ጠላት እንቆጥረዋለን። ስንተች አንወድም።
ግፉ ጭክኔው ከጊዜ ወደ ጊዜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ተባብሷል አንጂ አልቀነሰም። የግፍ አገዛዙ ይኸው 25ኛ አመት የብር እዩቤልዩን አከብሯል። እልፍ ደርጅት ነው ያለው በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ፤ ግን ምንም የተለወጠ የተለየ ነገር የለም። አፍጥጦ የወጣው ሐቁ ይሄ ነው።
ለአገዛዙ አሁን በስልጣን ላይ መሆን ተጠያቂዎቹ በዋናነት ተቃዋሚዎች ናቸው ባይ ነኝ። በፓርቲዎች ዉስጥ ተቋማትን ከማጠናከር የተቃዋሚ መሪዎችን እላይ እንክባቸዋለን። ሲዋሹ፣ ሲያጭበረብሩ፣ ለስልጣናቸውና ለክብራቸው ሲሉ አብሮ ከመስራት ፣ ከመተባበር ሲቆጠቡ፣ ገንዘብ ሲመዘብሩ፣ የሰበሰቡትን ገንዘብ ምን ላይ እንዳዋሉት ሲጠየቁ መልስ አልሰጠም ሲሉ ፣ በሚወስኗቸው ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ስለመሆናቸው ቻሌንጅ ሲደረጉ ሲያኮርፉ፣ ዝም እንላቸዋለን። ጥያቄ የሚያቀርቡትን “ወያኔዎች ናቸው፣ እንዴት መሪያችንን ይናገራሉ ?” ብለን እንጨረጨራለን። ገንዘባችንን በልተው፣ ልባችንን ሰርቀው፣ “ሆ ሆ ሆ ” አሰኝተዉን ዘጭ ሲያደርጉን መልሰን ደግሞ እነርሱን መራገም እንጀምራለን። ተስፋ እንቆርጣለን።
አንድ አጉል የሆነ ንግግር ደግሞ አለ። “መጠላለፍ የለብንም። ወያኔ ላይ ብቻ ነው ማተኮር ያለብን” የሚል። ለምንድን ነው ወያኔ ላይ ብቻ የሚተኮረው ? ለወያኔ መኖር ምክንያቱ የተቃዋሚው መዳከም መሆኑ ተረስቶ ነው ? እንደዉም ማጭድና መዶሻ በመያዝ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ከሥር አንስቶ ማሻሻል ያስፈልጋል።
ሰው ማንበብ የሚጽፈውን ብቻ እየጻፍን እንዲጨበጨብልን ማድረግ እንችላለን። በጣም ቀላል ነው። ግን ሰው መስማት የሚፈልገውን ብቻ የመናገር ፖለቲካ ውጤት አያመጣምም። አላመጣም። እዉነቱን መነጋገር አለብን። በተቃዋሚዎች ዘንድ መሰረታዊ የአካሄድ ለዉጥ መኖር አለበት።
1. የተናጥል ትግል መቆም አለበት። ቢያንስ አገር አቀፍ የሆኑ ድርጅቶች ሪሶርሳቸዉን፣ ሃይላቸውን ማሰባሰብ አለባቸው። በጎሳ የተደራጁ ደርጅቶች ጋር መሰባሰቡ ፈታኝ ቢሆንም፣ በሚያስማሙ የጋራ ጉዳዮች ዙሪያ አብሮ መስራት የሚቻልበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይቻላል።እንዲህ ሲል ትእዛዝ እየሰጠሁኝ አይደለም። አንዳንድ ሰዎች ለምን እንደዚያ እንደሚያስቡት አላውቅም። ሐሳብ ነው እያቀረብኩ ያለሁት።
2. የሰለጠነ፣ የመቻቻል ፖለቲካን ማራመድ ያስፈልጋል። የሰለጠነ ፖለቲካ የዴሞክራሲ ካምፑን የሚያሰፋ ነው። ከኛ ጋር የማይሰማማዉን ሁሉ ሳይቀር ወያኔ፣ ሆዳም ፣ ባንዳ እያለን የምንሰድብ ከሆነ ብቻችንን ነው የምንቀረው። እንደዉም ፖለቲካችን ከኢሓዴግ ወገን ያሉትን ወደኛ የማምጣት ሥራን ማካተት ሁሉ አለበት። ኢሕአዴግ ዉስጥ ያሉትን በሐሳብ ማሳመን ከቻልን፣ እነርሱ ደግሞ ሄደው በደርጅታቸው ዉስጥ ተጽኖም ሊያመጡ ይችላሉ። ዝም ብሎ ቁም ነገር የሌለው፣ ያከረረ. የጥላቻ ፣ የንዴት ፖለቲካ የትም አያደርሰንም። ፖለቲካ ማለት ወዳጆችን ደጋፊዎች ማፍራት ነው። የስድብ፣ የእልህ፣ የንዴት ፖለቲክ ሰዉን የሚገፋ እንጂ የሚሰብ አይደለም።
3. ሕዝብን በየክልሉ ማደራጀት ያስፈለጋል። የፖለቲክ ሥራ አዲስ አበባ ባሉ ጽ/ቤቶች ወይንም ከኢሳት ወይን አሜሪካን ዽምጽ ወይም ፓልቶክ ጋር በስልክ የሚደረግ ቃለ ምልልስ አይደለም። የፖለቲካ ሥራ ወደ ሕዝብ ወርዶ ህዝብን ማደራጀት ይጠይቃል። ወደ ህዝብ ያልወረደ ትግል ዋጋ የለውም።
4. የድርጅት መሪዎች አምባገነን እንዳይሆኑ የሚቆጣጠር አሰራር መኖር አለበት። የድርጅቶች ተቋማት ጠንካራ መሆን አለባቸው። በቅንጅት ጊዜ ሲያምሱን የነበሩት እነ ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል ነበሩ። በመኢአድ ዉስጥ የአቶ ማሙሸትና የአቶ አበባው ዉዝግብ ነበር ደርጅቱን የጎዳው። በሰማያዊ ዉስጥም የነበረዉን የምናወቀው ነው። መሪዎች ሲበጠብጡ …
5. ትግሉ ከኤርትር መንግስት ነጻ መሆን አለበት። ከሻእቢያ መመሪያ እየተቀበሉ የሚደረግ ትግል ከወዲሁ የሞተ ነው። ብዙ አርቆ ማሰብም አይስፈልግም። ኢትዮጵያዉይን አይኖቻችንን በዉስጣችን ያለው ሃይል ላይ እንጂ አስመራ ላይ ማድረግ የለብንም። ይኸው ላለፉት 25 በአስመራ ተረዳን እያሉ እንታገላለን የሚሉ ደርጅቶች ብዙ ነበሩ። ግን አንድ ቀበሌ ለመቆጣጠር ቻሉ ? መልሱን ለአንባቢያን።
6. ትግሉ ያለው ኢትዮጵያ ዉስጥ ነው።ዲሲ፣ ወይ ጀርመን፣ ወይ ሲያትል ፣ ወይ አስመራ አይደለም።
ወገኖች ኢሕአዴግን በጣም ስለጠላን፣ በጣም ስለረገምነው፣ በጣም ጠዋትና ማታ አመራሮችን ስለዘለፍን፣ ነጋ ጠባ በራዲዮና ቴለቭዥን ፕሮፖጋንዳ ስለሰራን፣ አንድ ሺህ የፖለቲክ ደርጅቶችን ስላኮቶሎተልን፣ በየሰብሰባዎችን ስለፎከርን እና “ወያኔ አለቀላት” ስላለን፣ አሁን ያለውን ስርዓት አንለወጥም። አንሞኝ። በጭራሽ አንለዉጥም።፡ ከዚህ በፊት እንዳልኩት 25 እንዳከበርን 50 የወርቅ እዩቤልዩ እናከብራለን። በግሌም ውጤት በማያመጣ ትግል ላይ ጊዜ ማጥፋት አልፈለግም። በተቃዋሚ ፓርቲዎች ዘንድ መሰረታዊ ለዉጦች የማይታዩ ከሆነ ፣ የሰለጠነ ፖለቲካ የሚያራመድና የሚመራ ድርጅት ወይንም የድርጅት ስብስበ ከሌለ የፖለቲካ እንቅስቃሴዬን መመርመር ያለብኝ ይመስለኛል። ለማንኛውም እስቲ የሚሆነውን ሁኔታ በቅርበት እንከታተላለን። ለጊዜው ትኩረቴ መኢአድ እና ሰማያዊ ላይ ነው። መኢአድ ጠቅላላ ጉብዬን በተሳካ ሁኔታ አድርጓል። አዲስ አመራር መርጧል። ሰማያዊም ያሉ ችግሮቻቸውን በዉይይት ለመፍታት ተሰማምተዋል። ምናልባት እነዚህ ደርጅቶች ቀደም ሲል ከሚያደርጉት በተሻለ ሁኔታ ጠንካራ ሆነው ሊወጡ ይችሉ ይሆናል።
(በነገራችን ላይ ሐሳብን በሐሳብ መመከት ተስኗችሁ ወደ ስድብ የምትሄዱ፣ “ወያኔ፣ ሆዳም ሰላይ ” ወዘተረፈ ለምትሉ ወገኖች የፈለጋችሁን የማለት መብታችሁን እያከበርኩ፣ በናንተ እንዲህ ማለት ቅንጣት ያክል እንደማልነቃነቅ እንድትረዱልኝ እፈልጋለሁ። እኔ የምታዘዘው ለፈጣሪዬና ለሕሊናዬ ነው። ነጻነቴንም እወደዋለሁ።፡ የአገራችን ፖለቲክ ድብቅ እና ዉስጥ ዉስጡን ነው። እኔ ፖለቲካችን ግልጽነት ሊኖረው ይገባል ባይ ነኝ። በመሆኑም ይጠቅማል ብዬ እስካሰብኩ ድረስ መጦመሬን እቀጥላለሁ። ደስ የማትሰኙ ካላችሁምንም ማድረግ አልችልም። ጽሁፎቼን አለማንበብ ትችላላችሁ። ያስገደዳችሁ የለም። ስድባችሁን ግን እዚያው የለመዳችሁበት ቦታ አድርጉት)

