Saturday, April 29, 2017

ጋዜጠኞችን በማሰር ኢትዮጵያ በዓለም አምስተኛ ነች

    


የዓለም የፕሬስ ነጻነት ባለፈው የአውሮፓውያን 2016 ዓመተ ምህረት በአስራ ሦስት ዓመታት ውስጥ ባልታየ ደረጃ አሽቆልቁሉዋል ሲል ጽህፈት ቤቱ ዩናይትድ ስቴትስ የሆነው የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ዛሬ ይፋ ባደረገው ዓመታዊ ሪፖርት አስታውቋል።
የዓለም የፕሬስ ነጻነት ባለፈው የአውሮፓውያን 2016 ዓመተ ምህረት በአስራ ሦስት ዓመታት ውስጥ ባልታየ ደረጃ አሽቆልቁሉዋል ሲል ጽህፈት ቤቱ ዩናይትድ ስቴትስ የሆነው የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ዛሬ ይፋ ባደረገው ዓመታዊ ሪፖርት አስታውቋል።
ይህ የሆነው በትላላቆቹ ዴሞክራሲያዊ ሃገሮች ከምን ጊዜውም በከፋ ደረጃ በጋዜጠኞችና በዜና ማሰራጫ ድርጅቶች ላይ በሚደርሰው ዛቻ አምባገነን መንግስታት ጥቃታቸውን እያባባሱ በመምጣትቸው ነው ሲል ፍሪደም ሃውስ ዛሬ ባወጣው የፕሬስ ነጻነት ሪፖርቱ ገልጿል።
በሪፖርቱ መሠረት አሁንም ቀንደኞቹ የፕሬስ ነፃነት ረጋጮች በአምባገነኑ ኪም ጆንግ ኡን የምትመራዋ ሰሜን ኮሪያ፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት በርስ በርስ ጦርነት እየታመሰች ያለችው ሶሪያ እና የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃኑን ሙሉ በሙሉ ኮምዩኒስት ፓርቲው የሚቆጣጠርባት ቻይና ናቸው።
በአሁኑ ጊዜ እየታየ ያለው አንድ ለውጥ ግን “እንደ ዩናይትድ ስቴትስ ባሉ ዴሞክራሲያዊ ሀገሮችም የፕሬስ ነፃነት እየተጎዳ መምጣቱ ነው” ብለዋል የፍሪደም ሃውስ የምርምር ዳይሬክተር ጀነፈር ደነም።
አንዱ ትልቁና አሳሳቢው ለውጥ ዴሞክራሲ እየተሸረሸረ መሄዱ መሆኑን የገለፁት ደነም በተለይ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ በጋዜጠኞች እና በዜና አውታሮች ላይ የሚሠነዝሯቸውን ውረፋዎች በተለይ ጠቅሰዋል።
ይሁንና ሥጋቱ ቢኖርም “የዩናይትድ ስቴትስ የመናገር ነፃነትና የሚድያውም ነፃነት እንደተቋም እንደተጠበቀ ነው” ብሏል ፍሪደም ሃውስ የሚባለው የዴሞክራሲ አስተሳሰቦች አራማጅ ተቋም፡፡

አገር የሚያፈርስ ማን ነው? – የጉድ ሐገር



የጉድ ሐገር !!!!
(ከአቶ ግርማ ሰይፉ ገፅ የተገኘ አሳዛኝ መረጃ)
ዛሬ ጠዋት ከቤቴ ወጥቼ ልጆች ትምህርት ቤት ካደረሰኩ በኋላ የተገኘሁት ቦሌ ክፍለ ከተማ ዐቃቢ ህግ ቢሮ ነበር፡፡ አብሮኝ የሸዋስ አሰፋ ነበር፡፡ ያጎደልኩት ካለ ይጨምርበታል፡፡ የተጋነነ የለውም፡፡ የሄድንበት ምክንያት ወደጆቻችን ኤሊያስ ገብሩ እና ዳንኤል ሸበሺ ለረጅም ጊዜ በእስር በመቆየታቸው ፋይላቸው በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጉዳያቸውን እየተመለከተው ይገኛል ከሚባለው ዐቃቢ ህግ ሃላፊ ጋር ለመነጋገር ነበር፡፡ ሃላፊው አቶ ዘለቀ ይባላል፡፡ ጠዋት ከቢሮ ብንገኝም አቶ ዘለቀ ለአራት አስር ጉዳይ ሲል ወደ ቢሮ ገቡ፡፡ ማርፈዳቸው ቢገባቸው ብዬ ይቅርታ ገና ከመግባቶ የመጣነው ውጭ ትንሽ ሽለቆየን ነው በማለት ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ ማርፈዳቸው ምንም ግድ አልሰጣቸውም፡፡ ያለምንም ቢሮክራሲ ቢሮ ገብተን ማናገር ጀመርን፡፡ ምንም ቢሮክራሲ የማያውቁት አቶ ዘለቀ ላቀረብንላቸው ጥያቄዎችም አንድም የሲቪል ሰርቪል ደንብና ህግ፣ የአገልጋይነ መንፈስ የለባቸውም፡፡ ዐቃቢ ህግ የሚለው ነገር ትርጉም ካልተቀየረ በስተቀር ለህግ ልዕልና የሚቆም ባለሞያ የሚሰጠው ስለ ሰው ልጅ ስብዓዊ መብት ግድ የሚሰጣቸው ሆኖ አላገኘኋቸውም፡፡ ዝርዝሩን ልነግራችሁ አልችልም ብዙ ነው፡፡ ለማሳያ ያክል ላካፍላችሁ፡፡

ለአቶ ዘለቀ የመጣንብተን ጉዳይ አስረዳናቸው፡፡ እነዚህ ልጆች በእስር ስድስት ወር ሊሞላቸው ነው፡፡ ወይ ፍርድ ቤት አልቀረቡም፤ ወይም እንደሌሎች ስልጠና ወስደው አልተለቀቁ እና ጉዳያቸው ምን እንደደረሰ ለማወቅ እና አፋጣኝ መፍትሔ እንዲያገኙ እንዲያግዙን ነው፡፡ አልኳቸው፡፡ የአቶ ዘለቀ መልስ “ለምን ይፈጥናል እነዚህ እኮ ሀገር ሊያፈርሱ የነበሩ ናቸው፡፡” ብለው በግል ጠብ ያላቸው የሚያስመስል ነገር ነገሩኝ፡፡ እነርሱ ባስነሱት ጦስ “ሀገር ልትፈርስ ለጥቂት ነው የዳነችው” ብለውኝ አረፉት፡፡ አለቆቻቸው የሲኒ ማዕበል ነው ሲሉ እርሳቸው ደግሞ ሀገር ልትፈርስ ለጥቂት መዳኗን፣ የዳነችውም እነ ኤሊያስ ገብሩ በመታሰራቸው እንደሆነ እና አገር የሚፈርሰው እነዚህ ልጆ በፌስ ቡክ ላይ በሚለጥፉት ፅሁፍ መሆኑ ገረመኝ፡፡ አቶ ዘለቀን አግባብቶ ወደ ቁም ነገሩ ለመውሰድ ብዬ፡፡ መቼም ይህ የሚነግሩኝ ጉዳይ ለጫወታ ሊሆን ይችላል፤ እነዚህ ልጆች ጥፋተኛ ከሆኑም ፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲሰጥ ፋይላቸው ፍርድ ቤት መቼ እንደሚቀርብ ማወቅ ፈልገን ነው የመጣነው አልናቸው፡፡ “ምን ያሰቸኩላል እያጣራን ነው ስንጨርስ ውሳኔ ይሰጥበታል፡፡” አሉን፡፡ በዚህ መሃክል ቤተሰብ ይፈርሳል፣ ጥፋተኛ ካልሆኑ ደግሞ ፍትህ ይዛባል ሰለዚህ እንዲፋጠን የፈለግ ነው ለዚህ ነው ብለን ሃሳባችንን ሳንጨርስ፤ “ይፍረሳ (ቤተሰቡ ማለታቸው ነው)፤ እነርሱ አኮ ሀገር ለማፍረስ እንጨት ይዘው ሲጎረጉሩ ነበር፡፡” በማለት ሀገር የሰጋቱራ ክምር ይመስል በእንጨት ጉርጎራ የምትፈረስ አደረጉና ግራ አጋቡን፡፡ አቶ ዘለቀ ሀገር እኮ የቤተሰብ ድምር ነው ብዬ ጣልቃ ስገባ፤ “እሱን አላጣሁትም፣ አገር ከሚፈርስ ግን አንድ ቤተሰብ ቢፈርስ ችግር የለውም ነው የምልህ፡፡” ብለው አስረግጠው ደገሙልኝ፡፡
ተመሳሳይ መልሶችን ለሌሎችም እንደሰጡ ተረድቻለሁ፡፡ እነዚህ ልጆች በጣቢያ በእስር ቤት ውስጥ ሆነው ሁሉ የሚሰሩትን እንደሚያውቁ፤ በኢሣት እና በቪኦኤ በፌስ ቡክ ስለነሱ ብቻ እንደሚወራ እንደሚያውቁ፤ መግለጫ ሰጡን፡፡ ይህን ፅሁፍ የፃፍኩትም አንባቢ ከእነ ኤሊያስ እና ከአቶ ዘለቀ አገር የሚያፈርስ ማን ነው? ብዬ ለመጠየቅ ነው፡፡ ለረጅም ጊዜ በመንግሰት መስሪያ ቤት አገልግያለሁ፣ በዚህ ደረጃ ለተገልጋይ መልስ የሚሰጥ በኃላፊነት ደረጃ ያለ ሰው ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ በዚህ ደረጃ ሃላፊነት ያለበት ሰው የተጠየቀውን ጥያቄ የግል ሰሜቱን ዋጥ አድርጎ የስራ ሂደቱን በመንገር መረጃ ከመስጠት ሃልፎ አንድን ቤተሰብ ቢፈርስ ግድ እንደማይሰጠው ሲነግረኝ መስማት ያሳምማል፡፡ አንድ መስሪያ ቤት የያዘውን ጉዳይ መቼ ጀምሮ መቼ እንደሚጨርስ የሚቀመጥ ጊዜ በመኖሩ ይህ ጊዜ ካልተቻለ ደግሞ ምክንያቶች መግለፅ እንደሚቻል ማንም ያውቃል፡፡
ለማነኛውም በእኔ እምነት ይህች አገር የምትፈረሰው ኤልያስና ዳንኤል ፅፈው በሚለጥፉት መልዕክት ክፋትና መጥፎነት ሳይሆን የመንግሰት የሃላፊነት ቦታዎች በተለይ ደግሞ በህግ ሊመሩ የሚገባቸው ዓቃቢ ህጎች ዓቃቢ ፖለቲካ ከሞያቸው ይልቅ ካድሬነታቸው ሲያመዝን ነው፡፡ እነ ዘለቀ የጥልቅ ተሃድሶ ውጤት ከሆኑ፣ የወረድንበትን ዝቅጠት ጥልቅነት ለመገንዘብ ይቻላል፡፡ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት አሠጣጥ እዚህ ደረጃ መውረዱ ያሳዝናል፡፡ በፌስ ቡክ ስለ እነ ኤሊያስ ብቻ ይወራል ያሉት አቶ ዘለቀ ደስ ይበላቸው ይኽው ስለ እርሳቸውም አወራን፡፡

