Monday, October 17, 2016

በ ጎንደር ዶባው አካባቢ ሲደረግ የነበረው የ 4 ቀን ውጊያ በአማራ ታጋዮች ድል አድራጊነት ተደምድሟል


የህወሓት የመከላከያ ሰራዊት ለወሬ ነጋሪ እንኳ ሳይቀር ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል። የህውሓት ባለ ስልጣኖች ፥ ሬሳ ለመውሰድ ስላልቻሉ የአካባቢውን ሽማግሌዎች የወታደሮቹ ሬሳ ይመለስ ዘንድ እየለመኑ ነው ።
ቁጥራቸው ከ 500 በላይ የሚሆኑ የአርማጨኾ የአማራ ታጋዮች ቁልፍ ቦታዎች ተቆጣጥረዋል ። የመሳሪያ እና የጥይት ችግር እንደሌለባቸው ምንጮቻችን ጠቁመዋል!
በጦርነቱ ጊዜ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው የአማራ ታጋዮች ፥ በቂ የሆነ ህክምናም እንደሚያገኙ የደረሰን መረጃ ያሳያል ።
በተያያዘ ዜናም ፥ የአርማጭሆ የአማራ ታጋዮች ፥ ሌሎች የአማራ ተወላጆች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል!
የመንግስት ወታደሮችን ሬሳ የሚያሳየውን መረጃ ( እንደደረሰን እናቀርባለን ) እና ተመሳሳይ ጉዳዮች ወደ ኋላ ላይ እናቀርባለን !
በትግሉ ላይ ቀጥታ ከሚሳተፉት እና ከትግሉ መሪዎች ጋም ስታራቴጂ ነክ ጉዳዮችን ተወያይተናል ። ትግሉን በተመለከተ ያለውን ብዥታም ለማጥራት እና ህዝቡ እውነቱን ያውቅም ዘንድ ፥ ከማን ጋ እና እንዴት መታገል አለበት ፥ ትግሉንስ እንዴት ሊቀላቀል ይችላል ለሚለውም የረጅም ግዜ ጥያቄዎች ፥ አብሪ ጥይት የሆኑ ሃሳቦችን በተከታታይ ከአሁን በኋላ ማሳወቅ እንጀምራለን ። እኛ ድርጅት አይደለንም ፥ ግን ታጋዮች ነን!
ድል ለአማራው ህዝብ!

No comments:

Post a Comment