በእንደራሴ ምደባ ጉዳይ: ፓትርያርኩ እስከ ነገ አቋማቸውን የሚያሳውቁበት የማሰላሰያ ጊዜ ተሰጣቸው


Abune Mathias perplexed
  • ከንግግራቸው በተፃራሪ በአማሳኞችና በተሐድሶ መናፍቃን ተጽዕኖ ውስጥ ወድቀዋል
  • የተጽዕኖው አስጊነት ምደባውን አስፈላጊ እንዳደረገው በምልዓተ ጉባኤው ታምኖበታል
  • ፓትርያርኩ፣ “ሌላ አለቃ ልታስቀምጡብኝ ነው ወይ?” በሚለው ተቃውሟቸው ውለዋል
  • በተቃውሞ ከጸኑ፣ ጉባኤው በአብላጫ ድምፅ ወስኖበት ሌላ ሰብሳቢ በመምረጥ ይቀጥላል
*           *           *
  • ቅ/ሲኖዶስ፣ የመጨረሻው መንፈሳዊ እና አስተዳደራዊ ሕግ አውጭ እና ወሳኝ አካል ነው
  • ሕጎችን ያወጣል፤ ያሻሽላል፤ ይሽራል፤ የአስተዳደር መዋቅርን ደረጃና ተጠሪነት ይወስናል
  • በእንደራሴ ምደባ ጉዳይ የሚያሳልፈው ውሳኔም፣ የሕገ ቤተ ክርስቲያኒቱ አካል ይኾናል
  • ፓትርያርኩን በአመራር ለማገዝ ለሚሾመው እንደራሴ ምደባ፣ ዝርዝር ደንብ ይወጣል
*           *           *
  • ፓትርያርክ የሚባሉት ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ፣ የቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን አባት ናቸው
  • የፓትርያርክነት/ርእሰ ሊቃነ ጳጳስነት ሥልጣናቸው የአመራር እንጂ የክህነት ደረጃ አይደለም
  • ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቀው ያለአድልዎ የማስተዳደር እና የመምራት ሓላፊነት አለባቸው
  • ቤተ ክርስቲያንን ማስነቀፋቸውና ታማኝነት ማጣታቸው ከተረጋገጠ ከሥልጣናቸው ይወርዳሉ
*           *           *
በዛሬ፣ ግንቦት ፳፪ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም. ከምደባው ጋር በተያያዘ ከምልዓተ ጉባኤው ውይይት የሚጠቀሱ፡-
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፡-
  • “በሕጉ እንደራሴ ይመደብ የሚል ሕግ የለም፤ ከሕጉ ውጭ ነው፤ ሕጉ ይከበር፤ እኔስ ምን አደረግኋችኹ? እየሠራኹ አይደለም ወይ? ከእኔ በላይ ሌላ አለቃ፣ ሌላ ባለሥልጣን ልታስቀምጡ ነው ወይ?”
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፡-
  • “ምልዓተ ጉባኤው÷ ሕግ የማውጣት፣ የወጣውን የማሻሻልና የመሻር ከፍተኛ ሥልጣን አለው፤ ውሳኔውም እንደ ሕግ ይሠራል፤ የቅዱስነትዎም ተጠሪነት ለቅዱስ ሲኖዶስ ነው፤ ሓላፊነትዎ ከባድና ክፍተቱ ብዙ ቢኾንም የተሰጠዎትን ከመናገር በቀር ምንም አልሠሩም፤ ምክርዎም ከአማሳኞችና ከመናፍቃን ጋር ነው፤ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ውጭ እስከ ሀገረ ስብከትና አጥቢያ ድረስ ወርደው ሥራ አስኪያጅ፣ ጸሐፊ እና ሒሳብ ሹም ይመድባሉ፤የምንሾመው የሚያግዝ እንደራሴ ነው፤ አንድ ብቻ ሳይኾን ብዙ ሊያስፈልግ ይችላል፤ ከዚኽ በፊትም በየዘመነ ፕትርክናው ሠርተንበታል፤”
  • እንደ ጉባኤው ሕግና ደንብ፣ አጀንዳው በድምፅ ብልጫ ሊወሰንበት ይገባል፤ ምልዓተ ጉባኤው 50 ለ1 ኾኖ መቀጠል የለበትም፤
  • ፕትርክናዎን ከቅዱስ ሲኖዶስ እና ለቤተ ክርስቲያን ከሚያስቡ ጋር ሊሠሩበት እንጂ ከማይመለከታቸውና ከሚያበጣብጡን ጋር ሊመክሩበት አይገባም፤ ካልኾነ ሥልጣኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ነው፤
  • ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር መሥራትዎ ግድ ነው፤ ሕዝብ ይግባ፤ መንግሥት ይግባ ማለት ሕገ ቤተ ክርስቲያንንና ሕገ መንግሥቱን አለማወቅ ነው፤ ማንም በማንም መግባት አይችልም፤ እኛም አንፈልግም፤
  • ቤተ ክርስቲያን በሕዝብ መካከል ኾና ኹሉንም በአንድነት የምትጠብቅ ችግር ፈቺና አስታራቂ ተቋም ናት፤ እነእገሌ ይግቡ፤ እነእገሌ ይምጡ የሚለው አስተሳሰብ የመከፋፈል አጀንዳ ያላቸው ሰዎች ከውጭ የሚረጩት ነው፤
  • ለረጅም ጊዜ በቤተ ክርስቲያንና በብፁዓን አባቶች ላይ ሲዘምቱ የቆዩ መናፍቃን፣ ስለአጀንዳው የሚያሰራጯቸው አሉባልታዎች፣ ፍጹም ሐሰትና ኾነ ተብሎ የጉባኤውን አቅጣጫ ለማስለወጥ የሚያናፍሷቸው ናቸው፡፡

Monday, May 30, 2016

ስኬት እና ተምሳሌት – “በዛሬው ዕለት በታሪክ ተመዝግቦ የሚኖር አኩሪ ድል በደማቅ ተጽፏል!!!” ይድነቃቸው ከበደ (እርገጤ)


ስኬት እና ተምሳሌት  ይድነቃቸው ከበደ (እርገጤ)
—-
“በዛሬው ዕለት በታሪክ ተመዝግቦ የሚኖር አኩሪ ድል በደማቅ ተጽፏል!!!”
——
Yidnekachew Kebede's Profile Photoብልህነት የተሞላበት ስትራቴጂ ከተነደፈ፣ አምባገነናዊ ሥርትዓት እና የሥራዓቱ አራማጆችን በአነስተኛ መሰዋዕትነት ትልቅ ድል ማስመዝገብ ይቻላል።ለዚህም በዛሬው ዕለት በታሪክ ተመዝግቦ የሚኖር አኩሪ ድል በደማቅ ተጽፏል። አምስት ወር ሙሉ ትምህራትቻውን ባአግባቡ ሳይከታተሉ፣ በአገዛዙ ጠባቂዎች ሲገደሉና ሲንገላቱ የነበረ ተማሪዎች፤ በግዳጅ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የብሔራዊ ፈተና እንዲፈተኑ የታቀደው እቅድ፣ በሰለጠነ የሰላማዊ ትግል ዜዴ ማስቀረት ተችሏል ።ይህን መሰል አኩሪ ድል ለፈጸሞት ምስጋና ሲያንስባቸው እንጂ አይበዛባቸውም።
“የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን”የሚል ስያሜ የተሰጠው የመሬት ነጠቃ እና ወረራ ፤የህዝብ ጥቅም እና ፍላጎትን ያልጠበቀ መሆኑን ተከትሎ ፣በተደረገ ህዝባዊ ጥያቄ እና በገዢው መንግሥት በኩል በተሰጠው ምላሽ ፣ መተኪያ የሌለው የሰው ልጅ ሕይወት እንዲጠፋ ፣የንብረት ውድመትና ኪሳራ እንዲደርስ ምክንያት ሆኗል።ለህዝብ አቤቱታ እና ተቃውሞ ፣ተገቢውን ክብርና ምላሽ የመስጠት የአቅም ውስንነት ብቻ ሳይሆን አፈጣጠሩ ጭምር የማይፈቅድለት የህውሓት/የኢህአዴግ አንባገነን መንግሥት ዓይኑን በጨው አጥቦ ፣ከሞትና ከእስራት የተረፉ ታዳጊ ወጣቶችን፣ በከፍተኛ ትምህርት መግቢያ በብሔራዊ ፈታና ለመቅጣት ሲዳክር ፣ የአገዛዙ ስርዓት ለብቀላ አንድም ሣይቀር ምን ያህል ርቀት እንደሚሄድ የሚያመላክት ነው።
የከፍተኛ ትምህርት የብሔራዊ ፈተና፣አንድ ተማሪ በቀጣይ የትምህርት ሂደቱ እና በወደፊት የስራ መስክ ላይ ቀጥተኛ ውሳኔ የሚወስንበት የዓመታት የልፋት ውጤት ነው። የፈተና ውጤቱ የሚያስከትለውን አሉታዊ እና አወንታዊ ተጽእኖ ቀላል የሚባል አይደለም ። በዚህ ላይ አሻሚነት እንደሌለው የጋራ እምነት ካለ፤በአንድ ተማሪ ላይ የዚህን ያህል ተፅእኖ ካለው፤ በአገራችን በተለያየ ክፍለ አገር በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች ላይ ድርጊት ቢፈጸም ፣የጉዳቱ መጠን ምን ያህል አስደንቃጭ ሊሆን እንደሚችል ግልፅ ነው፡፡
አሁንም እየተጠየቀ ያለው ፣ተማሪዎች ለአምስት ወራት ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዳይከታተሉ ተደርጓል ፣ለዚህም የመንግስት እጅ አለበት።በመሆኑም ፈተናው አገር አቀፍ እንደመሆኑ መጠን ፣አመቱን ሙሉ ሲማር እና ለአምስት ወር የተማረ ተማሪ እኩል ፈተና ላይ መቀመጥ የለበትም ።ስለዚህም በቂ የፈተና ጊዜ እና የማካካሻ ት/ት ተሰጥቶ ፤ብሔራዊ ፈተና መካሄድ እንዳለበት ነው።ይህ ጥያቄ የማንም መብት የማይጋፋ፣ከምንም በላይ የፈተናው ሚዛናዊነት እንዲጠበቅ የሚያደርግ ነው፡፡
የህውሓት/የኢህአዴግ አንባገነን መንግሥት “የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን” የሚል ስያሜ ሰጥቶ የነበረው እቅድ ተግባራዊነቱ እንዲቆም፣ በህውሓት የሞግዚት አስተዳደር የሚመራው ኦህዴድ መዕከላዊ ኮሚቴ መወሰኑ የሚታወቅ ነው። ድርጅቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የህዝብ ተቃውሞና አለም አቀፍ ማህበረሰብና የውጪ መንግስታት ከፍተኛ ጫና ተከትሎ ነው።በተለይ በአገራችን በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች የህይወት መሰዋዕትነት ሁሉ ከፍለውበታል።
አቶ ኃ/ማርያም ዳሳላኝ በተለያየ ወቅት በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ቀርበው ፣እሳቸውና እና መንግሥታቸው ፤የኦሮሚያ ልዩ ዞን ማስተር ፕላን አስመልክቶ በተከሰተው ነገር ይቅርታ ከመጠየቃቸው በላይ ፣ለይስሙላ የተወሰኑ ባለስልጣናት ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ እና እንዲጠየቁ አስችለናል ሲሉ ተደምጠዋል።ይህን ማድረግ ከተቻለ መንግስት ነኝ ባዮም ኃላፊነት ወስጃለሁ ካለ ፣ለተማሪዎች ተጨማሪ የፈተና ጊዜ እና የማካካሻ ትምህርት ለምን አይስጥም ?! ብሎ መጠየቅ አግባብነት አለው።ተገቢውን መልስ የሚሰጥ የመንግስትነት ቅርጽ ያለው ስርዓት ስለመኖሩ ዋና መሰረታዊ ጥያቄ ነው።የሆነዉ ይሁንና ተብሎ የማይታለፈው ፣ዛሬ የሆነው ነገር ስኬቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ተምሳሌታዊነቱ ለአማራጭ የሰላማዊ ትግል ዘዴ ትልቅ ቦታ ይኖሯዋል።
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!
ግንቦት 22 ቀን 2008 ዓ.ም
ይድነቃቸው ከበደ (እርገጤ)

የብሄራዊ ፈተናው መሰረዝ ለሕዝብ ልጆች ድል ለአገዛዙ የፖለቲካ ኪሳራ ነው:: አንድ እውነት … !!!