ኦባንግ ሜቶ ከከፋ አደጋ ተረፉ! – “ዳግም የመኖር እድል ተሰጠኝ፤ ተማርኩበት፤ እናንተም ተማሩ”



ፎቶ – ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
“ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ በሁሉም ስፍራ፣ በየትኛውም አጋጣሚ ለሚፈልጋቸው ሁሉ “አለሁ” የሚሉ ኢትዮጵያዊ ናቸው። ዘረኝነትን፥ ዘውገኝነትን፥ ጎሠኝነትን አጥብቀው ይዋጋሉ። ይጸየፉታል። ከዘር ቆጠራና ከቂም የጸዳች ኢትዮጵያን ማየት ህልማቸውና የመጨረሻ ግባቸው ነው።

Friday, April 28, 2017

ኢሳያስ እና ሻቢያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ የችግር ወይስ የመፍትሔ አካል? (በወረታው ዋሴ)

    
ኢሳያስ እና ሻቢያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ የችግር ወይስ የመፍትሔ አካል?  (በወረታው ዋሴ)
«ኦኤምኤን» የተባለ የቴሌቪዥን ጣቢያ ከሻቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ አዳመጥኩት፡፡ ከኢሳያስ ዲስኩር ምንም አዲስ ነገር አላገኘሁም፡፡ ሰውየው የኢትዮጵያን ፖለቲካ እያማሰለ መኖር ዋናው የህይወት መርሁ መሆኑን በግልፅ አሳይቷል፡፡ እርሱ የተነሳበትንና ማን እንደነበር አሁን ያለው እብሪቱ ጨርሶ ከጭንቅላቱ አጥፍቶበታል፡፡
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ያለውን የአማሳይነትና የበጥባጭነት ሚና ለማሳካት ለተለያዩ የኢትዮጵያ ድርጅቶች በሚያደርገው ድጋፍ ልቡ ምን ያህል በእብሪት ማበጡንና ለሌሎች ድጋፍ ማድረግ የድጋፍ አድራጊውን ታላቅነትና የድጋፍ ተቀባዩን ትንሽነት ለማሳየት ከመመሪያ ሰጭነትና ከአስተማሪ ነኝ ባይ ድስኩሩ ተረድቻለሁ፡፡
ኢሳያስ ድጋፍን ከሌሎች መቀበል ታናሽነትን የሚያሳይ መሆኑን ሲነግረን ከሁሉ አስቀድሞ የመጀመሪያው ታናሽ ራሱ መሆኑን ግን ፈፅሞ ረስቶታል፡፡ ኢሳያስ ኤርትራን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል የጀመረውን ደባ ለማሳካት ኢትዮጵያን ለመበታተንና ለማዳከም ከሚፈልጉ ሀገሮች ማለትም ሶማሊያ፣ሶሪያ፣አልጀሪያ፣ግብፅ፣ኳታር እና ኢራቅ ፓስፖርት ተዘጋጅቶለት በየቤታቸው እየዞረ በተረጅነት ሲቀላውጥ የኖረ ታናሽ ሰው ነው፡፡ ዛሬ ያ ተረጅነቱ በግርዶሽ ወደተሞላው ጭንቅላቱ ወርዶ መናገርና ማስመሰል የሚፈልገው ድጋፍ አድራጊነቱን ብቻ ሆኗል፡፡
ሻቢያና ኢሳያስ ወደስልጣን ከመውጣታቸው በፊትም ሆነ አሁን በስልጣን ባሉበት ዘመን በርዕየተ አላማቸውና ስለኢትዪጵያ አራምባና ቆቦ የሆነ አመለካካት ያላቸውን ድርጅቶችን እንደ ኢህአፓ፣ ኦነግ፣ ወያኔ፣መኢሶን እና ሌሎችም በተመሳሳይና በተለያዬ ጊዜ ሲደግፍና ሲያስታጥቅ ቆይቷል፡፡ ሻቢያ የተለያየ አቋም ያላቸውን ድርጅቶች የሚደግፋቸው ድርጅቶቹ በሚያደርጉት ትግል ምክንያት ኢትዮጵያን በማዳከም እንደየወቅቱ ሁኔታ ሊያሳካ የሚፈልገውን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ቀላል እንዲሆንለት በማሰብ ነው፡፡
ኢሳያስ እና የሚመራው ድርጅት ሻቢያ እያደረጉ ያሉት ኢትዮጵያን ለማዳከምና ለመበታተን ከሚፈልጉ ሀገሮች የተቀበለውን ኢትዪጵያን እስከመጨረሻው የማፍረስ የቤት ስራ ለመጨረስ እንጅ መቸውንም ቢሆን ለተሻለች ኢትዮጵያ ቅንጣት አስተዋፅዖ ለማድረግ አይደለም፡፡ ዛሬ በከፋፍለህ ግዛው ብሂል በተዳከመችዋ ኢትዮጵያ በድንበር ይገባኛልና በሌሎች ባልተሳኩ የደባ ጥቅሞች ምክንያት በውዝግብ ውስጥ የገባው ኢሳያስ ጠንካራዋ ኢትዮጵያ መቸም ቢሆን እረፍትና መረጋጋት እንደማትሰጠው ስጋቱና የቀን ቅዠቱ እንደምትሆንበት ይረሳል ብሎ ማሰብ ቂልነት ነው፡፡ በአንፃሩ ይህንን እውነታ በሚገባ እየተረዱ ሃቁን ሸፍኖ ከሻቢያ ጋር በማበር ለኢትዮጵያ የተሸለ ነገር እናመጣለን በማለት የሚደረገው ነገር ሁሉ አንድም የፖለቲካ አድርባይነት ነው ወይም ኢትዮጵያን ለማፍረስ ለሚደረገው የቤት ሥራ የበኩላቸውን ድንጋይ ለመወርወር የሚሯሯጡ ወገኖች የደባ ስራ ነው፡፡
በመግቢያዬ አካባቢ እንደገለፅኩት ሻቢያና ኢሳያስ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት እጅግ የተራራቀ አመለካከት ያላቸውን ድርጅቶች እንደ ኢህአፓ፣ ኦነግ፣ ወያኔ፣መኢሶን፣ግንቦት ሰባት እና ሌሎችም ነፃ አውጭ ነን የሚሉ ድርጅቶችን ሲደግፍ እንደነበረና አሁንም እየደገፈ እንደሆነ ኢሳያስ በቃለ ምልልሱ ነግሮናል፡፡ በጣም አስገራሚው ነገር በአመለካከታቸው እጅግ የተራራቁና እርስ በእርስ በጠላትነት የሚፈላለጉ ድርጅቶችን አንዱ ሻቢያ ድጋፍ ሲያደረግላቸው የተነሱለት ዓላማ እንዳይሳካ እየሰራባቸው መሆኑን አለመረዳት የእነዚህ ድርጅቶች የፖለቲካ አስተሳሰብ አርጧል ወይም በአድርባይነት የሚፈልጉትን ነገር በአቋራጭ ለማግኘት ከመሮጥ ያለፈ ራዕይ የሌላቸው ናቸው፡፡
እጅግ የሚያስገርመው እስካዛሬ ኢትዮጵያን ለማዳከምና ለመበታተን በሚፈልጉ ሀገሮችና በሻቢያ የተሰራብንን ደባ የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ ብሎ በማለፍ ከሻቢያና ከኢሳያስ በሚደረግ ድጋፍ በኢትዮጵያ ሕዝባዊ መንግስት እንመሰርታለን በማለት የሰውን ልጅ ክቡር ሕይወት በከንቱ የሚያስቀጥፉና የብዙ ለሐገራቸው ቀና አመለካከት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ጊዜና ገንዘብ እያባከኑ አካሔዳቸው ስህተት እንዳለበት ሲነገራቸው እንደ አበደ ውሻ ያዙኝ ልቀቁኝ የሚሉ ሰዎችን ስመለከት የፖለቲካ አድርባይነትና የግል ፍላጎት ያወረውን የእነዚህን ድርጅቶች የፖለቲካ አስተሳሰብ ለማረቅ ፈታኝ ትግል እንደሚጠይቅ ተገንዝቢያለሁ፡፡
ለማጠቃለል በታሪክ እንደምንገነዘበውና አሁንም በቃለ ምልልሱ እንደተረዳሁት በኢሳያስና በሻቢያ ድጋፍ ለኢትዮጵያ መልካም ነገር እናመጣለን ማለት ከእባብ እንቁላል እርግብ እንደመጠበቅ ነው፡፡ስለሆነም የኢትዮጵያ ሃቀኛ የፖለቲካ ሃይሎች ይህንን አውዳሚ ተግባር በይፋ ልንታገለው ይገባል፡፡
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

ከመቀሌ – እንዳስላሴ የታቀደውን የባቡር ሀዲድ ሀይለማርያም ሰረዘው እየተባለ የሚለቀቀው ዲስኩር ሽፋን ነው፡፡ Tesfaye Ru


    