አገዛዙ ያልገባው እያወቀ ሊውጠው የማይፈልገው አንድ እውነት አለ::ይህም ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል ሕዝብ ነጻነት ይፈልጋል:: ሕዝብ እኩልነት ይፈልጋል:: ሕዝብ የመንግስት ሌቦችን ተሸክሞ ሊጓዝ በፍጹም አይሻም:: ሕዝብ የፖለቲካና የኢኮኖሚ መብቱ እንዲገፈፍ በፍጹም አይፈልግም::ሕዝብ ከቀየው ከኖረበት በጉልበተኛ የመንግስት ማፊያዎች እንዲፈናቀል አይፈልግም::በወያኔ አገዛዝ እጅግ በርካታ ወንጀሎች በሕዝብ ላይ እየተሰሩ ነው::አገዛዙ አናቱ የገማ ሲሆን ከስሩ ያሉትም አባሎቹ ሳይቀር ለውጥ ይፈልጋሉ::የሕዝብ ልጆች ነጻነትና የመብት ጥያቄ ጎን ብመቆም ታላቅ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ::ይህ ደግሞ ለአገዛዙ የፖለቲካ ኪሳራ ለሕዝብ ደግሞ ድል ነው::የመላው ኢትዮጵያ ተማሪዎች ከኦሮሚያ ክልል ተማሪዎች ጎን ሊቆሙ የወገናዊነት ግዴታ አለባቸው::
Minilik Salsawi's photo.
የወያኔው አገዛዝ ሁሉ ነገር ከእጁ አፈትልኮ ወቷል::ካሁን በኋላ ማስተካከል ስለማይቻል ያለው አማራጭ ስልጣን መልቀቅ ብቻ ነው::የሕዝብ ልጆች ባልተሳተፉበት የመንግስት ስርዓት ውስጥ ዜጎች አያገባችሁም በተባለበት በገዛ አገራቸው ውስጥ ካሁን በኋላ ሕዝብን አስተዳድራለሁ ብሎ ማሰብ ጅልነት እና ሞራለ ቢስነት ነው::ይህን ደግሞ ማናቸውም ኢትዮጵያን እናስተዳድራለን ብለው የሚመኙ ፖለቲከኞች ሊያውቁት ይገባል::የሕዝብ ልጆች የጋራ ትግል ማንኛእንም አምባገነን ስርዓት ገዝግዞ የመጣል አቅሙ ብርቱ ነው::በኦሮሚያ ክልል የተደረጉ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አመቱን በከፊል ከአስተማሪ ጋር ሳይሆን ከፌዴራል ፖሊሶች ጋር ሲፋጠጡ የነበሩ ተማሪዎችን ካለምንም ዝግጅት ፈተና ላይ ለማስቀመጥ ያሰበው አገዛዝ ሊያወትበት ካለመው የተማሪው ሞራል በተጫረ ክብሪት ከባድ እፍረትን ተከናንቧል::
ትግሉ አሁንም ይቀጥላል!!! የሕዝቦች ትግል ተጀመረ እንጂ አላለቀም የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለያዩ ብልሃቶቹ አገዛዙ አያመነመነ በማደባየት ይቀብረዋል::ይህ በፍጹም የማይታጠፍ ሃቅ ነው::ፈተናውን በሰላም ተዘጋጅተው ለመፈተን ያሰቡ ተማሪዎች ፈተናው ሲቋረጥ የሚያሳዝናቸው ከሆነ በገዛ ወንድሞቻቸው ላይ አደጋ መሆናቸውን መዘንጋት የለባቸውም::ፈተናው መቋረጡ ለሃገራቸው መጻኢ እድል አስታውጾ እንደሚያደርግ ሊገባቸው ይገባል::ፈተናው በመቋረጡ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ተማሪዎችን የትግል የስኬት የድል ሞራል ከፍ እንደሚያደርገው ልሊያውቁት ይገባል::ማንም በማንም ላይ ተረማምዶ የልጥላውን መብት ተጋፍቶ ፈተና መቀመጥ ለነገ አደጋ እንደነበረው በመገንዘብ ፈተናው መቋረጡ በመላው አገሪቱ የሚኖሩ የማትሪክ ተፈታኦችን ሊያስደስት ይገባል::ተጀመረ እንጂ አልተቋጨም !!! ከሕዝብ ልጆች ጥያቄ እና እንቅስቃሴ የሚያመልጥ ማንም የለም:: …. የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ብቻ ሳይሆን የአገዛዙም እስትንፋስ መቋረጡን በቅርቡ በራሱ ሚዲያ በሰበር ዜና ትሰማላቹህ::ይህ የኛ የሕዝብ ልጆች ቃል ነው:: ሁሉም ተማሪዎች ከኦሮሚያ ተማሪዎች ጎን ሊቆሙ ይገባል::ድል የሕዝብ ነው::

የሕወሓት መንግስት “እንቁልልጬ” የተሰኘ ዶክመንታሪ ፊልም በኤርትራ መንግስት ላይ ለቀቀ | ለምን በፊልሙ ላይ ግንቦት 7ን መጥራት አልፈለገም?

አርበኞች ግንቦት 7 በአርባምንጭ 20 የመንግስት ወታደሮችን ገደልኩ ባለበት ማግስት ዘ-ሐበሻ ሕወሓት መራሹ መንግስት በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ የራሱን ሰዎች አስጠንቶ ዶኩመንታሪ ፊልም እየሰራ መሆኑን ምንጮቿን ጠቅሳ መዘገቧ አይዘነጋም:: ዛሬ የግንቦት 20 ማግስት የአርበኞች ግንቦት 7ን ስም ሳያነሳ በኤርትራ መንግስት ላይ ዶክመንታሪ ቪዲዮ በፖሊስ ፕሮግራም ላይ ለቆታል:: ለግንዛቤና አስተያየት ይሰጡበት ዘንድ አቅርበነዋል::
ይህን ፊልም ከማየታችሁ በፊት ከዚህ ቀደም ትግራይ ሆቴልን አፈነዱ ተብለው በቴሌቭዥን የታዩትን እና አፈንድተናል ብለው የተናገሩትን የ’ኦነግ አባላት’ ተብለው በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ታይተው በኋላም ተስፋዬ ገብረአብ ደቡብ አፍሪካ ሲሰደድ እነዚህን ወገኖች እዛው አገኘኋቸው ማለቱን ያስታውሷል::
የሚገርመው በቪዲዮው ላይ ተያዙ ተብለው የቀረቡት የጺማቸው አቆራረጥ እስረኛም አያስመስላቸውም። አንዱ ደግሞ “[መያዛችንን] ባውቅ ኖሮ እዚህ ውስጥ አልገባም ነበር” እያለ ድራማው ድራማ መሆኑን ይነግረናል::
በነገራችን ላይ በዚህ ዶክመንታሪ ፊልም ላይ መንግስት የአርበኞች ግንቦት 7 ለአርባ ምንጩ ጥቃት ኃላፊነቱን ወስዶ እያለ ለምን የግንባሩን ስም ለምን መጥራት አልፈለገም?

አርከበ እቁባይ የራሳቸውን ሞራል እየገነቡ ነው

(ዘ-ሐበሻ) “የመለስ ራዕይ የሚባል በቃ” ሲሉ እየተከራከሩ ቆይተዋል የሚባሉት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘ልዩ’ አማካሪ አቶ አርከበ እቁባይ “Made in Africa industrial policy in Ethiopia” የተሰኘውና በርሳቸው ስም ይጻፍ እንጂ እርሳቸው ይጻፉት አይጻፉት ያልተረጋገጠውን መጽሐፋቸውን ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስተማሪያነት በስጦታ መልክ አብርክቻለው በሚል ዜናውን በሚያዟቸው ሚዲያዎች በማስነገር በመገባት ላይ ናቸው::
“Made in Africa industrial policy in Ethiopia” የተሰኘውና በአቶ አርከበ ስም የወጣው መጽሐፍ አቶ አርከበ እንዳልጻፉት እየተነገረ ቢሆንም ዘ-ሐበሻ ለዚህ ጉዳይ ማረጋገጫ ማግኘት አልቻለችም:: ሆኖም ግን የመጽሐፉ ጸሐፊ ነኝ ያሉት አቶ አርከበ ከ20 በላይ ለሚሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት “መጽሐፋቸው” ለማስተማሪያነት እንዲውል ማበርከታቸውን በከፍተኛ የመንግስት ሚድያዎች እንዲዘገብ አድርገዋል::
ከዚህ ቀደም በርካታ ጥልቅ እውቀትን የያዙ መጽሐፍ የጻፉ ወገኖች መጽሐፍቶቻቸውን ለክፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለማስተማሪያነት ቢያበረክቱም እንደ አቶ አርከበ የመንግስት ሚዲያ ሽፋን ሳያገኙ ቀርተዋል::

መኢአድ ከ”አንድነት” ጋር አድርጎት የነበረውን ስምምት አጸደቀ- የሚሊዮኖች ጽምጽ

መኢአድ ከ”አንድነት” ጋር አድርጎት የነበረውን ስምምት አጸደቀ- የሚሊዮኖች ጽምጽ
መኢአድ አዲስ አመራር መርጧል። የአንድነት ሴንትሪስት ፕሮግራም ፕሮግራሙ አድርጎ አጽድቋል፡
በምርጫ ቦርድ የፖለቲካና የደርጅቶች ጉዳይ ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ አክሊል እና አቶ ዮሴፍ የተባሉ የምርጫ ቦርድ ታዛቢ በተገኙበት መኢአድ ጠቃላላ ጉብዬውን ዛሬ ግንቦት 21 ቀን 2008 ዓ.ም አድርጓል።
ከአንድ አመት ተኩል በፊት መኢአድ አድርጎት በነበረው ጠቃላላ ጉባዬ በተፈጠሩ አለመስማማቶች ምንክያት ፓርቲው ገፍቶ ሊሄድ አለመቻሉ ይታወቃል። ለፓርቲው አንድነት እና ጥንካሬ ሲባል አቶ አበባው መሐሪ ራሳቸውን ለሊቀመንበርነት ምርጫ እጩ አድርገው ስላላቀረቡ፣ ጉብዬው ላበረከቱት አስተዋጾ ምስጋናውን አቅርቦ በክብር ሸኝቷቸዋል።
ጠቅላላ ጉብዬው የተጀመረው ምርጫ ቦርድ ኮረም መሙላቱን ካረጋገጠ በኋላ ሲሆን በአጠቃላይ ከሚያስፈለገው 300 አባላት ወደ 320 የሚሆኑ ጠቅላላ ጉብዬዉን ተካፍለዋል። ጠቅላላ ጉብዬው አዲስ የአመራር አባላትን ከመምረጥ በተጨማሪ ፣ የፕለቲካ ፕሮግራም እና የደርጅቱ ሕገ ደንብ ማሻሻያዎችን አድርጓል።
ከሁለት አመታት በፊት አንድነት እና መኢአድ ዉህደት ለመፈጸም ስምምነቶች አድርገው ሕግወ ወጥ በሆነ መልኩ ዉህደቱን ምርጫ ቦርድ ማጨናገፉ ይታወቃል። ያንን አሳዛኝ ክስተት በማስታወስ ፣ ከሰሜን ሸዋ ፣ ደብረ ብርሃን የመጡ ፣ አቶ ወርቁ ተገኑ የተባሉ ሰው፣ በስብሰባው ለተገኙ የምርጫ ቦርድ ታዛቢዎች ፊት ምርጫ ቦርድን ኮንነዋል።
በወቅቱ በተደረገው ስምምነት የአንድነት ፓርቲ ሴንትሪስት ፕሮግራም የዉህዱ ፓርቲ ፕሮግራም እንዲሆን፣ የመኢአድ ሕግ ደንብ ደግሞ የዉህዱ ፓርቲ ደንብ እንዲሆን ነበር የተወሰነው። በዚያ መሰረት፣ አሁን የሚዋሃድ ኦፌሴላዊ የሆነ የ”አንድነት” ፓርቲ ባይኖርም፣ የመኢአድ ጠቃላላ ጉብዬ የአንድነት ፕሮግራም የመኢአድ ፕሮግራም እንዲሆን ወስኗል።
የየነበረዉን የመኢአድ ደንብ በማሻሻል የጠቅላላ ጉብዬውን አባላት ቁጥር ከ600 መቶ ወደ 334፣ የብሄራዊ ምክር ቤት አባላትን ቁጥር ከ105 ወደ 81 ዝቅ አደርጎታል።
ጠቃላላ ጉብዬው ባደረገው ምርጫ፣ አቶ አበባው መሐሪ ተክተው፣ በቅንጅት ጊዜ የላእላይ ምክር ቤት አባል የነበሩ፣ ከአንጋፋ የመኢአድ አመራር መካከል የሚቆጠሩት ዶር በዛብህ ደምሴ ተመርጠዋል።
በመምህርነት ያገለገሉ፣ ከፍተኛ ትምህርቶች በጀርመን እና በኮሪያ የወሰዱና የማስተርስ ዲግሪ ያላቸው፣ አቶ አሰፋ ሃብተወልድ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡ ሲሆን፣ የተዎሎጂ ምሩቅ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ አበባ ደግሞ ም/ሊቀመንበር ሆነዋል። የሕግ ባለሞያ የሆኑትና ከስሜን ወሎ የመጡት አቶ አዳነ ጥላሁን የመኢአድ ዋና ጸሃፊ ሆነው ተመርጠዋል።
በተጨማሪም ጉብዬ 50 የላእላይ ምክር ቤት አባላትን መርጧል። ከ31 የአገሪቷ ዞኖች ፣ ዞኖችን ወከለው የመጡ አባላት፣ በመኢአድ ደንብ መሰረት በቀጥታ፣ በዞን ሃላፊነታቸው የላእላይ ምክር ቤት ናቸው። ባጠቃላይ ምክር ቤቱ 81 አባላት ይኖሩታል።
ዶር በዛብህ ደምሴ በሥራ አስፈጻሚ ዉስጥ የሚሰሩት ሌሎች አባላት መርጠው በምክር ቤቱ በቅርብ ያጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዶር በዛብህ ቀዳሚ ተግባራቸው በተለያዩ ምክንያት ከፓርቲው የተለዩትን ማሰባሰብ እንደሆነ የደረሰንዝ ዘገባ ይጠቁማል።
ከአንድነት ጋር የተደረጉ ስምምነቶች መኢአድ ማጽደቁ፣ በርካታ የቀድሞ የአንድነት አባላትና አመራሮች መኢአድን ይቀላቀላሉ ተብሎም ይጠበቃል።

ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ በDropbox እና ሶሻል ሚድያዎች ተሰራጨየ


የሱፍ ጌታቸው's photo.
በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ የ12ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ ሰኞ እንደሚካሄድ ቀነ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረ ሲሆን ሆኖም ግን ፈተናው ተሰርቆ ቀድሞ በኢንተርኔት መሰራጨቱ ታወቀ:: በDropbox አማካኝነት እንዲሁም በፌስቡክ እና በሌሎች ሶሻል ሚድያዎች ፈተናው ተሰራጭቶ የሚገኝ ሲሆን መንግስት ግን ምንም ዓይነት ፈተና አልተሰረቀም ሲል በሚያዛቸው ሚዲያዎቹ አውጇል::

Sunday, May 29, 2016

ሜ/ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት ለኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ኦነግ፣ ሲነግ ክሬዲት ሰጡ – “ተወልደ፣ ፃድቃን፣ ስዬና ተፈራ ዋልዋ ስለአሰብ ጥያቄ ያነሱ ነበር” አሉ

 በሕወሓት ክፍፍል ወቅት ስልጣናቸውን እንዲያጡ የተደረጉት የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለ ሃይማኖት ደርግን ለመጣል ለተደረገው ትግል ኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ኦነግ፣ ሲነግና ወዘተ አስተውጽኦ እንደነበራቸው ተናገሩ:: ጄነራሉ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ግንቦት 20ን በማስመልከት ባደረጉት ንግግር ስለአሰብ ወደብ ጉዳይም ተናግረዋል::
“ድሮም ቢሆን የኤርትራን ነፃነት ተቀብለው የአሰብ ጉዳይ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች ነበሩ። እንደነ አቶ ተወልደ ወልደ ማርያም፣ ሌተና ጄኔራል ፃድቃን ገብረ ትንሳኤ፣ አቶ ስየ አብርሃ፣ አቶ ተፈራ ዋልዋ፣ እኔም ጥያቄዎች የምናነሳበት ሁኔታ ነበር፡፡ በዝርዝር ባንወያይበትም። አሜሪካ ሄጄ ሁለተኛ ዲግሪዬን ስሠራ ግን በዚህ ላይ ጥናት አካሂጄ የባህር በር መብታችንን በሕጋዊ መንገድ ማስመለስ እንደምችል የሚያረጋግጥ ድምዳሜ ላይ ደረስኩ። ባለማወቅና በመታበይ (Ignorance and arrogance) ያጣነው መብት ነው፡፡ አሁንም ግን ሕጋዊ መሠረት አለን፡፡”
ያሉት ጀነራሉ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል::
አሁን እየተነሱ ባሉት የህዝብ እንስቅቃሴዎች ዙሪያ ከሪፖርተር:-
“ሕዝባዊ አመፅ እየታየ ያለው በተካሄደው ምርጫ ገዢው ፓርቲ መቶ በመቶ ማሸነፉን በገለጸበት ማግሥት ነው፡፡ ይህን ያህል የሕዝብ ተቃውሞ መነሳቱ በምርጫ ሒደቱ ላይ ጥያቄ አያስነሳም?” የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ሜጀር ጀነራል አበበ ” የመንግሥትና የፓርቲ መዋቅሮች መደባለቅ አንዱ ትልቅ ችግር ነው። ኢሕአዴግ የመንግሥት ሚድያ፣ የመንግሥት ቢሮ፣ ገንዘብና አሉ የሚባሉ እርከኖችን ለፓርቲ ሥራ ስለሚያውል የፉክክር ሜዳው ዴሞክራሲን የሚያስችል (democracy enabling) እንዳይሆን አድርጎታል። ቻርለስ ቲሊ የሚባል ታላቅ የፖለቲካ ሳይንቲስት አንድ ፓርቲ ከሰባ አምስት በመቶ በላይ የፓርላማ መቀመጫዎችን ለብቻው ከያዘ ገና ከወዲሁ ዴሞክራሲያዊና ፍትሓዊ ያልሆነ፣ በሕዝብ ተቀባይነት የሌለው ምርጫ ነው ማለት ይቻላል ይላል። ምክንያቱም አንድ ሕዝብ ከፋብሪካ እንደሚወጣ ወጥ ምርት አይደለም። የተለያየ ፍላጎት፣ ምርጫና ዝንባሌ ስለሚኖረው። አሥር በመቶ እንኳ ተቃዋሚዎች ቢያሸንፉ መሬት ላይ ያለውን ሀቅ አያንፀባርቅም። የፌዴራሊዝም ባለሙያዎችና አገራዊ የውክልና ተቋማት ሕዝቡ ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን ማንፀባረቅ አለባቸው ይላሉ። ስለዚህ ኢሕአዴግ አሽነፍኩ ያለበት ሒደትም የታወጀው ውጤትም አስቂኝ ብቻ ሳይሆን አደገኛም ጭምር ነው። ውጤቱ ሲነገር ስቀን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ አደጋው ፈጦ እያየነው ነው። ኢሕአዴግ ማሸነፍ አይችልም ነበር እያልኩ አይደለም፡፡”
ብለዋል::
ቃለምልልሱን እንደወረደ ለግንዛቤ እንዲረዳዎ እንደሚከተለው አቅርበነዋል:-