ከመቀሌ – እንዳስላሴ የታቀደውን የባቡር ሀዲድ ሀይለማርያም ሰረዘው እየተባለ የሚለቀቀው ዲስኩር ሽፋን ነው፡፡ Tesfaye Ru
ከአዋሽ-ኮምቦልቻ-መቀሌ ያለው የባቡር ሀዲድ ዋጋ ከአባይ ግድብ በላይ ዋጋ ወጥቶበት በመሰራት ላይ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ብር አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አቅም ግን ከሙስናና ዝርፊያ ተርፎ አባይን መጨረስ አቅቶት በ6ኛ አመቱ ግማሽ ላይ ደርሶ አሁን መራመድ አቅቶት ወገቤን እያለ ነው፡፡
ባቡር ትርፋማ ስለሆነ ከአዋሽ- ኮምቦልቻ-ሃራ ገበያ ያለውን የአውሮፓ ህብረት አበደረ፡፡ ከሀራ መቀሌ ያለውን የቻይና ባለስልጣናትን አስክረው በስካር መንፈስ አስፈርመዋቸው ነው መሰለኝ፤ የቻይና ኤግዚም ባንክ ሸፍኖታል፡፡
እስከ ኮምቦልቻ- ሀራ ገበያ ያለው ሀዲድ የተሰራው በወሎ፣ ጎንደርና፣ ጎጃም ማሊያ መቀሌ ተጫውታ ባስለቀቀች ገንዘብ ነው፡፡
economically profitable, technically feasible የሚል ነገር መጨረሻው ላይ ላልተፃፈበት ፕሮፖዛል ፈረንጅ አያበድርም፡፡ እና እንዳስላሴ ይቺን የአዋጪነት መስፈርት ስላላሟላች ብድር ስላልተገኘ ተገደው የቀረውን ፕሮጀክት ወያኔ በራሱ ፍላጎት፥ ተመጣጣኝ የመሰረተ ልማት ክፍፍል ሊያደርግ አስቦ እንደተወው አድርጎ መወራቱ ያሳፍራል፡፡
ወያኔ ለተንኮል ከባህር ዳርና ከመተማ የሚነሳው ሀዲድ በወልዲያ ብሎ አዋሽ ጋር ይገናኛል በሚለው ፕሮፖዛሉ የመቀሌውን ሀዲድ በግርግር በአማራ ከተሞች ሽፋን ተጠቀመ፡፡
ትክክለኛው፣ አትራፊውና ለመስራትም ምቹ የሆነው መንገድ ከመተማና ጎንደር የሚነሳው ወረታ ላይ ተገናኝቶ በባህር ዳር ብሎ፣ በማርቆስ አድርጎ፣ በደጀን ብሎ፣ 20ኪ/ሜ አካባቢ የመሬት ውስጥ ተነል ከደጀን ውስጥ ለውስጥ አባይ ላይ በሚሰራ ድልድይ አልፎ ዳግም በተነል ወደ ጎሃ ጽዮን አካባቢ ወጥቶ በመሬት ላይ ቀጥታ ወደ አዲስ አበባ መግባት ይችላል፡፡ ከአባይ ሸለቆ በስተቀር ሁሉም ሜዳ ለሜዳ ስለሆነ ለመስራት ርካሽና በጣም ጠቃሚ አማራጭ ነበር፡፡ ነገር ግን ለትግራይ ጥቅም ጎጃምና ጎንደርን መስዋዕትነት አስከፈሉ፡፡
አሁን ከባህር ዳር አዲስ አበባ ለመግባት የዙሪያ ጥምጥም መጓዝ ምን ይባላል? ያውም ለጉዞ ምቹ ባልሆነ ሞቃት መንገድ በረሃ ለበረሃ፡፡ ሰዎች በባቡር በዚያ ከሚጓዙ በመኪና በደጀን መሄድን ይመርጣሉ፡፡
እዳውን ለመክፈል ግን አብረን ስንገተገት እንኖራለን፡፡
ደግሞም አበዳሪ ያጣው የእንዳስላሴና አክሱሙም አይቀርም፡፡ አበዳሪ ቢጠፋም እንደ አባይ ግድብ “እኛው በእኛው እንሰራዋለን” ይባልና የህዳሴው ሀዲድ እየተባለ ህዝቡ መገፍገፍ ይጀምር ይሆናል፡፡

Thursday, April 27, 2017

የተጋድሎው አይዲዮሎጅ ምን እንደሆነ ይነገረን! በተለይ ለአርበኞች ግንቦት ሰባት


መስቀሉ አየለ
አንድ ድርጅት ምንነቱ የሚመዘነው አንድም ድርጅቱ በተቋቋመበት አላማ፣ ድርጅቱን በሚመሩት የሰዎች አይነት፣ሰዎቹ የድርጅቱን አለማ ወደ ጫፍ ለማድረስ ያላቸው ቁርጠኝነት እና ይኽ ድርጅቱ ከራሱም ባሻገር ከሌሎች መሰል ተቋማትም ሆነ እታገልለታለሁ ከሚለው ማህብረሰብ ጋር ያለው ቀጥተኛ ግንኙነት ጭምር ነው።

ወያኔ በዚህ ስሌት ሲመዘን የድርጅቱ ጠንሳሽና አንኳር ናቸው የሚባሉቱ ሰዎች በዘመን እርዝመት የማይጠግግ በጸረ ኢትዮያዊነት ይልቁንም በጸረ አማራና ኦርቶዶክስ ሽንት ተቦክተው የተጋገሩ ናቸው።ይኽን አላማ ዳር ለማረስ የሚያስችል ደግሞ በቂ ጥላቻ አላቸው። በአስራ ዘጠኝ ስልሳ ስምንት የተጻፈው የደደቢቱ ማኔፌስቶ እስከ አሁን ያልተሰረዘው ለዚህ ነው። ጠንካራ ጎናቸው ነው ከተባለ የወያኔ ጠንካራ ጎን ይኼው ጠላቴ ብሎ ባሳመረው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ያለውን አቋም ዛሬም ከአራት አስርተ አመታት ቦሃላ እንኳን ሳይቀር በጥርሱ ነክሶ እንደያዘ መቆየት መቻሉ ነው።ይኽ ማለት ትሃት ወያኔ፣ ኢህ አዴግ ብሄር-ብሄረሰቦች፣ ቦናፓርቲዝም፣ አብዮታዊ ዲሞክራሲና ህዳሴው ሽህ አይነት ስም ይሰጠው እንጅ በመርህ ደረጃ የወያኔ አይዲዮሎጅ አማራን ብሎም ኢትዮጵያን ማጥፋት መሆ ዛሬ ለማንም ጠርቶ የወጣ እውነት ሆኗልና ለክርክር የሚጠፋ ጉልበት የለም::
በሌላ በኩል ይህን ሰይጣናዊ አላማ ተፈጻሚ ለማድረግ ከፊት የተሰለፉት እነዚህ የስርአቱ ጉምቱዎች ከድቁርና፣ ከበታችነት ስሜት፤ ከጥላቻና ከችጋር ሰቀቀን የወጡ መሆናቸው፣ በታሪክ አጋጣሚ አንድ ግዜ እጃቸው ላይ ከገባው ስልጣን ውጭ ሌላ ነገን የማየት አቅም ማጣታቸው ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቢወጡ ሌላ ሊሆኑ የሚችሉት ምንም አይነት ማንነት የሌላቸው፤ ከጸጋ በታች እራቁታቸውን የተወለዱ መሆናቸው ነው። እንዲህ አይነት ሰዎች ደግሞ ከስልጣን ወንበራቸው ላይ ተጣብቆ ለመሞት ካላቸው እልህ የተነሳ ዛሬ በምናየው ደረጃም ሆነ ነገ በሚገለጠው የከፋው ማንነታቸው ቢከሰቱ ሊደንቀን አይገባም።

የሰላማዊ ትግል ክሽፈት

ባለፉት እሩብ ምዕተ አመታት ለውጥ ለማምጣት በአገራችን ውስጥ የተደረጉት ሰላማዊ ትግሎች በሙሉ ጸሃይ እንደገላመጠው ጉም በነው የጠፉትበት ምክንያቱ ዛሬም ይህንን አጀንዳ መኖሪያ ያደረጉት የጆሊ ባር አካባቢ ፖለቲከኞች እንደሚሉት “ሰላማዊ ትግሉ በሚገባ ስላልተፈተሸ” አይደለም። መሰረታዊ ችግሩ ከላይ በደምሳሳው የተቀመጠው የወያኔ ባህሪ ነው። ከሰብአዊ መብት ተሟጋች እስከ ነጻው ፕሬስ ጋዜጠኛ፣ ከዋልድባ ምናኔ እስከ ተዋዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ሁሉም ያልተቻሉባት፣ ይልቁንም አገሩን መግዛት ከጀመሩ ከሁለት አስርተ አመታት ቦሃላ ሳይቀር 99.82 ፐርሰንት የፓርላማ ወንበር ይዘው አንድ ግርማ ሰይፉ ጸጉረ ልውጥ ሆኖ ስለገባባቸው የተፈጠረባቸውን ስጋት ታዝበናል; የሰላም ትግል ብሎ ብሎም ቀሪ የተስፋ ጭላንጭል እንደማይታሰብ አረጋግጠናል።ይልቁንም የፖለቲካ ፓርቲዎችን ምርጫ “ካልኩሌቲቭ ሪስክ” ነው ብሎ የደመደመ፣ “በምርጫ ስልጣን ለመያዝ የሚያስቡ ካሉ እግር እስኪያወጡ መጠበቅና ጠብቆ በመቁረጥ ስሌት የምንሄድ መሆኑን ይወቁት” ብሎ ግልጥ ባለ አማርኛ የድጅቱን እውነተኛ ባህሪ “ከውስጥ ከፍቶ ያሳየው” የስርዓቱ አፈ ሊቅ ተክሎት የሄደው የመርዝ ሰንኮፋ ዛሬም ከአራት ኪሎ አልወጣምና በሽታው እስካልተነቀለ ድረስ ቁስሉ ሲመረቅዝ መኖሩ የግድ ነው።