ሪፖርተር፡- መድበለ ፓርቲ ሥርዓትና ተቋማዊ አሠራር ከመገንባት አንፃር አሁን መሬት ላይ ያለው አሠራር ከሕገ መንግሥቱ ጋር ሲታይ ምንይመስላል?
ጄኔራል አበበ፡- በጣም ዘመናዊ ሕገ መንግሥት አለን። ሕገ መንግሥቱ ግሎባላይዜሽን፣ የሌሎች አገሮች ተሞክሮና የራሳችን ሁኔታ ታሳቢ አድርጎ የወጣ ነው። ነገር ግን ፍፁም ነው ማለት አይደለም። በመሠረቱ ሲታይ ግን ሕገ መንግሥቱ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ፍላጎትን ያሟላ ነው። መስተካከል ያለበት ነገርም ሊኖር ይችላል። አሁን ትልቁ ችግር ያለው በተግባር ማዋል ላይ ነው። የሕገ መንግሥት ተቋማት ነፃነት የተጠበቀ አይደለም። በእኔ ግምገማ ሁሉንም ሥልጣን የያዘው አስፈጻሚው አካል ነው። የተወካዮች ምክር ቤት ከሚጠበቀው አንፃር ሲታይ ብዙ መሠረታዊ ችግሮች አሉበት። በሕገ መንግሥቱ የበላይ አካል ተቆጣጣሪ ሆኖ እያለ በተግባር ግን ሥራ አስፈጻሚ የሚያዘውን የሚፈጽም ነው፡፡ በተመሳሳይ ፍርድ ቤትም እንደዚያው ነው። በተለይ መንግሥትና ፓርቲ አንድ የሆኑበት አሠራር ነው ያለው። መለያየት አለበት። ይህ በጠቅላላ ሕገ መንግሥቱን የሚንድ አሠራር ነው። ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ህልውናም ትልቅ አደጋ ነው። ኢሕአዴግ መንግሥት በመያዙ ለአደጋው ዋና ድርሻ ቢኖረውም በአጠቃላይ ሲታይ ግን አብዛኛዎቹ ተቃዋሚዎችም ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸው ናቸው። ሕገ መንግሥትን መሠረት አድርገው፣ በሕገ መንግሥቱ ያሉት ተቋማትን ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ ትልቅ ክፍተት ይታያል። አሁን ያለው መንግሥት ‹‹ከእኔ በላይ ማን አለ?›› የሚል እብሪትም ያለበት መንግሥት ነው። የዴሞክራሲ ምኅዳር እያጠበበ እያጠበበ ሄዷል። ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እየተገደበ ነው ያለው። አሁን ያሉትን ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንደ ፀጋ አያይም፡፡ ኢሕአዴግ የተደራጀ የሕዝብ እንቅስቃሴ ሥጋት ይሆንበታል። ስለዚህ ፓርቲዎችን የማዳከም ሥራ ነው የሚሠራው። ይህም ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት አደጋ ነው።
ከተቋማት አኳያ ሲታይም በተለይ ፖለቲካዊ ተቋማት እንደ ፓርላማ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ጠንካራ ናቸው ለማለት የሚከብድ ነው። ተቋማቱ ያረጁ ናቸው። ይኼ ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትና ለዴሞክራሲ አደገኛ ነው። ስለዚህ ገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎችን እንደ ፀጋ ዓይቶ አብሮ የሚሠራበትንና ተቃዋሚዎች የሚጠናከሩበትን ሁኔታ መፍጠር አለበት። የፕሬስ መብትን ማረጋገጥም አለበት፡፡ በተለይ የተደራጀ ሕዝብ ተቃውሞ በሚያሰማበት ጊዜ ይህን እንደ ትልቅ ሀብት ዓይቶ መደገፍና ሕዝቡን ሰምቶ የሕዝቡን ፍላጎት በተሻለ ለሟሟላት መንቀሳቀስ አለበት። አሁን የስኳር ኮርፖሬሽንን ስናየው 77 ቢሊዮን ብር ያህል የሚያንቀሳቅስና በቀጥታ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራ ድርጅት ነው፡፡ እንዴት ነው አንድ ትልቅ በጠቅላይ ሚኒስትር የሚመራን ድርጅት ማን ነው የሚያስፈራራው? እነዚህ ሰዎችስ ማን ናቸው? በስኳር ያለው ችግርም በሌሎች ትልልቅ ፕሮጀክቶች ላይ እንዳለ ባለሙያዎች መረጃ አላቸው። ለምሳሌ ግልገል ጊቤ ሦስት እስከ አሁን ለምን ተጓተተ? የሥራው ጥራትስ ምን ያህል ነው? አሁን የምንፈልገውን ኃይልስ አግኝተናል ወይ? በህዳሴ ግድብ ላይም ቢሆን ብዙ ባለሙያዎች ጥያቄዎችና ሥጋቶች ያነሳሉ።
ሪፖርተር፡- የትጥቅ ትግል ከማካሄድና ሲቪል መንግሥት ሆኖ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ከመገንባት የቱ ይከብዳል ይላሉ?
ጄኔራል አበበ፡- የትጥቅ ትግል የፀረ ዴሞክራሲ ዘበኛን ለማስወገድ የሚካሄድ ትግል ነው፡፡ ስለዚህ የትጥቅ ትግል በኃይል የሚደረግ በመሆኑ በባህሪው ከዴሞክራሲ ጋር ግጭት ሊኖረው ይችላል። ምክንያቱም ማስገደድ ይኖረዋል።  ይህ የፀረ ዴሞክራሲ ዘበኛ በሕዝባችን ትግል ከተወገደ በኋላ በሽግግር መንግሥት ቻርተርና ቀጥሎ በመጣው ሕገ መንግሥት በኩል ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መንደርደርያ የሚሆን ሥራ ተሠርቷል። በዚህም የሕዝቦች መሠረታዊ ጥያቄ ለመፍታት ትልቅ ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ብዙ ያልተሻገርናቸው ፈተናዎች አሉ። በመጀመርያ ኢሕአዴግ ራሱን መቀየር ነበረበት። የትጥቅ ትግል አስተሳሰብና የአገር ግንባታ አስተሳሰቦች መሠረታዊ ልዩነት አላቸው። ኢሕአዴግ ራሱን ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግብዓት ከሆኑ እሳቤዎች ጋር አጣጥሞ የሄደ አይመስለኝም። ኢሕአዴግ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የእኛ ትውልድ የአማፂ ትውልድ ነው። የአማፂ ትውልድ የዴሞክራሲ ትውልድ መሆን አይችልም። ስለዚህም ሌሎች ፓርቲዎችም ራሳቸውን በሕገ መንግሥቱና በዓለም ላይ ካሉ ዘመናዊ እሳቤዎች ጋር ማጣጣም ይኖርባቸዋል። የእኛ ትውልድ ከራሱ እሳቤና ተግባር ውጪ ያለን አካል መብት የማያከብር ‹‹እኔ ብቻ ነኝ ልክ›› የሚል አክራሪነት የሚታይበት ትውልድ ነው። ተማሪ ሆነን ሰላማዊ ሠልፍ እንውጣ በምንልበት ጊዜ እምቢ የሚል ተማሪ ካለ ይመታል፡፡ ይህ በመሠረቱ ኢዴሞክራሲያዊ አካሄድ ነው። እንጭጭነትም ነው። ስለዚህ የኛ ትውልድ የዴሞክራሲ ትውልድ አይደለም፡፡ የአመፅ ትውልድ ነው፡፡ የፀረ ዴሞክራሲ ዘበኛ የነበረን ሥርዓት ግን በማስወገዱ እኮራበታለሁ።  ከዚያ በኋላ  አዲሱ ትውልድ ተረክቦ መሄድ ነበረበት፡፡ ሆኖም የእኛ ትውልድ አሁንም ሥልጣንን የሙጥኝ ብሎ አልለቅም በማለቱ አሁን ለሚታየው ቀውስ ምክንያት ሆኗል።
ሪፖርተር፡- ምን ማለት ነው ‹‹የሙጥኝ ብሏል›› ሲሉለምሳሌ ኢሕአዴግ ውስጥ መተካካት እየተደረገ እንደሆነ ይሰማል፡፡ የመተካካቱን ሒደት አላመኑበትም?
ጄኔራል አበበ፡- መተካካት ሲባል የትውልድ መሆን አለበት፣ የግለሰቦች አይደለም። የአሁኑ ትውልድ ብቃት ያለው ትውልድ ነው። ገና ሲወለድ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የሚያውቅ፣ ከመንግሥት የተለዩ ጋዜጦችንና መጽሔቶችን የሚያነብ፣ የተለያዩ ሐሳቦችን የሚያውቅ፣ ዓለም አቀፍ ትስስር ያለው፣ በምርምር ብዙ ነገር ማድረግ የሚችል ትውልድ ነው። ስለዚህ መተካካት ሲባል የትውልድ መጎራረስ ነው። ካለፈው ትውልድ በጎ በጎውን ተምሮ የራሱን ጥበብ ጨምሮበት እንደ ትውልድ አገሩን ሲረከብ ነው መተካካት የሚባለው።
ሪፖርተር፡- ‹‹የዴሞክራሲ ምኅዳሩ እየጠበበ ነው›› ብለዋል፡፡ ‹‹ኢሕአዴግን ባልመጣበት የሰላማዊ ትግል መድረክ ማሸነፍ ስለማይቻል አዋጪውየትጥቅ ትግል ነው››የሚሉ ተቃዋሚዎች አሉ። የእርስዎ ግምገማ ምን ይመስላል?
ጄኔራል አበበ፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ለውጥ እየተመዘገበ ነው። ይህ ለዴሞክራሲው ምን ማለት ነው የሚለው በደንብ መታየት አለበት። መንገድ ተሠራ ሲባል ሕዝቦች የሚገናኙበት፣ አንዱ የአንዱን ባህል የሚማርበት ዕድል ሰፋ ወይም ተፈጠረ ማለት ነው። ስለዚህ የትብብርና የአስተሳሰብ አድማሱ የሚሰፋበት ዕድል አለ ማለት ነው። የውኃ አገልግሎት ተሠራ ማለት ያቺ ሚስኪን ሴት አራት አምስት ሰዓታት ለውኃ የምታጠፋውን ጊዜ ትቆጥባለች ማለት ነው። ጤና ኬላ ተሠራ ማለት ጤንነቱ የተጠበቀ ልጅ መማር ይችላል ማለት ነው። የአንደኛ ትምህርት መስፋፋት ማለት እኮ ለዴሞክራታይዜሽን ሰፊ ምንጣፍ እየተነጠፈ ነው ማለት ነው። አባትም፣ እናትም ልጅም ለፖለቲካዊ ተሳትፎ የሚሆን ጊዜ አገኙ ማለት ነው። በአጠቃላይ ማኅበረ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታው እየተቀየረ ነው፡፡ ፖለቲካዊ ፍላጎቱ የሚጨምር ትውልድም እየተፈጠረ ነው። እዚህ ላይ ቅራኔ አለ፤ ሆኖም ይህንን ቅራኔ መፍታት የሚችል ትውልድ እየመጣ ነው፡፡ ይህ ትውልድ ያጣው ቦታ ብቻ ነው። በትጥቅ ትግል ዴሞክራሲን ማስፈን የሚለው ነገር አስቂኝ ነው። ትጥቅ ትግል ለዚህች አገር አይረባም፣ በጣም አደገኛ ነገር ነው። የዴሞክራሲ ምኅዳሩ እየጠበበ መሄዱ ወደ ትጥቅ ትግል እንድትገባ ምክንያት ሊሆን አይችልም። በዚህ ጠባብ ሁኔታም ጭምር ጠንካራና እውነተኛ ፖለቲካዊ አመራር መስጠት የሚችል ካለ መታገል ይቻላል፡፡ ስለዚህም ነው በርካታ ዜጎች አገር ውስጥ እየታገሉ ያሉት። ምክንያቱም ሕዝቡ በቦታው ነው።
የኢትዮጵያ ዴሞክራታይዜሽን በኢሕአዴግ ፈቃድ ላይ የሚመሠረት ነገር አይደለም። በተወሰነ ሁኔታ ኢሕአዴግ ጥሩ በሚሆንበት ጊዜ ሒደቱን ሊያፋጥነው ይችላል ወይም በተቃራኒው ሊሆን ይችላል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኢሕአዴግን ፈቃድ መጠየቅ የለበትም። ሕዝቡ ይህንን ሥርዓት ያመጣው በራሱ ትግል ነው፡፡ የሚያስቀጥለውም ሕዝቡ ራሱ ነው። የ1997 ዓ.ም. ክስተት ሕዝብ ካመፀ ምን ማድረግ እንደሚችል ደንበኛ ማሳያ ነው። አሁን በኦሮማያና በትግራይ እምባሰነይቲ አካባቢ እየታየ ያለው የተደራጀ ሕዝባዊ የመብት ጥያቄ አለ። በሁሉም የሚታይ ባይሆንም አሁንም ኢሕአዴግ ውስጥ ሁሉንም ነገር በኃይል ለመፍታት የመፈለግና የመሞከር አዝማሚያ ይታያል። ይህንን የትጥቅ ትግል አስተሳሰብ አሽቀንጥረው መጣል አለባቸው። ምኅዳሩም ፍፁም ዝግ አይደለም፡፡ ጠባብ በመሆኑ ግን ብዙ መስዋዕትነትና ዋጋ ይጠይቃል።
ሪፖርተር፡- ሕዝባዊ አመፅ እየታየ ያለው በተካሄደው ምርጫ ገዢው ፓርቲ መቶ በመቶ ማሸነፉን በገለጸበት ማግሥት ነው፡፡ ይህን ያህል የሕዝብ ተቃውሞ መነሳቱ በምርጫ ሒደቱ ላይ ጥያቄ አያስነሳም?
ጄኔራል አበበ፡- የመንግሥትና የፓርቲ መዋቅሮች መደባለቅ አንዱ ትልቅ ችግር ነው። ኢሕአዴግ የመንግሥት ሚድያ፣ የመንግሥት ቢሮ፣ ገንዘብና አሉ የሚባሉ እርከኖችን ለፓርቲ ሥራ ስለሚያውል የፉክክር ሜዳው ዴሞክራሲን የሚያስችል (democracy enabling) እንዳይሆን አድርጎታል። ቻርለስ ቲሊ የሚባል ታላቅ የፖለቲካ ሳይንቲስት አንድ ፓርቲ ከሰባ አምስት በመቶ በላይ የፓርላማ መቀመጫዎችን ለብቻው ከያዘ ገና ከወዲሁ ዴሞክራሲያዊና ፍትሓዊ ያልሆነ፣ በሕዝብ ተቀባይነት የሌለው ምርጫ ነው ማለት ይቻላል ይላል። ምክንያቱም አንድ ሕዝብ ከፋብሪካ እንደሚወጣ ወጥ ምርት አይደለም። የተለያየ ፍላጎት፣ ምርጫና ዝንባሌ ስለሚኖረው። አሥር በመቶ እንኳ ተቃዋሚዎች ቢያሸንፉ መሬት ላይ ያለውን ሀቅ አያንፀባርቅም። የፌዴራሊዝም ባለሙያዎችና አገራዊ የውክልና ተቋማት ሕዝቡ ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን ማንፀባረቅ አለባቸው ይላሉ። ስለዚህ ኢሕአዴግ አሽነፍኩ ያለበት ሒደትም የታወጀው ውጤትም አስቂኝ ብቻ ሳይሆን አደገኛም ጭምር ነው። ውጤቱ ሲነገር ስቀን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ አደጋው ፈጦ እያየነው ነው። ኢሕአዴግ ማሸነፍ አይችልም ነበር እያልኩ አይደለም፡፡
ሪፖርተር፡- እየታየ ያለው የአስተዳደር ቀውስ የሥርዓት ችግር (Systemic Problem) ነው ብለው በቅርቡ በጻፉት ጽሑ ላይ ተከራክረውነበር። በመፍትላይም የሰጡት አስተያየት ነበር። ሥርዓታዊ ችግር ሲሉ ምን ማለትዎ ነው?
ጄኔራል አበበ፡- መንግሥት ችግራችን የመልካም አስተዳደር ነው ብሎ ትልቁን ምሥል ወደ ጎን ትቶ ነገሩን ወደ ቴክኒካዊ ደረጃ አውርዶ ነው እያየ ያለው። እየተወሰደ ያለው ዕርምጃም ሥርዓቱን እንደ ሥርዓት የሚገመግምና የሚያስተካክል ሳይሆን፣ ታችኛው አመራርና ሲቪል ሰርቫንቱን ማዕከል ያደረገ ቁንፅል ነገር ነው። እኔ ደግሞ የምለው ‹‹ችግሩ ተራ የአስተዳደር ችግር ሳይሆን አጠቃላይ የዴሞክራሲ እጥረት የሚባል ነገር ነው፣ በአጭሩ ጉዳዩ የዴሞክራታይዜሽን ችግር ነው፤›› ነው። ጉዳዩ ሕገ መንግሥታዊ ተቋማትና አሠራሮች ከመሥራት ወይም ካለመሥራታቸው የተያያዘ ነው። ቀላል ነገር አይደለም። መዋቅራዊ ችግርን አድበስብሶ ማለፍ ውጤቱ እስከ አገር ማፍረስ ሊዘልቅ ይችላል፡፡ ነገርየውን መመርመርና መፈተሽ ያለብንም ከዚህ አቅጣጫ ነው። ከሁሉም በላይ ግን የሕዝቡን የተደራጀና የተናጠል ትግል ለማፈን የሚደረጉ ነገሮች ስለችግራችን ስፋትና ዓይነት ብዙ ነገር ይነግሩናል።
ሲቪል ማኅበረሰቡም ቢሆኑ የፓርቲ ተቀጥያ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ያለው፡፡ ሥራ ለማግኘት አባልነትና ድጋፍ መለኪያ ሲሆን ጉዳዩ የሕገ መንግሥት ጥሰት መሆኑን መገንዘብ አለብን። ለምሳሌ ኦሮሚያ ውስጥ የተነሳውን ሕዝባዊ አመፅ ብንመለከት ለዴሞክራሲ ትልቅ ግብዓት ይሆን ነበር፡፡ መንግሥት ብስለቱና ብልኃቱ ስለሌለው በተወሰነ መልኩም ቢሆን ፅንፈኞችና አክራሪዎች ሕዝቡ በማይፈልገው መንገድ ለመጠቀም ችለዋል፡፡
እነዚህ ኋላቀር ፅንፈኞች ደግሞ ይህንን ተገቢ ትግል በሕዝቦች መካከል ጥርጣሬ እንዲሰፍንና ግጭት እንዲቀሰቅሱበት ለመጠቀም ሞከሩ፡፡ በተወሰነ ደረጃም ተሳካላቸው። ጥያቄው ሕዝቡ ወዳልፈለገው አቅጣጫ ለመውሰድ የሞከሩ ፅንፈኞች የአቅማቸውን ያህል ቢጥሩም የሕዝቡ ጨዋነት ግን የሚገርም ነበር፡፡ ይህ ጨዋ ሕዝብ ላይ የደረሰው ሞት፣ የአካል ጉዳትና ውድመት በጣም አሳዛኝ ነው። ከዚህ ሒደት የምንማረው በገዢው ፓርቲና በሕዝቦች መካከል ትልቅ ክፍተት እንዳለ ነው። ሕዝቦች በገዢው ፓርቲ መሪነት አንድ ትልቅ ደረጃ ላይ ደርሰዋል፡፡ ኢሕአዴግ ግን  ቆሟል ወይም ወደኋላ እየነጎደ ነው። ከሕዝቦች ፍላጎትና ዕድገት ጋር አብሮ መሄድ አልቻለም።
ሪፖርተር፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ‹‹ሕዝቡን አስለቅሰነዋል፣ በድለነዋል›› ብለዋል።ይቅርታምጠይቀዋል።
ጄኔራል አበበ፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ እንደዚያ ማለታቻው የሚመሠገን ተግባር ነው፡፡ አንድ ዕርምጃ ወደፊት መሄድ ነው። በኮሙዩኒኬሽን ሚኒስትሩ በኩል የሚገለጸው ነገርም አንዳንዴ ተስፋ የሚሰጥ ነው። ይቅርታ ማለት ሕዝብን ማክበር ነው፣ ትልቅነት ነው። ይቅርታ ማለት መጀመሩ በራሱ እንደ ትልቅ ነገር አድርጌ ነው የምቆጥረው። ለዚህም ማመስገን እፈልጋለሁ። ይቅርታ ብቻውን ግን በቂ አይደለም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ችግሩ መላውን ኢትዮጵያ የሚያስለቅስ ከሆነ ነገሩ ሥርዓታዊ ነው ማለት ነው። ዋናው ጥያቄ መሆን ያለበትም ይህ ችግር ከየት ይመነጫል የሚለው ነው። የፍትሕ መጓደል፣ ሙስና፣ አስተዳደራዊ በደል በተለያየ መጠን ይኖራሉ፡፡ ሆኖም የዴሞክራሲ ምኅዳሩ ሲጠብ ችግሮቹ ይጎለብታሉ፡፡ በተቃራኒው የዴሞክራሲ ምኅዳሩ ሲሰፋ ችግሮቹ ይቀጭጫሉ፡፡ ምክንያቱም ሕዝቡ ይሳተፋል፡፡ በሰላማዊ ሠልፍ፣ ሐሳቡን በነፃነት በመግለፅ፣ በነፃ በመደራጀትና በመሳሰሉት ይሳተፋል። ኢዴሞክራሲያዊ ኃይሎችና ክራይ ሰብሳቢዎችን ይታገላቸዋል ማለት ነው፡፡ ለግላዊና ለቡድናዊ መብቱ ዘብ ይሆናል ማለት ነው። ስለዚህ ችግሩን ሲገመግሙ ከላይ ከቁንጮው ነበር መገምገም የነበረባቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የቀረበው ጥናት ጥሩ ነበር፡፡ ቀጣይ ዕርምጃዎቹ ግን መሠረታዊ ስህተት ነበረባቸው፡፡ ከላይ መጀመር ሲገባው የሆነው በተገላቢጦሽ ነበር።
ሪፖርተር፡- ‹‹በተገላቢጦሽ›› ሲሉ ምን ለማለት ነው?