የፖለቲካ አመራር ብቃት ማነስ በአሜሪካ ስህተት፣ በኢትዮጲያ ውድቀት ያስከትላል



ከስዩም ተሾመ
የበለፀገ ኢኮኖሚ እና የዳበረ ዴሞክራሲ ያላቸው ሀገራት አንዴ ጦረኛ፥ ሌላ ግዜ ምሁር፣ ከዛ ደግሞ ዘረኛ የሆነ መሪ ሊኖራቸው ይችላል። ለምሳሌ አሜሪካ እንደ ጆርጅ ቡሽ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የአፍጋኒስታን፣ ኢራቅ፣ ፓኪስታን፣…ወዘተ ዜጎችን ለሞት፥ ሥቃይና ስደት የዳረገ ጦረኛ ፕረዜዳንት ነበራት። ከእሱ ቀጥሎ ደግሞ ገና ለፕረዜዳንትነት በተመረጠ ማግስት የዓለም የሰላም ኖቬል ሽልማትን የተሸለመው ባራክ ኦባማ መርቷታል። በአሜሪካ የመጀመሪያው ጥቁር ፕረዜዳንት የተተካው ግን የመጨረሻ የነጭ አካራሪና ዘረኛ በሆነው ዶናልድ ትራምፕ ነው።
ስዩም ተሾመ
በዚህ መልኩ ፕ/ት ጆርጅ ቡሽ ያበላሸውን ገፅታ ባራክ ኦባማ ሲገነባ፣ ፕ/ት ባራክ ኦባማ የገነባውን ገፅታ ዶናልድ ትራምፕ መልሶ ያፈርሳል። ያም ሆኖ ግን፣ የአሜሪካ ፕረዜዳንቶች የፖለቲካ አመራር ብቃት በሀገሪቱ የወደፊት ዕጣ-ፋንታ እና በሕዝቡ ሕይወት ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖ በጣም ውስን ነው። እንደ ኢትዮጲያ ባሉ የበለፀገ ኢኮኖሚ እና የዳበረ ፖለቲካዊ ሥርዓት በሌላቸው ሀገራት ግን የመሪዎች የአመራር ብቃት የሕልውና ጉዳይ ነው። ምክንያቱም፣ የደሃ ሀገራት መሪዎች የፖለቲካ አመራር ብቃት በሀገሪቱ ሰላም፥ ልማትና ዴሞክራሲ ከማረጋገጥ ጋር ቀጥተኛ የሆነ ተያያዥነት አለው።
ደቡብ አፍሪካዊው ፀኃፊ “William Gumede” ስለ ጉዳዩ በሰጠው ትንታኔ መሰረት፣ የፖለቲካ አመራር ብቃት ከበለፀጉ ሀገራት ይልቅ በደሃና ታዳጊ ሀገራት ዘንድ እጅግ ወሳኝ የሆነ ሚና አለው። ምክንያቱም፣ የበለፀጉ ሀገራት በተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ከፍተኛ የዕውቀትና የልምድ ክምችት አለ። ከዚህ በተጨማሪ፣ አስፈላጊው የፖለቲካ አመራር ብቃት የሌለውን መሪ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ አማካኝነት በቀላሉ ከስልጣን ማውረድና በሌላ መተካት ይችላሉ።
እንደ ኢትዮጲያ ባሉ የአፍርካ ሀገራት ግን የፖለቲካ መሪዎች ብቃት የሀገራቱን ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ወደፊት ሊያስቀጥል ወይም ወደኋላ ሊቀለብስ ይችላል። እንደ ፀኃፊው አገላለፅ፣ እንደ ኢትዮጲያ ባሉ ሀገራት የሕዝቡ ሰላምና ደህንነት፥ የሀገሪቱ ልማትና ዴሞክራሲ በዋናነት የተመሰረተው በፖለቲካ መሪዎች የአመራር ብቃት ላይ እንደሆነ እንደሚከተለው ገልፆታል፡-
“In poor countries, competent political leadership is a scarce skill that matters even more than in industrial nations. Industrial nations, where power is dispersed across the society, can tolerate bad leaders better. Better still, bad leaders can generally be outvoted. The right kind of leader in fractious, ethnical diverse and underdeveloped African countries, can be a rallying force that helps binds them together, and helps unleash the country’s productive energies. A bad leader, in the context of fragile democratic institutions, ethnic diversity, and underdevelopment, can be terribly destructive – holding back democracy, growth and nation-building. Worse, in African countries bad leaders are difficult to rid of, and remain a drain on the system long after they are eventually gone.” William Gumede, Pambazuka News, Nov 26, 2009

ከላይ በጥቅሱ እንደተገለፀው፣ የተጠናከሩ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት፣ የተለያዩ ብሄሮች፥ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች፣ እና ዝቅተኛ ልማት ባለበት ሀገር ብቃት የሌለው የፖለቲካ መሪ ለሀገሪቱ እድገት፣ ዴሞክራሲ እና አንድነት ዋና እንቅፋት ነው። ነገር ግን፣ የችግሩ መሰረታዊ መንስዔ ከብሄር ልዩነት ወይም ከሀገሪቱ የልማት ደረጃ ጋር ይልቅ የተጠናከሩ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ካለመኖራቸው ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው።
በመሰረቱ፣ ውሳኔ መስጠት (Decision making) ከተለያዩ አማራጭ የውሳኔ ሃሳቦች ውስጥ አንዱን መምረጥ ነው። በዚህ መሰረት፣ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ባላቸው ሀገራት የፖለቲካ ውሳኔና አመራር መስጠት በጣም ቀላል ነው። በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ አማራጭ የውሳኔ ሃሳቦች የሚቀርበው ከአራት የተለያዩ አቅጣጫዎች ነው።
ለምሳሌ፣ አዲሱ የአሜሪካ ፕረዜዳንት ገና ወደ ስልጣን እንደመጡ በተወሰኑ ሀገሮች ላይ የጉዞ እገዳ መጣላቸው ይታወሳል። በመጀመሪያ ይህ የውሳኔ ሃሳብ የቀረበው ከራሳቸው ከፕረዜዳንቱ፣ ከካቢኔያቸው ወይም ከአማካሪዎቻቸው ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ፣ አንድ የውሳኔ ሃሳብ ለፕረዜዳንቱ መቅረቡ እንደታወቀ በዋናነት የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሚዲያ ተቋማትና የሙያና ሲቭል ማህበራት የእያንዳንዱን አማራጭ የውሳኔ ሃሳብ አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች በዝርዝር እየተነተኑ ማቅረብ ይጀምራሉ። ስለዚህ፣ የፖለቲካ መሪው የውሳኔ ሃሳቡን ያሻሽላል። በዚህም ከሁሉም አማራጮች የተሻለው የውሳኔ ሃሳብ ተቀብሎ ያፀድቃል። ልክ ፕ/ት ዶናልድ ትራምፕ የእነዚህን አካላት ሃሳብና አስተያያት ችላ ብሎ ተቀባይነት የሌለው ውሳኔ የሚያሳልፍ ከሆነ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውድቅ ይደረጋል።
በኢትዮጲያ ሰፊ የሆነ የብሄር ልዩነት እና ዝቅተኛ ልማት መኖሩ እርግጥ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ በፖለቲካዊና ታሪካዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባት የለም። ከሁሉም በለይ ግን በሀገሪቱ ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት የሉም። የኢህአዴግ መንግስት ባለፉት አስር አመታት ውስጥ በፀረ-ሽብር ሕጉ፣ በሚዲያ ሕጉ፣ እንዲሁም የበጎ-አድራጎት ተቋማት ማቋቋሚያ አዋጅን ተግባራዊ በማድረጉ በሀገሪቱ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መዋቅር ሙሉ-በሙሉ ፈርሷል። በዚህ ምክንያት፣ ኢትዮጲያ ውስጥ ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት የሚባሉት፤ ነፃና ገለልተኛ የሚዲያ ተቋማት፣ የተደራጁ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶች እና የሲቪል ማህበራት ከነጭራሹ የሉም ማለት ይቻላል።
የፖለቲካ መሪዎች ውሳኔና አመራር የሚሰጡት ከተለያዩ አማራጮች ውስጥ የተሻለውን የውሳኔ ሃሳብን በመምረጥ ነው። እንደ አሜሪካ ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት ካላቸው ሀገራት አንፃር ሲታይ በኢትዮጲያ የፖለቲካ ውሳኔና አመራር መስጠት በጣም ከባድ ነው። ቀደም ሲል ለመግለፅ እንደተሞከረው፣ የዳበረ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ባላቸው ሀገራት አማራጭ የውሳኔ ሃሳቦች የሚቀርቡት ከአራት የተለያዩ አቅጣጫዎች ነው። ነገር ግን፣ እንደ ኢትዮጲያ ነፃና ገለልተኛ የሚዲያ ተቋማት፣ የተደራጁ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶች እና የሲቪል ማህበራት በሌሉበት አማራጭ የውሳኔ ሃሳቦች የሚቀርቡት ከአንድ ወገን ብቻ ነው።
ለምሳሌ፣ ከአሜሪካው ፕሬዜዳንት ወይም ደግሞ ከእንግሊዝ ጠ/ሚኒስትር አንፃር ሲታይ የኢትዮጲያው ጠ/ሚኒስትር ውሳኔና መመሪያ የሚሰጡት ልክ በድቅድቅ ጭለማ ውስጥ እንዳለ ሰው ነው። በራሳቸው ከሚያውቁት፣ ከፓርቲያቸው ወይም ከአማካሪዎቻቸው ከተሰጣቸው ውጪ፤ የውሳኔያቸውን አግባብነት ለመፈተሸ የሚያስችሉ አስተያየቶች፣ ሌሎች አማራጭ የውሳኔ ሃሳቦች ስለመኖራቸው፣ ወይም ውሳኔያቸው ስለሚያስከትለው አሉታዊና አዎንታዊ ጎን ተጨማሪ ሃሳብና አስተያየት የሚያገኙበት መንገድ የለም። ስለዚህ፣ ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ልክ በድቅድቅ ጭለማ ክፍል ውስጥ እንዳለ ሰው በራሳቸው በሚያውቁትና በመሰላቸው መንገድ የፖለቲካ ውሳኔና መመሪ ይሰጣሉ።
“William Gumede” እንዳለው፣ በአብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት የሕዝቡ ሰላምና ደህንነት፥ የሀገሪቱ ልማትና ዴሞክራሲ በዋናነት በመሪዎቹ የአመራር ብቃት ላይ የተመሰረተ ነው። ለዚህ ዋናው ምክንያት ከላይ የተጠቀሰው ጭለማ ነው። የፖለቲካ መሪዎቹ፣ ከገዢው ፓርቲ አባላትና አመራሮች በተጨማሪ፣ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ ሃሳቦችና አስተያየቶችን የሚቀበሉ ከሆነ፣ በዚህም በትክክለኛ መረጃና ዕውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ፣ እንዲሁም በተግባር የተደገፈ መመሪያ የሚሰጡ ከሆነ የሕዝቡ ሰላምና ደህንነት፣ የሀገሪቱ ልማትና ዴሞክራሲ ማረጋገጥ ይችላሉ።
ነገር ግን፣ ጠንካራ የዴሞክራሲ ተቋማት በሌለበት ሁኔታ የሀገሪቱ መሪዎች በራሳቸው ተነሳሸነት የሕዝቡን ጥያቄና ፍላጎት ለማወቅ ጥረት ካላደረጉ፣ ከአንድ ወገን በመጣ መረጃ ላይ ብቻ ተመስርተው ውሳኔና መመሪያ የሚሰጡ ከሆነ የፖለቲካ አመራር ብቃት የላቸውም። እነዚህ መሪዎች የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሥርዓት ለመዘርጋት አስፈላጊ የሆነውን የአመራርነት ሚና መወጣት አይችሉም። የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሥርዓትና ቁርጠኛ አመራር በሌለበት ሁኔታ የሀገሪቱን ሰላምና ልማት በዘላቂነት ማረጋገጥ አይቻልም። በመሆኑም፣ እንዲህ ያሉ የፖለቲካ አመራር ብቃት የሌላቸው መሪዎች ለሀገር ሰላም፥ ልማትና ዴሞክራሲ እንቅፋት ናቸው።
በዚህ መሰረት፣ “የሀገራችን መሪዎች የፖለቲካ አመራር ብቃት እንዴት ይታያል?” የሚለውን በሌላ ፅሁፍ እመለስበታለሁ። እንደው በጥቅሉ ሲታይ ግን፣ አሁን በሀገራችን የሚስተዋለው መሰረታዊ ችግር የመልካም አስተዳደር እጦት ወይም የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት አይደለም። ከዚያ ይልቅ፣ የሀገሪቱ መሰረታዊ ችግር የመሪዎቿ የፖለቲካ አመራር ብቃት ማነስ ነው።

የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን: የፕሮጀክት አጋሮቹን ለምክክር ሊጠራ ነው


ሐራ ዘተዋሕዶ
  • የማኅበረሰብ ተጠያቂነት አጋርነት ማሕቀፍ ትግበራ፣ ከአጋሮች ጋራ ግንኙነቱን አጠናክሮታል
  • በዘላቂ ልማት እና የአገልግሎት ጥራት፣ የምርጥ ተሞክሮ ግምገማ በተከታታይ ተሸላሚ ኾኗል
  • የበጎ አድራጎት ሕጉ፣ በኮሚሽኑ የውጭ ለጋሽ ድርጅቶች ርዳታ አሰጣጥ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሯል
  • የገቢ ምንጭ መምሪያ በማደራጀት፣ የገንዘብ አቅሙን በሀገር ሀብት ለማጠናከር እየሠራ ይገኛል
  • ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆ ራስን ለመቻል ይረዳናል ያልነውን ጥናት አዘጋጅተናል”/ሊቀ ጳጳሱ/
**
ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል፤ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ
*
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን፣ ከውጭ የርዳታ ጥገኝነት ለመላቀቅ የሚያስችለው ሕግና ደንብ ማዘጋጀቱን የገለጸ ሲኾን፤ ከፕሮጀክት አጋሮቹ ጋራ በቀጣይ ስለሚኖረው የሥራ ግንኙነት ለመምከር ማቀዱን አስታወቀ፡፡
የዓለም አቀፍ ለጋሾች ርዳታ፣ ለተወሰነ የሽግግር ጊዜ ከመርዳቱ በቀር በዘላቂነት የሚጠቅም እንዳልኾነ ለሳምንታዊው ሰንደቅ ጋዜጣ የተናገሩት የኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል፣ ለልማትና ተራድኦ የሚውል ሀብት ከሀገር ውስጥ ለማሰባሰብ የሚያስችል ሕግና ደንብ በኮሚሽኑ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
“ጥናቱ ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆን ራሳችን እንድንችል የሚረዳን ይኾናል፤” ያሉት ብፁዕነታቸው፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ጨምሮ ሌሎች ምሁራንን በማሳተፍ መዘጋጀቱንና ለቅዱስ ሲኖዶስ ቀርቦ ሲጸድቅ በሥራ ላይ እንደሚውል ጠቁመዋል፡፡
ከ10 በመቶ በላይ ከውጭ ለጋሾች ገንዘብ መቀበል እንደማይቻል የሚከለክለው (የ10 በ90) የበጎ አድራጎት ሕጉ፣ የሀገሪቱንና የረጂዎችን ኹኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ ባለመኾኑ ተጽዕኖ እየፈጠረ እንዳለ የኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስ ተናግረዋል፡፡
ይህ 10 በ90(10 ከመቶ በላይ ከውጭ ለጋሾች ገንዘብ መቀበል አይቻልም) የሚለው የውጭ ለጋሽ ድርጅቶች ብዙም አልተቀበሉትም። እርሱ ነው ተጽዕኖ እየፈጠረ ያለው። ሕጉ፥ የሀገሪቱንና የረጂዎችን ኹኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም።
ያም ኾኖ፣ ከዓለም የኢኮኖሚ ቀውስና ረጂዎች በዓለም ዙሪያ ቅድሚያ የሚሰጧቸው ችግሮች በመብዛታቸው የውጭ ርዳታ እየቀነሰ በመምጣቱ፣ ኮሚሽኑ ከውጭ ከሚያገኘው የርዳታ ድጋፍ በተጨማሪ የገቢ አቅሙን የሚያጠናክርበት የተለያዩ ዕቅዶች ማዘጋጀቱን ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ጠቅሰዋል፤ የኮሚሽኑ የገቢ ምንጭ መምሪያ መደራጀቱንና የተጀመሩ ሥራዎችም እንዳሉ ዘርዝረዋል፡፡
የልማትና ክርስቲያናዊ ኮሚሽኑ፣ በአኹኑ ወቅት ከለጋሽ አካላት ጋራ ስላለውና በቀጣይ ስለሚኖረው ግንኙነት ሰንደቅ የጠየቃቸው ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ፣ የኮሚሽኑ እንቅስቃሴ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለበት በመኾኑ በየጊዜው ከለጋሽ ድርጅቶች አዎንታዊ ምላሽ እያገኘ እንዳለ ተናግረዋል፡፡ በተገበራቸውና ዘላቂነታቸው በተረጋገጡ የልማት ተቋማትና ለኅብረተሰቡ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ጥራት፣ በክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ድርጅት ጥምረት(CCRDA) በተደረገው የምርጥ ተሞክሮ ግምገማ፣ በአገሪቷ ከሚንቀሳቀሱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች መካከል ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በቀዳሚነት አሸናፊ ኾኖ ለመሸለም መብቃቱን በዐብይ አስረጅነት ጠቅሰዋል፡፡

  • በተለያዩ ክልሎች 27 የማኅበረሰብ ልማት ፕሮጀክቶች፤
  • ከ10ሺሕ በላይ አሳዳጊ አልባ ሕፃናት ክብካቤ፤
  • በ18 የመጠለያ ካምፖች ከ810ሺሕ በላይ ስደተኞች፤

በተለይ ኮሚሽኑ፣ የማኅበረሰብ ተጠያቂነት አጋርነት(Humanitarian Accountability Partnership) ማሕቀፍ አዘጋጅቶና አጽድቆ በመተግበሩና የሕፃናት ፖሊሲን ቀርፆና አጽድቆ በሥራ ላይ በማዋሉ ከአጋር ድርጅቶች ጋራ ያለው ግንኙነት የበለጠ ተጠናክሯል።
ከኹሉንም የፕሮጀክት አጋሮች ጋራ ኮሚሽኑ ባለው የጋራ አጀንዳና በቀጣይ ስለሚኖረው የሥራ ግንኙነት በተመለከተ ከተወካዮቻቸው ጋራ በቅርቡ ለመወያየት ዕቅድ መያዙን በምላሻቸው የጠቆሙት ብፁዕነታቸው፣ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡
“ዋናው ጉዳይ የታለመለትን ፕሮጀክት በጥራትና ዘላቂ ጥቅም በሚሰጥ መልኩ በጽናት ማከናወን ነው፤” ያሉት ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ አያይዘው እንደገለጹት፥ የክልል፣ የዞንና የወረዳ መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶችም፣ ኮሚሽኑ የተገበራቸውን የልማት ሥራዎችና በተጠቃሚው ኅብረተሰብ ላይ ያመጣውን ተጨባጭ ለውጥ በመመልከት ምስጋናና ዕውቅና እየቸሩት ይገኛሉ፤ ብለዋል፡፡
ከዛሬ 46 ዓመታት በፊት የተመሠረተውና በእንቅስቃሴውም አብዛኛውን የኢትዮጵያ አካባቢዎች(ክልሎች) በመሸፈን ላቅ ያለ ማኅበራዊ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የልማትና ክርስቲያናዊ ኮሚሽን፣ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የበጐ አድራጐት ድርጅቶችና ማኅበራት ኤጄንሲ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 621/2001 መሠረት፣ በኢትዮጵያዊ ነዋሪዎች በጐ አድራጐት ድርጅትነት በምዝገባ ቁጥር 1560 ተመዝግቦ የማኅበራዊና የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ሰንደቅ ጋዜጣ፣ በትላንት፣ ሚያዝያ 18 ቀን 2009 ዓ.ም. እትሙ ያወጣውና ከኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ጋራ ያደረገው ቃለ ምልልስ ሙሉ ይዘት የሚከተለው ነው፡፡

በሀገር ውስጥ የሀብት ማሰብሳብ ከውጭ ጥገኝነት ለመላቀቅ እየሠራ ያለ ተቋም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን፣ ከዛሬ 46 ዓመታት በፊት የተመሠረተና በእንቅስቃሴውም አብዛኛውን የኢትዮጵያ አካባቢዎች(ክልሎች) በመሸፈን ላቅ ያለ ማኅበራዊ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ነው።
ኮሚሽኑ ከሚያደርጋቸው መጠነ ሰፊ የልማትና የርዳታ ሥራዎች ጋራ በተያያዘ፣ ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ድርጅት ጥምረት (CCRDA) በተደረገው የምርጥ ተሞክሮ ግምገማ፣ በአገራችን ከሚንቀሳቀሱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች መካከል በቀዳሚ አርኣያነት አሸናፊ ኾኖ ለመሸለም በቅቷል። በዚኽና መሰል ጉዳዮች ከኮሚሽኑ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ጋራ ባልደረባችን ፍሬው አበበ ያደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ተጠናቅሮ ቀርቧል።

ሰንደቅ፡- ኮሚሽኑ በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ውስጥ ያለውን አደረጃጀት ቢገልጹልን?
ብፁዕነታቸው፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን፣ በሕግ ክፍል ማስታወቂያ 415/1964 በነጋሪት ጋዜጣ፣ ከታኅሣሥ 26 ቀን 1964 ዓ.ም. ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ውስጥ ራሱን የቻለ መሥሪያ ቤት በመኾን ተቋቁሞ የሚሠራ ሲኾን፤ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ መንግሥት፣ የበጐ አድራጐት ድርጅቶችና ማኅበራት ኤጄንሲ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 621/2001 መሠረት፣ በኢትዮጵያዊ ነዋሪዎች በጐ አድራጐት ድርጅትነት በምዝገባ ቁጥር 1560 ተመዝግቦ የማኅበራዊና የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኝ የበጐ አድራጐት ድርጅት ነው። ድርጅቱ፥ ጠቅላላ ጉባኤ፣ ቦርድና የአመራር አባላት ያሉት ኮሚሽን ነው።
በመኾኑም የልማት ኮሚሽን፣ ቤተ ክርስቲያን፣ የወገን ደራሽነቷን ለማረጋገጥ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የነፍስ አድን ርዳታ በማድረግ ብሎም መልሶ በማቋቋምና በልማት በማገዝ ፈርጀ ብዙ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶአል፤ አኹንም እየሰጠ ይገኛል።
ሰንደቅ፡- በአኹኑ ሰዓት የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ዋና ዋና ትኩረቶች ምንድን ናቸው?
ብፁዕነታቸው፡- የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፥ የገጠር ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክቶች የሚስፋፉበትን መንገድ መቀየስ፤ በገጠር የሚኖሩ ዜጐች የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ የሚኾኑበትን መንገድ መቀየስና መሥራት፤ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ የተቀናጀና የተጠናከረ ሥራ መሥራት፤ በሥነ ተዋልዶ ጤና ላይ የበኩሉን የሥራ ድርሻ ማበርከት፤ በእናቶችና ሕፃናት ሥርዓተ ምግብ ላይ ትርጉም ባለው መንገድ መሳተፍ፤ ስደተኞችን የመቀበልና ማስተናገድ ሥራን አጠናክሮ መቀጠል፤ ችግር ፈቺ የኾኑ የልማት ሥራዎችን በማጥናትና በፕሮጀክት በማካተት ሥራ ዐጥ ወጣቶችንና ችግረኛ ሴቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ኑሮአቸው የተሻሻለ እንዲኾን ማገዝና የመሳሰሉት ናቸው።
ሰንደቅ፡- በልማት የተለያዩ ዘርፎች በኮሚሽኑ የተከናወኑ ተግባራትና ተጨባጭ ውጤቶች ምን ምንድን ናቸው?
ብፁዕነታቸው፡- ኮሚሽኑ ከበርካታ ሀገር አቀፍና የውጭ በጎ አድራጐት ድርጅቶች ጋራ አጋርነት በመፍጠር፣ በአገሪቷ የተለያዩ ክልሎች የሚኖሩ አያሌ ማኅበረሰቦች ካሉባቸው ችግሮች እንዲላቀቁ በማድረግ ከመንግሥትና ከሕዝብ ጎን በመኾን አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ ችሏል።
ይኸውም በበርካታ ወረዳዎች የገጠር ልማት ፕሮጀክቶችን በመተግበር፥ በመስኖ፣ በንጹሕ መጠጥ ውኃ፣ የተሻሻሉ የግብርና ዘዴዎችን በማዝለቅ፣ በገቢ ምንጭ ተግባራት፣ በአቅም ግንባታ፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ በማኅበረሰብ የአደጋ ጊዜ መቋቋሚያና መጠባበቂያ ፈንድ ማኅበራትን በመመሥረትና በማጠናከር፣ በሥርዓተ ምግብ አጠቃቀም፣ በሥነ ተዋልዶ ጤና፣ በፀረ-ኤች.አይ.ቪና በመሳሰሉት የበኩሉን አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ይገኛል።
በሌላ በኩል፣ በኮሚሽኑ ሥር ባለው የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች መምሪያ አማካይነት፣ ከጐረቤት ሀገራት ተሰደው የሚመጡትንና ከስደት ተመላሾችን፣ ኮሚሽኑ ባቋቋመው የስደተኛ ካምፖች በመቀበል አስፈላጊውን ሰብአዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች እንዲያገኙ አድርጓል። ለዚህም፣ ልማት ኮሚሽኑ በተገበራቸው ዘላቂነታቸው በተረጋገጡ የልማት ተቋማትና ለኅብረተሰቡ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ጥራት፣ በክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ድርጅት ጥምረት(CCRDA) በተደረገው የምርጥ ተሞክሮ ግምገማ፣ በአገሪቷ ከሚንቀሳቀሱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች መካከል ለሦስት ተከታታይ ዓመታት በቀዳሚነት አሸናፊ ኾኖ ለመሸለም መብቃቱ በዐብይ አስረጅነት ሊጠቀስ ይችላል።
በተጨማሪም በመንግሥት የክልል፣ የዞንና የወረዳ መሥሪያ ቤቶች የልማት ኮሚሽናችን በተገበራቸው የልማት ሥራዎች፣ በተጠቃሚው ኅብረተሰብ ላይ ያመጣውን ተጨባጭ ለውጥ በመመልከት ምስጋናና ዕውቅና እየቸሩን ይገኛሉ።
ሰንደቅ፡- በክርስቲያናዊ ተራድኦ ረገድ፣ በተለይም ከአየር ንብረት ለውጥና ከድርቅ ጋራ በተያያዙ የተፈጥሮ አደጋዎች ኮሚሽኑ የፈጸማቸውን ጉዳዮች ቢዘረዝሩልን?
ብፁዕነታቸው፡- ልማት ኮሚሽኑ፣ በአኹኑ ሰዓት ለዓለም አስጊ ለኾነው የአየር ለውጥ ችግር ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት፣ የአየር ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመቋቋም የሚያስችሉ የልማት ሥራዎችን በፕሮጀክት ጥናቶቹ በማካተት ተግባር ላይ እያዋለ ነው። ይኸውም ለተጠቃሚ አርሶ አደሮች የአየር ለውጥ መቋቋም የሚችሉ የሰብል ዝርያዎችን በማቅረብና በማከፋፈል፤ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት፤ የተፈጥሮ ሀብት ክብካቤና ጥበቃ ሥራን በማጠናከር የጎላ ተግባር እያከናወነ ነው።
ልማት ኮሚሽኑ ለቤተ ክርስቲያን ደን ልማትና ጥበቃ ከምንጊዜውም በላይ ትኩረት በመስጠት፣ የቤተ ክርስቲያን ደን ፕሮጀክት አጥንቶ በአጋርነት የሚሠራ ድርጅት በማግኘቱ፣ በተመረጡ ገዳማት ላይ የደን ጥበቃና ማስፋፋት ሥራን መሠረት በማድረግ፣ የተራቆቱ መሬቶች በደን የሚሸፈኑበትን ኹኔታ ለማስቻል ደረጃ በደረጃ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በተጨማሪም ኮሚሽኑ፣ የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጅና የሶላር መብራት ተከላ፣ በ15 ገዳማት ያከናወነ ሲኾን፣ ለወደፊቱም በሰፊው የሚሠራበት የልማት መስክ ኾኖ የሚቀጥል ይኾናል።
የልማት ኮሚሽኑ፣ በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተቋማትን በመገንባትና የመስኖ ልማት በማስፋፋት ወደፊት በድርቅ ሳቢያ የሚከሠቱ ችግሮችን ለመቋቋም የሚያስችሉ ሥራዎችን በአፋር እና በሰሜን ሸዋ የአፋር አዋሳኝ ወረዳዎች እና በሌሎችም ላይ በሰፊው በማከናወን ላይ ይገኛል።
ሰንደቅ፡- በኮሚሽኑ የማኅበረሰብ ልማት ሥራዎች ውስጥ፣ የሕዝቡ ተሳትፎ ምን ይመስላል?
ብፁዕነታቸው፡- ልማት ኮሚሽኑ ሥራውን እስከ ታች አውርዶ ለመሥራት የሚያስችል የልማት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች በክልል እና በዞን ከተሞች ስላሉት በእነርሱ አማካይነት ሥራውን ማኅበረሰቡን መሠረት አድርጎ ለማከናወን ምቹ ኹኔታ ተፈጥሮለታል። በመኾኑም ኮሚሽኑ በሚንቀሳቀስባቸው የፕሮጀክት ወረዳዎችና ቀበሌዎች ሥራውን ለማስተዋወቅም ኾነ ከሕዝብ ጋራ ለመሥራት ምቹ መንገድ በመኖሩና ኮሚሽኑ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ስላለው የማኅበረሰቡ የልማት ተሳታፊነት በጣም ከፍተኛ ነው። የልማት ሥራዎቻችን በዘለቄታዊነት አገልግሎት እየሰጡ ያሉት፣ የማኅበረሰቡ ተሳትፎ ስለታከለበት ነው፤ ይህም በግልጽ የሚታይ እውነት ነው።
ሰንደቅ፡- የስደተኞችንና ከስደት ተመላሾችን፣ መሠረታዊ ፍላጎት በማሟላትና መልሶ በማቋቋም በኩል በኮሚሽኑ ሥራዎች የተገኙትን ውጤቶች ቢያብራሩልን?
ብፁዕነታቸው፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን፣ ስደተኞችንና ከስደት ተመላሾችን በመቀበልና አስፈላጊውን ርዳታ በማድረግ በሀገሪቱ ቀደምት ታሪክ ያላት ስትኾን ከአምስት ዐሥርት ዓመታት በላይ አገልግሎቱን እየሰጠች ትገኛለች። የሀገሪቱ መንግሥትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለስደተኞችና ከስደት ተመላሾች በተቀናጀ ኹኔታ አገልግሎት መስጠት ሳይጀመሩ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ይህን አገልግሎት በቀዳሚነት መስጠቷን ያሳያል። በነበሩት የድጋፍ ጊዜያትም ለሰው ልጅ ሕይወት አስፈላጊ የኾኑና መሠረታዊ ፍላጎቶችን ያማከለ ድጋፍና ርዳታ መስጠት ተችሏል።
በሒደትም የቤተ ክርስቲያንዋ የማኅበራዊ ረድኤት ክንፍ የኾነው የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን፣ በ1964 ዓ.ም. በሕግ ሲቋቋም፣ የስደተኞችና ተመላሾች ጉዳይ እንደ አንድ የሥራ ዘርፍ በማካተት በርካታ ተግባራትን ለመፈጸም በቅቷል።የስደተኞችና ተመላሾች ጉዳይ መምሪያ፣ በልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሥር በመኾንና የራሱን አስተዳደር በማቋቋም የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዚኽም መሠረት ኮሚሽኑ፥ ከመንግሥት፣ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ከሌሎች ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶችጋ በጋራ በመኾን በዐዲስ አበባና አካባቢዋ ባሉ ከተሞችና በአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫ በሚገኙ 18 የመጠለያ ጣቢያዎች አማካይነት ቁጥራቸው በየጊዜው የሚለያይ ቢኾንም፣ በአኹኑ ሰዓት ከ801 ሺሕ በላይ ለሚኾኑ የተለያዩ ሀገር ስደተኞች ማለትም፦ ከደቡብ ሱዳን፣ ከሶማልያ፣ ከየመን፣ ከኤርትራ፣ ከኮንጎ፣ ከሱዳን፣… ወዘተ ለመጡ ስደተኞች የተለያዩ ድጋፎችን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ኮሚሽኑ ለስደተኞች፥ የመጠለያ፣ የምግብ፣ የአልባሳት፣ የገንዘብ፣ የጤና፣ የማኅበራዊና የሥነ ልቡና ምክር፣ የትምህርትና የሞያ ክህሎት ሥልጠና ድጋፍና የመሳሰሉትን አገልግሎቶችን ይሰጣል። በተጨማሪም ስደተኞች ቤታቸው እንዳሉ ኾነው እንዲሰማቸው ለማድረግ የሚኖሩበት መጠለያና አካባቢው ምቹ እንዲኾን ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል። የአካባቢ ክብካቤ፣ የአካባቢና የግል ንጽሕና እንዲጠበቅ እንዲኹም የመጡበትን ዐዲስ አካባቢ እንዲላመዱ የማስተማርና የማሳወቅ ሥራዎች በሰፊው ይከናወናሉ።
በመኾኑም ስደተኞች በሚሰጣቸው የትምህርትና የሞያ ክህሎት ድጋፍ የበርካታ ሞያዎች ባለቤት ኾነው የተለያዩ የገቢ ምንጮች የሚያስገኙ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ራሳቸውን በማቋቋም ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም ስደተኞችን ከቤተሰብ ጋራ በማገናኘት ከፍተኛ ጥረት የሚያደርግ ሲኾን፣ ለዚህም አስፈላጊውን ድጋፍ ይሰጣል።
በአራቱም የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገኙ ስደተኞች የተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ፤ በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ድጋፍና ክብካቤ፣ በግጭት አፈታት፣ በፆታ ጥቃት ዙሪያ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችንም ይሠራል።
ሰንደቅ፡- ኮሚሽኑ ከቤተ ክርስቲያኒቱ የተለያዩ አካላትና ከመሰል አገራዊና የውጭ ተቋማት ጋራ ያለው ቅንጅትና መተባበር ምን ይመስላል?
ብፁዕነታቸው፡- የልማት ኮሚሽኑ በሚተገብራቸው የልማት ሥራዎችና በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ጥራት ከሌሎች ልቆ እስከ መሸለም የበቃው ከሌሎች የልማት አጋሮች ጋራ ተናቦ፣ ተቀናጅቶና ተባብሮ በመሥራቱ ነው። ዘላቂ ልማትን ማምጣት የሚቻለው ከኹሉም ባለድርሻ አካላት ጋራ ተቀናጅቶና ተባብሮ መሥራት ሲቻል እንደኾነ የታወቀ ነው።