ጄኔራል አበበ፡- ጥናቱ መገምገም የነበረበት መዋቅራዊ ጉዳዮችን በማንሳት ነበር። በፓርቲና በመንግሥት መካከል ያለው ግንኙነት፣ የዳኞች አሿሿም፣ የከፍተኛ ባለሥልጣናት የምልመላና የግምገማ ሥርዓት፣ በፓርላማውና በሥራ አስፈጻሚው መካከል ስላለው ግንኙነት፣ የሚዲያው ሁኔታ፣ የፍርድ ቤቶች ነፃነት ነበር መገምገም የነበረበት፡፡ በፓርቲውና በሕገ መንግሥቱ መካከል የሐሳብ ቅርበት ወይም ልዩነት አለ ወይ ብሎ መገምገም ነበረበት። ነፃ የሆኑ የሕዝብ አደረጃጀት አለ ወይ? የግል ፕሬሱና ሲቪል ማኅበረሰቡ በነፃ ይንቀሳቀሳሉ ወይ? ፓርቲዎቹስ መተንፈሻ አግኝተዋል ወይ ብሎ መታየት አለበት። ሲጠቃለል ሕዝቡ ትርጉም ያለውና በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ተሳትፎ እንዲያደርግ የሚያስችል ሁኔታ አለ ወይ ብሎ ነው መገምገም ያለበት። በአስገዳጅ ስብሰባዎች እጅ እንዲያወጣ ማድረግ አይደለም ተሳትፎ ማለት። አንዳንድ በጎበኘሁዋቸው አካባቢዎች ‘አንድ ለአምስት’ የሚባል አደረጃጀት አደገኛ የስለላ መዋቅር እየሆነ ነው። ማኅበራዊ እሴቶቻችንን የሚበጣጥስና ማኅበራዊ ኑሮን ሊያናጋ በሚችል መንገድ ሥራ ላይ እየዋለ ሳይ በጣም ደንግጬያለሁ። ባልና ሚስት፣ ልጆችና ወላጆች በአጠቃላይ ቤተሰብ ቤተሰቡን የሚሰልልበትና የሚያስፈራራበት አሠራር እየሆነ ያለበት አጋጣሚ ስላለ ቆም ብሎ ማሰብ ይጠይቃል። ቤተሰብን ይበትናል። አደረጃጀቱም በኃይል ስለሆነ ግለሰባዊ ቅንነትንም ይገድላል። ስለዚህ ኢዴሞክራሲያዊ እየሆነ የመከባበር፣ የመተማመንና የአብሮነት እሴቶችን ይገድላል። በዘመናት የተገነባ እሴት በዓመታት ዋጋ ቢስ ሆኖ ብዙ ዋጋ እንዳያስከፍለን እሠጋለሁ።
ሪፖርተር፡- በቅርቡ በትግራይ ክልል የእምባሰነይቲ ሕዝብ ‹‹ወረዳችን ይመለስልን›› የሚል ጥያቄ አንስቷል። ይህ ሕዝብ የሕወሓት ኮር ቤዝ የሚባልነበር። በድርጅቱየተሰጠው መልስና ጥያቄው እንዴት ያዩታል?
ጄኔራል አበበ፡- በመጀመርያ የእምባሰነይቲ ሕዝብ እንደዛ ጨዋነት በተሞላው፣ የሞራል ልዕልናውን ባረጋገጠ መንገድ ጥያቄውን በተደራጀ መንገድ ማቅረቡ ሊያስመሰግነው ይገባል፡፡ እኔም በግሌ ያለኝን ልባዊ አክብሮት መግለጽ እወዳለሁ። በዚህ ሒደት ሁለት ነገሮች አሉ። የሕዝቡ ተገቢ ጥያቄ እንዳለ ሆኖ መንግሥትም ያገባኛል ማለቱ የግድ ነው፡፡ የበጀትና ተያያዥ ነገሮች ስላሉ። መንግሥት ግን ሲያገባው እንዴት ነው መልስ የሚሰጠው የሚለው መታየት አለበት። መጀመሪያ ጥያቄ ለምንድነው ወረዳ የሚፈልገው የሚለው ከሕዝቡ ፍላጎት ጋር አስተሳስሮ መመለስ ነበረበት፡፡ ይህ ለሃያ ዓመታት የቆየች ችግር በጥናት በተረጋገጠ መንገድ አልተመለሰም። የሕዝቡን ጥያቄ አክብሮ ከማዳመጥ ይልቅ የት ትደርሳላችሁ የሚል የትዕቢት መልስ መንግሥት መስጠቱን ሕዝቡ በሰላማዊ ሠልፉ ላይ ገልጿል፡፡ ይህ አሳፋሪና አሽማቃቂ መልስ ነው። ይህ ሕዝብን መናቅ ነው፡፡ ሕዝብን ማዳመጥ እየጠፋ ነው ማለት ነው፡፡ ከሕዝብ ጋር ሆነህ መፍትሔ መሻት የሚባል ነገር የለም ማለት ነው። ሰማንያ አንድ ወረዳ ቢፈጠር ለልማት እንቅፋት ይሆናል የሚል ሥጋት እንኳን ቢኖራቸው፣ ሥጋታቸውን ከሕዝቡ ጋር ሆነው ተመካክረው ወረዳ መሆን የሚሰጠውን ጥቅም በሆነ አሠራር ሕዝቡ እንዲያገኝ ለማድረግ ፍላጎት አለማሳየታቸው ያሳዝናል። ነገሩን ከባድ የሚያደርገው ደግሞ ጥያቄው የእምባሰነይቲ ብቻ አለመሆኑን እያወቁ ማስፈራራትን እንደ መፍትሔ መውሰዳቸው ነው።
ችግሩ የኪራይ ሰብሳቢ፣ የጥገኛ አመራር፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ሴራ አድርገው ማየታቸው ምን ማለት እንደሆነ የገባቸው አይመስለኝም፡፡ ሕዝቡን ሞኝ ነህ፣ ተታለህ ነው፣ ስለራስህ ምንም አታውቅም እያሉት ነው። ይህ ደግሞ ከማሳዘን አልፎ ከባድ አላዋቂነት ጭምር መሆኑን ነው የሚያሳየው። በኦሮሚያም የተባለው ተመሳሳይ ነው፡፡ በሁሉም ክስተቶች የእገሌ የእገሌ እየተባለ ሕዝብን ማሸማቀቅ ፀረ ዴሞክራሲያዊነት መሆኑ መታወቅ አለበት። ሲጀመር መንግሥት የት ነበርና ነው?
ሪፖርተር፡- ከኦሮሚያ ቀጥሎ በቅርቡ የታጠቀ ኃይል በሕገ መንግሥታዊ ተቋማት ላይ የበላይነት ከያዘ፣ የፖለቲካ ፍላጎት ሊያሳድር ይችላል የሚል አስተያየትም ሰጥተው ነበር፡፡ ዕውን በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ዓይነት ሥጋት ይኖራል?
ጄኔራል አበበ፡- የደኅንነትና የዴሞክራሲ እጥረት ዋናው የድህንነታችን ጥያቄ ነው። በአፍሪካ እንደምናየው የታጠቀው ኃይል ከትጥቅ በላይ ከፍተኛ የፖለቲካ ተፅዕኖ አለው። በሲቪል ቁጥጥር ሥር ካልዋለ ራሱን ንጉሥ ወይም አንጋሽ የመሆን ፍላጎት ሊያዳብር ይችላል። ሕገ መንግሥታዊ ተቋማት ሕጉ በሚያስቀምጠው መንገድ መሥራት ካልቻሉ አጠቃላይ መዛባት ይፈጠራል። ሕገ መንግሥቱ በተለያዩ ተቋማት መካከል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት በሥርዓቱ ደንግጓል፡፡ ሕጉ በተገቢ መንገድ በማይተገበርበት ጊዜ ግን መዛባት ይፈጠርና ጉልበት የበላይነት ያገኛል። ሥልጣን አስፈጻሚው ዘንድ ሲጠቃለል የመጀመሪያው የአደጋ ምልክት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ከአስፈጻሚው ጋር ደግሞ ሲቪልና የደኅንነት አካላት አሉ። እዚህ ጋ መዛባት ሲፈጠር ጠቅላላ ኃይሉ ወደ ታጠቀው ይጠቃለላል። ካልተዛባ ቦታውን ይይዛል፣ አገሩንም ይጠብቃል፣ የውጭ ጠላትን ይመክታል ይከላከላል። ካልሆነ ግን ፖለቲካዊ ፍላጎት አዳብሮ ተፅዕኖ ማሳደር ይችላል። ሕገ መንግሥቱ መሠረት ተደርጎ ካልተኬደ ሲቪሉ በታጠቀው ኃይል ሥር ይወድቃል። አሁን አንዳንድ ምልክቶች እየታዩ ነው። ከስኳር ኮርፖሬሽን ጋር ተያይዞ የተሰማው ነገር የዚህ ምልክት ነው እንዴ? እንድትል ያደርጋል።
ሪፖርተር፡- ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየመን የሳዑዲ ዓረቢ እንቅስቃሴ አለ፡፡ ከደቡብ ሱዳን የመጡ ታጣቂ ቡድኖች በጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች ላይ ብዙጉዳት አድርሰዋል፡፡ቀጣይነት ያለው ከኤርትራ የሚመጣ አደጋ አለ። እርስዎ እንደ የሰላምና የደኅንነት ባለሙያና የቀድሞ ጄኔራል እንደመሆንዎ መጠንበዚህ የደኅንነት ጉዳይ ላይ ምን ይላሉ?
ጄኔራል አበበ፡- ባለሙያ ለመባል እንኳን ያስቸግረኛል። ጋምቤላ ላይ የተፈጠረው ትልቅ ጉዳይ ነው። ብዙ ሰው ነው የሞተውና የተጎዳው። ለቤተሰቦቻቸውና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ፅናቱን እንዲሰጣቸው እመኛለሁ። ለብቻው ስታየው የሚያጋጥም ነገር ነው ለማለት የሚቻል ይሆናል። ነገር ግን ብዙ ጥያቄዎች ያሉበት ነው። ሙርሌዎች እንዴት ብለው ነው ልባቸው ሞልቶ ለቀናት ተዘጋጅተውና ሠልጥነው ያጠቁት? እንዴት ብለው ነው የደፈሩት? እዚያ አካባቢ ያለው የደኅንነትና የመከላከያ ኃይሎች ምን ይሠሩ ነበር? በአካባቢው ሠራዊት ነበር? አልነበረም? ለምንድነው በአጭር ጊዜ ምላሽ ያልተሰጠው? ሕፃናቱን ማስመለስ ለምንድነው የዘገየው? ሲደጋገምና ተመሳሳይ ክስተቶች በርከት ብለው ሲታዩ ጥያቄ መነሳቱ የግድ ነው። ይኼ ነገር የሥርዓቱ ችግር ሊሆን ይችላል ተብሎ ከብሔራዊ የደኅንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ ከፖሊሲው ማኔጅመንት፣ ከሥራ አስፈጻሚውና ከተወካዮች ምክር ቤት ሚና ጋር አያይዞ ማየት ያስፈልጋል። የሥርዓቱ በሽታ ማሳያ ሊሆን ይችላል። ፓርላማው ሐዘን ከማወጅ የዘለለ ለምን ተከሰተ ብሎ አስፈጻሚውን መጠየቅና ማጣራት አለበት፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥንም ቢሆን ይህ ነገር ለምን ተከሰተ ተብሎ ሊጠየቅና ማብራርያ ሊሰጥ ይገባዋል። መከላከያ ሚኒስትሩም እንዲሁ። ይህ ክስተት ሥርዓቱን እያስተካከልን እንሄዳለን የሚል በጎ አስተሳሰብ ካለ አጠቃላይ ሥርዓቱን ለመፈተሽ ይጠቅመናል፡፡ ክስተቱ የውድ ዜጎችን ሕይወት የቀጠፈ አሳዛኝ ድርጊት መሆኑ ሳይረሳ።
ሳዑዲዎች የኤርትራ ባህር ዳርቻዎች ላይ የጦር መርከቦቻቸው ሲያሰፍሩ ኢትዮጵያን አንነካም፣ ዓላማችን የመን ላይ ነው እያሉ ይምላሉ ይገዘታሉ፡፡ እኛ እንደ ሞኞች ብለውናል ብለን ነው መሄድ ያለብን? የፈለጉትን ነገር ለማድረግ ተፅዕኖ እየፈጠሩ ነው? ሳዑዲ ዓረቢያ አሥራ አምስት ቢሊዮን ዶላር አካባቢ በሱዳን ኢንቨስት እያደረገች ነው፡፡ ለሱዳን ወታደራዊ ድጋፍ እየሰጠች ነው፡፡ ሱዳን ሠራዊትዋን ወደ የመን ልካለች፡፡ በሳዑዲና በኢራን መካከል ከነበረው ፍጥጫ ተነስተው ሱዳንና ሶማሊያ ከኢራን ጋር የነበራቸውን ግንኙነት አቋርጠዋል። ይኼ የሱዳንና የኢራን እንጂ እኛ ጋ ሊከሰት አይችልም የሚባል ነገር ልክ አይደለም። አጠቃላይ ሁኔታው ምን ይመስላል የሚለው ነገር መጤን አለበት። የኤርትራም ጉዳይ ከዚህ ጋር ተያይዞ ነው መታየት ያለበት።