ኮሚሽኑ ይህን መርሖ በዋናነት በመከተል በግልጽነትና በተጠያቂነት በመንቀሳቀስ በአነስተኛ በጀት ታላላቅ የልማት ሥራዎችን በመገንባት እውን እያደረገ ይገኛል። በመኾኑም ኮሚሽኑ የከፈታቸው የልማት የማስተባበሪያ ጽ/ቤቶችም ኾነ የፕሮጀክት ጽ/ቤቶች በሚሠሩባቸው አካባቢዎች፣ ከኹሉም የልማት ባለድርሻ አካላት ጋራ መልካም ግንኙነት ያላቸው ከመኾኑም በተጨማሪ፣ በፕሮጀክት ሥራ መልክአ ምድራቸው አስቸጋሪ በኾኑ ሥፍራዎች ኹሉ የተለያዩ የልማት ተግባራትን በማከናወንና ተጨባጭ ለውጥ በማምጣት የካበተ ልምድ ስላላቸው በየፎረሙም በተምሳሌነት የሚቀርቡ ኾነዋል።
ሰንደቅ፡- የኮሚሽኑ ፕሮጀክቶችና እንቅስቃሴዎች፣ በሀገራዊ ሽፋን ያላቸው ሥርጭት የተመጣጠነ ነው?
ብፁዕነታቸው፡- አዎን! በእኛ በኩል ሙሉ በሙሉ ባይኾን እንኳ ፕሮጀክቶች ያላቸው ሥርጭት በአብዛኛው የተመጣጠነ እንደኾነ እምነታችን ነው። ኮሚሽኑ በአኹኑ ሰዓት በሚያካሒዳቸው 27 የሚኾኑ የልማት ፕሮጀክቶችና በ18 የስደተኞች መቀበያ ካምፕ አማካይነት በኹሉም ክልሎች በሚገኙ የፕሮጀክት ወረዳዎች ላይ እየሠራ ይገኛል።
ይኸውም በጋምቤላ ክልል፥ ጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ፣ ፊኝዶ፣ ተርኪዲ፣ ኩሌ፣ ሆኮቡ፤ በቤሻንጉል ጉሙዝ ክልል፥ በከማሽ፣ በኩርሙክ፣ በሸርቆሌ፣ በባምፓሲ፣ በቶንጎ፤ በአፋር ክልል፥ በአርጎባ ልዩ ዞን፣ ሰሙ ሮቢ፣ ዱለቻ፤ በኦሮሚያ ክልል፥ በጉርሱም፣ በጃርሶ፣ በአርሲ ሮቤ፣ በቄለም ወለጋ፤ በሶማሌ ክልል፥ በጅግጅጋ፣ በሸደር፣ በቀብሪበያህ፣ በአውበሮ፣ በኮቤ፣ በመልካ ጂዳ፣ በሔለወይኒ፣ በቆልማንዩ፤ በአማራ ክልል፥ በሊቦ ከምከም፣ በአንኮበር፣ በጊሼ ራቤል፣ በዳውንት፣ በበርኸት፤ በትግራይ ክልል፥ በክልተ አውላዕሎ፣ በእንደርታ፣ በሽመልባ፣ በአደ አርሹ፣ በእፀጽ፤ በደቡብ ክልል፥ በጉራጌ፣ በሙዑር፣ በቡታጀራ፣ በወልቂጤ፣ በሲዳማ፣ በጌዲዮ፣ በይርጋ ዓለም፣ በአለታ ወንዶ፣ በሃላባ፣ በአርባ ምንጭ በ10 ወረዳዎች የኤች.አይ.ቪና የሥነ ተዋልዶ ጤና ሥራዎች፤ ከዚህ በተጨማሪ ኮሚሽኑ በኹሉም ክልሎች በ150 ወረዳዎች ላይ የኤች.አይ.ቪ እና የሥነ ተዋልዶ ጤና ሥራዎች ያከናውናል።
ሰንደቅ፡- ኮሚሽኑ በተለያዩ ክልሎች ሲያከናውናቸው የቆያቸው የልማት ፕሮጀክቶች እየተዘጉ እንደኾነ ይነገራል፤ ፕሮጀክቶቹ የሚዘጉበት አልያም የሚቋረጡበት ምክንያት ምንድን ነው?
ብፁዕነታቸው፡- ፕሮጀክቶች በተፈጥሮአቸው የጊዜ ገደብ አላቸው፡፡ ይኹንና በኮሚሽኑ የሚቀረፁ ፕሮጀክቶች እስከ ታች የሚዘልቁትን የልማት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶችን፤ የፕሮጀክት ጽ/ቤቶችንና የማኅበረሰብ ማኅበራትን በመጠቀም ኅብረተሰቡን ያሳተፈ የፕሮጀክት አፈጻጸም ሒደት በመከተል ኅብረተሰቡ የተለያዩ ሕግጋትንና ደንቦችን እንዲያወጣ በማገዝ ፕሮጀክቶቹ በዘለቄታነት የሚቀጥሉበትን ኹኔታ እያመቻቸ በራሱ በኅብረተሰቡ እየተመራ የሚከናወኑ የፕሮጀክት ዓይነቶች ናቸው።
ፕሮጀክቶች ዘላቂ በኾነ መልኩ እንዲቀጥሉ የሚከተሉት ዝርዝር ተግባራት ይከናወናሉ። ተጠቃሚው ኅብረተሰብ፥ በፕሮጀክት ጥናት፣ ዕቅድ፣ ክንውን፣ ክትትልና ግምገማ እንዲሳተፉ ይደረጋሉ። በዕቅድ ዝግጅት ወቅት የኅብረተሰቡ ማኅበራዊ ድርጅቶች፣ በየደረጃው የሚገኙ የአካባቢ አመራሮች… ወዘተ በፕሮጀክት ሒደት ውስጥ ያላቸው ድርሻ በግልጽ እንዲቀመጥ ይደረጋል። የፕሮጀክቱን መጀመር የሚያበሥር ዓውደ ጥናት ይዘጋጃል፡፡ ከዚህም ጋራ ተያይዞ የእያንዳንዱ የሥራ ድርሻ በግልጽ ለውይይት ይቀርባል። የፕሮጀክት ተግባራትም እንደተጠናቀቁ የሚመለከተው ባለድርሻ አካል በወቅቱ በሕጋዊ የርክክብ ሰነድ ተረክቦ እንዲያስተዳድራቸው ይደረጋል።
ሰንደቅ፡- አንዳንድ ምግባረ ሠናይ ድርጅቶች፣ የበጎ አድራጎት ማኅበራት ሕግ አላሠራ እንዳላቸው ይጠቅሳሉ፤ በዚኽ ረገድ ኮሚሽኑ የገጠመው ችግር ይኖር ይኾን?
ብፁዕነታቸው፡- ኮሚሽናችን ከ46 ዓመታት በላይ በሥራ ላይ የቆየ ነው። በዕድሜው ሦስት መንግሥታት ተፈራርቀዋል። በእነዚህ ዘመናት ሕጎች ተለዋውጠዋል። ኮሚሽኑ ኹሉንም እንደ አመጣጡ አስተናግዷል። ፈቃድ ሰጪው አካል ቀድሞ በፍትሕ ሚኒስቴር ነበር፡፡ አኹን ራሱን የቻለ ኤጀንሲ ተቋቁሞ የራሱን ሕግ ይዞ እየሠራ ነው።
በእኛ በኩል ቀድሞውንም እንቅስቃሴያችን፥ ተጠቃሚውን መሠረት ያደረገ በመኾኑ የገጠመን የጎላ ችግር የለም። 70 በ30 የሚለውን ሕግ ቀድመን ተግብረነዋል፤ ነገር ግን ይህ 10 በ90(10 ከመቶ በላይ ከውጭ ለጋሾች ገንዘብ መቀበል አይቻልም) የሚለው የውጭ ለጋሽ ድርጅቶች ብዙም አልተቀበሉትም። እርሱ ነው ተጽዕኖ እየፈጠረ ያለው። ሕጉ፥ የሀገሪቱንና የረጂዎችን ኹኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም።
ለእኛ ግን ትልቁ ተጽዕኖ ይህ አይደለም። የእኛ ትልቅ ተጽዕኖ፣ ሕዝባችን ከተረጂነት መላቀቅ አለመቻሉ ነው። የውጭ እጅ ማየት የትም አያደርስም። የጠባቂነት መንፈስ ያሳድራል። ከጠባቂነት መንፈስ ተላቅቀን ባለን ሀብት መጠቀም መጀመር አለብን።
የረጂዎችንም ኹኔታ ስንመለከት፣ ቅድሚያ የሚሰጧቸው ችግሮች በዓለም ዙሪያ እየበዙ መጥተዋል። ሩቅ ሳንሔድ እዚኹ ጎረቤቶቻችን ሱዳንና ሶማልያ በየዕለቱ ሰዎች እየሞቱ፣ እየተሰደዱ ረጂዎች ለእኛ ቅድሚያ ሰጥተው እጃቸውን ሊዘረጉልን አይችሉም። በዚህ ምክንያት ከልመናና ከፈረንጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ መሥራት ይኖርብናል። ዓለም አቀፍ ርዳታ ለተወሰነ ጊዜ ከችግር ለመውጣት ሊጠቅመን ይችላል፤ ለሽግግር ጊዜ ሊረዳን ይችላል፤ በዘላቂነት ግን የሚጠቅመን አይደለም።
ሰንደቅ፡- ለልማትና ለርዳታ የሚውል ሀብት ከሀገር ውስጥ ለማሰባሰብ ዕቅድ አላችኹ?
ብፁዕነታቸው፡- በትክክል፤ ምንም ዓይነት የውጭ ተጽዕኖ የሌለበት ሕግና ደንብ አውጥተናል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ከሌሎች ምሁራን ጋራ በዚኽ ጉዳይ ሕግና ደንብ አዘጋጅተናል። በቀጣይ ለቅዱስ ሲኖዶስ ቀርቦ ውሳኔ ሲያገኝ በሥራ ላይ የሚውል ይኾናል። ይህ ጥናት ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆን ራሳችን እንድንችል የሚረዳን ይኾናል ብለን እናስባለን።
በአኹኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወደ 10ሺሕ ያኽል ሕፃናትን ትከባከባለች። ከሕፃናቱ መካከል አሳዳጊ አልባዎች አሉ። ቤተሰቦቻቸውጋ እንዳሉ የሚረዱ አሉ። ለእነዚኽ የምናገኘው ርዳታ በአኹኑ ሰዓት በግማሽ ቀንሷል። ምን እናድርግ ብለን አይተነዋል። በሐሳብ ደረጃ፥ አንድ ምእመን አንድ ልጅ በፈቃደኝነት ቢይዝ ብለን ብዙ ሕፃናትን መርዳትና መደገፍ እንደሚቻል አይተናል። በአኹኑ ወቅት በጉዲፈቻ ወደ ውጭ የሚሔዱ ሕፃናት ምን አሳዛኝ ኹኔታ እየደረሰባቸው እንደኾነ እናውቃለን። ይህ ችግር እንዲቆም እዚኹ በሀገራችን ልንረዳዳና ልንደጋገፍ ይገባናል።
ሰንደቅ፡- ኮሚሽኑ በአኹኑ ወቅት ከለጋሾች ጋራ ያለውን ግንኙነትና የወደፊት ዕቅዱን ቢጠቁሙን?
ብፁዕነታቸው፡- የልማት ኮሚሽኑ በአኹኑ ወቅት ከለጋሽ ድርጅቶች ጋራ ያለው ግንኙነት በመልካምና በተሻለ ኹኔታ ላይ ይገኛል። ዋናው ጉዳይ፣ ለሚረዱን ድርጅቶች፣ ለመንግሥትና ለተጠቃሚ ማኅበረሰብ ታማኝ ኾኖ በመገኘት የታለመለትን ፕሮጀክት በጥራትና ዘላቂ ጥቅም በሚሰጥ መልኩ በጽናት ማከናወን ነው።
የልማት ኮሚሽኑም ዋነኛ ዓላማ፣ የኅብረተሰቡ ኑሮ ተሻሽሎ ማየትና ለተሻለ ዕድገት ማብቃት በመኾኑ በዚኹ ረገድ ጠንክሮ እየሠራ ይገኛል። ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለበት ኹኔታ የሚንቀሳቀስ በመኾኑ በየጊዜው ከለጋሽ ድርጅቶች አዎንታዊ ምላሽ ሲያገኝ ቆይቷል፤ አኹንም እያገኘ ይገኛል።
በተለይ ኮሚሽኑ፣ የሕፃናት ፖሊሲን ቀርፆና አጽድቆ በሥራ ላይ ማዋሉና የማኅበረሰብ ተጠያቂነት አጋርነት(Humanitarian Accountability Partnership) ማሕቀፍ አዘጋጅቶና አጽድቆ በመተግበሩ ከአጋር ድርጅቶች ጋራ ያለውን ግንኙነት የበለጠ አጠናክሯል።
ኮሚሽኑ በቅርቡ፣ የኹሉንም የፕሮጀክት አጋሮች ተወካዮችን በመጋበዝ ባለን የጋራ አጀንዳና በቀጣይ ስለሚኖረው የሥራ ግንኙነት በተመለከተ ለመወያየት ዕቅድ በመያዝ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ሰንደቅ፡- ኮሚሽኑ በአኹኑ ሰዓት የራሱ የኾነ የገቢ ምንጭ ለማጠናከር ምን እየሠራ ነው?
ብፁዕነታቸው፡- ኮሚሽኑ ከውጪ ከሚያገኘው የርዳታ ድጋፍ በተጨማሪ በገቢ ራሱን ለማጠናከር እንዲቻል ዓላማው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ነው፤ ይልቁንም በአኹኑ ጊዜ በዓለም ዙሪያ በተከሠተው የኢኮኖሚ ቀውስ ምክንያት የውጭ ርዳታ በእጅጉ እየቀነሰ የመጣ ስለኾነ የተለያዩ የገቢ ምንጭ ዕቅዶችን ማዘጋጀትና መሥራት ግዴታ ኾኗል። በዚኹ መሠረት ኮሚሽኑ የገቢ ምንጭ መምሪያ አደራጅቶ ሥራ ጀምሯል።
በቃሊቲ አካባቢ ከሚገኘው የኮሚሽኑ ጋራዥና መጋዘን እንዲኹም የከርሰ ምድር መቆፈሪያ ሪግ ማሽንን ጨምሮ ለዚኹ ተግባር በማዋል የገቢ አቅሙን ለማሳደግ ጥረት እያደረገ ነው።
በተጨማሪም፣ አንድ የሻማ ማምረቻ ፋብሪካና በኹለት ቦታዎች ላይ የታሸገ የንጹሕ የመጠጥ ውኃ የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን ለማቋቋም መሠረታዊ ጥናቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል።
ሰንደቅ፡- ኮሚሽኑ በእንጦጦ አካባቢ የሆስፒታል ግንባታ ዕቅድ እንዳለው ይታወቃል፤ ሒደቱ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ማወቅ ይቻላል?
ብፁዕነታቸው፡- ቤተ ክርስቲያን፣ ከ46 ዓመት በፊት የልማት ኮሚሽኑን ስታቋቁም፥ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ስደተኞችን ለመርዳት፣ አባት እናት የሌላቸውንና ጧሪ ቀባሪ የሌላቸውን ምእመናን ከውጭና ከውስጥ በሚገኝ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ ነው።
ቤተ ክርስቲያን፥ በገዳማት፣ በአድባራትና በገጠር አብያተ ክርስቲያናት አካባቢ ጥቅም ላይ ያልዋለ ብዙ መሬት ስላላት መሬቱን በማልማት ገዳማቱና ኅብረተሰቡ ከልማቱ ውጤት እንዲጠቀሙ ማድረግ፤ እንዲኹም በየአካባቢው የትምህርት ቤትና የጤና አገልግሎቶች እንዲሰጡ ከመንግሥት ጋር በመተባበር መሠረተ ልማት ማካሔድ አንዱ ተግባሯ ነው። ይህን የጤና አገልግሎት ለማስፋፋትና ለማዳበር በቅርቡ በእንጦጦ አካባቢ አንድ ራሱን የቻለ ከፍተኛ ሆስፒታል ተቋቁሞ በዓይነትና በጥራት አገልግሎት እንዲሰጥ ዕቅድ ወጥቷል።
ሆስፒታሉ በዓይነቱም ኾነ በባሕርይው የተለየ ከመኾኑም ባሻገር የግንባታው ወጪ ከ370ሺሕ የአሜሪካን ዶላር በላይ ሲኾን፣ በኢትዮጵያ ብር ሲተመን ደግሞ ከ8 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ተይዞለታል። ሥራው በሚጀምርበት ጊዜም ለ2ሺሕ100 ቋሚና ለ369 ጊዜአዊ በጥቅሉ ለ2ሺሕ469 ሰዎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
ሆስፒታሉ፣ የልዩ ልዩ በሽታዎች መታከሚያና ማገገሚያ ክፍሎችና መሣሪያዎች ይኖሩታል፡፡ የዓለም አቀፍ ድርጅቶችን፣ የዲፕሎማቲክና የኤምባሲ ሠራተኞችንና ከልዩ ልዩ አካባቢዎች የሚመጡ ሕመምተኞችን ለማከም ከ200 በላይ አልጋዎች ይኖሩታል።
ቅድመ ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ ይህ በቀጥታ በኢትዮጵያ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በአሜሪካን ሀገር ከሚገኝ ሌዠንደር ኮርፕ ከተሰኘ ድርጅት ጋራ በአጋርነት የሚቋቋመው ሆስፒታል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና በአገሪቱ ውስጥ የቱሪዝምን አገልግሎት ለማስፋፋት እንደሚረዳ ይታመናል።
የአሜሪካ መንግሥትና በአሜሪካ ውስጥ ያሉ አበዳሪ ድርጅቶች፣ ብድሩንም ኾነ ለብድሩ ዋስትና ለመስጠት ሓላፊ እንደሚኾኑ ቃል ገብተዋል። በኢትዮጵያ በኩል፣ ግንባታውንና ከውጭ የሚገኘውን መዋዕለ ነዋይ እውን ለማድረግ፣ በእንጦጦ አካባቢ ያለውና ለዚኹ ጉዳይ የተከለለው መሬት ለአገልግሎቱ እንዲውል ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ለማግኘት በሒደት ላይ እንገኛለን።¾