ሪፖርተር፡- በቀጣናው እየታየ ያለውን የደኅንነት ሥጋት ለመቆጣጠር ከውስጥ ምን መደረግ አለበት ይላሉ?
ጄኔራል አበበ፡- በዚህ ጊዜ ደግሞ ለዘመናት የኢሕአዴግ ባህል የነበረው የጋራ አመራር እየጠፋ ነው፡፡ ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ባልተቋመበት፣ ሁሉን አቀፍ የሆነ ጽሕፈት ቤት ባልነበረት ሁኔታ አደጋ ተከስቷል። በዚህ ላይ አንድ የጻፍኩት ጽሑፍ አለ። በጥናቴ ያገኘሁት ነገር ቢኖር ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት በአዋጅ ቢቋቋምም፣ ሴክሬታሪያት የሌለውና አልፎ አልፎ እንደሚሰበሰብና የተጠናከረ አደረጃጀት እንደሌለው ነው። የዚችን ትልቅ አገር ደኅንነት በዚህ መልኩ መያዝ የለበትም፡፡ ጥንቃቄና ጥልቅ ትንተና የግድ ነው። ከየዘርፉ ምሁራን መሰብሰብ አለባቸው፡፡ ሥጋቶችና ፀጋዎች በደንብ መለየት አለባቸው፡፡ ትንበያዎችና ቅድመ ዝግጅቶች መደረግ አለባቸው። ነገሮች ከተፈጠሩ በኋላ እሳት ለማጥፋት አይደለም መሮጥ ያለብን፡፡ ሊፈጠር እንደሚችል መገመት የሚያስችል አቅም ልንገነባ ይገባናል፡፡ ታላቅ አገር ይዘን ንህዝላል መሆን አንችልም። የሁሉም የትምህርት ተቋማት፣ ኤምባሲዎችና ቆንፅላ ጽሕፈት ቤቶች፣ የደኅንነትና የወታደራዊ መረጃ፣ የቲንክ ታንኮችና ዓለም ላይ ሊገኙ የሚችሉ መረጃዎችን መሠረት እያደረገ ሴናርዮዎች (ቢሆኖች) ማቅረብ የሚችል በትልቅ አቅም የሚንቀሳቀስ የደኅንነት ሴክሬታሪያት ያስፈልገናል። ለምሳሌ ከተቋማዊ አሠራር አቅጣጫ ብናየው በተከታታይ የኤርትራ መንግሥት ሉዓላዊነታችንን እየደፈረ ዜጎቻችንን ይጠልፋል፣ አልፎ አልፎ ይመለሳሉ፡፡ ፓርላማው ግን አንድም ቀን ቢሆን አስፈጻሚውን ለምን እንዲህ ሆነ ብሎ ሲጠይቅ ዓይተን አናውቅም። ሙርሌዎች እንደዚህ ሲያበሳብሱን ፓርላማው ለምን ማለት ነበረበት፡፡ የሚመለከተው አካል መጠየቅና ኃላፊነት መውሰድ ነበረበት።
ሪፖርተር፡- ከኢሕአዴግ ነባር አመራሮች ወጣ ያ ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ያጣችው ‹‹በኢሕአዴግ አላዋቂነት ነው›› ብለዋል፡፡ በጥናታዊጽሑፍዎ ድምዳሜምሰፍሮ ይገኛል። እውነት ሕጋዊ መሠረት አለን ማለት ነው?
ጄኔራል አበበ፡- ድሮም ቢሆን የኤርትራን ነፃነት ተቀብለው የአሰብ ጉዳይ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች ነበሩ። እንደነ አቶ ተወልደ ወልደ ማርያም፣ ሌተና ጄኔራል ፃድቃን ገብረ ትንሳኤ፣ አቶ ስየ አብርሃ፣ አቶ ተፈራ ዋልዋ፣ እኔም ጥያቄዎች የምናነሳበት ሁኔታ ነበር፡፡ በዝርዝር ባንወያይበትም። አሜሪካ ሄጄ ሁለተኛ ዲግሪዬን ስሠራ ግን በዚህ ላይ ጥናት አካሂጄ የባህር በር መብታችንን በሕጋዊ መንገድ ማስመለስ እንደምችል የሚያረጋግጥ ድምዳሜ ላይ ደረስኩ። ባለማወቅና በመታበይ (Ignornace and arrogance) ያጣነው መብት ነው፡፡ አሁንም ግን ሕጋዊ መሠረት አለን፡፡ ዝርዝር ነገር የሚፈልግ ካለ የመመረቂያ ጽሑፌ ላይ አስፍሬዋለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- በአሰብ ጉዳይ ላይ ካደረጉት ጥናት ውጪ በተግባር የመሥራት ዕቅድ አለዎት?
ጄኔራል አበበ፡- አዎ፡፡ የአገር ጉዳይ ስለሆነ ነው። በእኔ አረዳድ የባህር በር ሳናውቅ ያጣነው አገራዊ ፀጋችን ነው። በእርግጥ የባህር በር ጉዳይ ከአጠቃላይ ሕገ መንግሥታዊና ፖለቲካዊ ሥርዓቱ አንፃር ካልታየ የወራሪነት ባህሪ ያለው አደገኛ ነገር ነው የሚሆነው፡፡ ስለዚህም ተጠንቅቄ የማነሳው ጉዳይ ነው። የባህር በር ጉዳይ በጣም አስፈላጊ ነው ስል የሞት ሽረት ጉዳይ አድርጌ አላየውም። ከኢኮኖሚም ከፀጥታም አኳያ በጣም ያስፈልገናል፡፡ ግን ሕጋዊና ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ነው መሆን ያለበት። አሁን ያለውን ሥርዓትና መሠረታዊ የፖለቲካ እሴቶቻችን በሚንድ መልኩ መሆን የለበትም። አሁን ያለን ሕገ መንግሥት ለሌሎች ሕዝቦችና አገሮች አርዓያ መሆን የሚችል የዳበረ ሕገ መንግሥት ነው። ስለዚህም የአሰብ ጉዳይ ተነስቶ ሕገ መንግሥቱን ለመሸርሽርና ለመናድ በሚደረግ እንቅስቃሴ አልሳተፍም። ይህ ሕጋዊ መብታችን ግን መረጋገጥ አለበት ብዬ ስለማምን በቻልኩት መጠን እንቅስቃሴ አድርጋለሁ።
ሪፖርተር፡- ኢሕአዴግ ከክፍፍሉ ከ1993 ዓ.ም. በፊትና በኋላ እንደ ድርጅት ውስጣዊ ጥንካሬው እንዴት ያዩታል?
ጄኔራል አበበ፡- ኢሕአዴግ በ1993 ዓ.ም. ቀውስ ውስጥ ሲገባ የድርጅቱ አባል አልነበርኩም፡፡ የአየር ኃይል አዛዥ ነበርኩ። ስለዚህ ድርጅት ውስጥ የነበረውን ነገር በዝርዝር አላውቅም፡፡ ሆኖም ከሁለቱም አንጃዎች በኩል የትጥቅ ጊዜ ጓደኞቼ ስለነበሩ በሁለቱም ጎራ የነበረውን ሁኔታ እሰማ ነበር። ከድርጅቱ ጋር በነበረን ሥነ ልቦናዊ ትስስርም ድርጅቱ እንዲፈርስ አንፈልግም ነበር። ቁውሱን ለመፍታት የተደረገው ድርጊት ግን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ጠባሳ ያሳደረ ነበር። ሒደቱ እልባት ያገኘው ኢዴሞክራሲያዊና ኢሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ነበር። የመንግሥት ሚዲያ የአሸናፊው አንጃ ሚዲያ ሆኖ ተሸናፊው አንጃ ሐሳቡን የሚገልጽበት ዕድል ተነፍጎ፣ ጄኔራሎችም ጭምር በጉዳዩ ፖለቲካዊ መግለጫ የሰጡበት ሕገ መንግሥታዊነት፣ ፌዴራሊዝምንና የድርጅትን ሕገ ደንብ ገደል የከተተ ሒደት ነበር። ለስዬ ተብሎ ሕግ እስከማውጣት ድረስ ተኪዷል፡፡ ፍርድ ቤት ሲለቀው ፖሊስ በጉልበት ይዞታል። በአጠቃላይ የቀውስ አፈታት ሒደቱ ኋላቀር ብቻ ሳይሆን የተወው ትምህርትም አደገኛ ነው። በውስጥ የፓርቲዎችን መብትም የናደ ነበር። በተለይ ኦሕዴድና ደኢሕዴን ላይ የተሠራው ሥራ ህልውናቸውንና ነፃነታቸውን በሚንድ መልኩ ነበር የተካሄደው። በዚያ መልኩ መለያየታችን ያሳዝነኛል።
ሪፖርተር፡- በ1993 ዓ.ም. የተከሰተውን ቀውስ በመፍታት ረገድ የታየው ፀረ ዴሞክራሲ አሠራር ከዚያ በፊት አልነበረም ይላሉ?
ጄኔራል አበበ፡- መለያየቱ ራሱ የነበረውን አቅም የበተነ ነበር፡፡ ትልቅ ብቃትና ዕውቀት የነበራቸው ሰዎች በአገር ግንባታ እንዳይሳተፉ ያደረገ ነገር በመሆኑ ያሳዝነኛል። በተጨማሪም አሸናፊው አንጃ የደኅንነት መዋቅሩን የሰው መብት በሚጥስና ፍራቻን ለማንገሥ ባለመ ሁኔታ ነበር ሲያንቀሳቅስ የነበረው። እንዲህ ዓይነት ዝንባሌዎች ከዚያ በፊት አልነበሩም ማለቴ አይደለም። ምናልባት እኛ ላይ ስለተፈጸመ ሊሆን ይችላል ያስተዋልነው ወይም መጠኑ ከፍ ብሎ ሊሆን ይችላል። በሰዓቱ የነበረን አስተሳሰብ ‹ከኢሕአዴግ መስመር ውጪ ሁሉም የጥፋት መስመር ነው› ብሎ የሚያምን ስለነበር ተቃዋሚዎችን እንደ ፀጋ የማያይ፣ እግራቸውን እንዳይተክሉ የሚያደርግ አስተሳሰብ ነበር፡፡ ጎልቶ የታየን ግን እኛ ላይ ሲደርስ ነው። ስለዚህ 1993 ዓ.ም. ብቻውን መለያ አይሆንም። እንደኔ አመለካከት ኢሕአዴግ የተሻለ ዴሞክራቲክ ድርጅት ነበረ ብልም ሙሉ በሙሉ ዴሞክራቲክ ነበር ለማለት አልችልም። ከቀውሱ በፊት ፓርላማው ማኅተም መቺ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቶች ነፃነት አልነበራቸውም፡፡ ‹ቼክ ኤንድ ባላንስ› የነበረበት የሥልጣን ክፍፍል አልነበረም፡፡ ከዘጠና ሦስት በኋላ ግን ባሰበት።
ሪፖርተር፡- ለወጣቱ ትውልድ ምን ይመክራሉ?
ጄኔራል አበበ፡- ወጣቱ ትውልድ ያለፈው ትውልድ የሠራውን ሥራ ዕውቅና እየሰጠ ሲያበላሽ ደግሞ አታበላሽ ማለት መቻል አለበት፡፡ ያለውን ብልሽት ለማስተካካል መሥራት አለበት፡፡ ማማረር ብቻ መፍትሔ አይሆንም። በምሬት መጀመር ባህርያዊ ነው። ወጣቱ ትውልድ በሚያምንበት አደረጃጀት እየገባ መታገል አለበት። በግልና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ የተሸሸጉ ማፊያዎችን መታገል አለበት። አገሪቷ በመስቀለኛ መንገድ ነው ያለችው፡፡ የወጣቱ ፖለቲካዊ ተሳትፎ የግድ የሚልበት ጊዜ ላይ ነው ያለነው። በፌስቡክም፣ በትዊተርም፣ በየጋዜጣና በየመጽሔቱ በትጋት የሚሳተፉ ወጣቶችን በርቱ ማለት እወዳለሁ።