ጠቅላይ ቤተ ክህነት: የ100ሺሕ ብር ካሳ ይከፈለኝ በሚል በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ በመሠረተው የፍትሐ ብሔር ክሥ ተረታ

    


ጠቅላይ ቤተ ክህነት: የ100ሺሕ ብር ካሳ ይከፈለኝ በሚል በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ በመሠረተው የፍትሐ ብሔር ክሥ ተረታ

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቂርቆስ ምድብ ኹለተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት፣ በከሣሽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና በተከሣሽ የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ፍሬው አበበ መካከል፣ በስም ማጥፋት ክሥ ጉዳይ የነበረውን የፍትሐ ብሔር ክርክር ሲመለከት ቆይቶ፣ ዛሬ፣ ሚያዝያ 17 ቀን 2009 ዓ.ም. ውሳኔ ሰጠ፡፡
ፍ/ቤቱ የግራና ቀኙን ክርክር በመመርመር፣ በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰ የስም ማጥፋት የለም፤ ስለዚኽም ተከሣሹ አቶ ፍሬው አበበ የሚከፍሉት ካሳ የለም፤ በማለት ተከሣሽን በነጻ አሰናብቶታል፡፡
ለክሡ መነሻ የኾነው፣ በሰንደቅ ጋዜጣ፣ 11ኛ ዓመት ቁጥር 551፣ ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓ.ም፣ «ፓትርያርኩ ለኢትዮጵያ የደኅንነት፣ ለምእመናን የድህነት ስጋት» በሚል ርእስ በዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተጻፈውን ጹሑፍ ጋዜጣው በማተሙ ምክንያት፣ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ፣ ጹሑፉ፥ የፓትርያርኩን መልካም ሰምና ዝና ያጠፋ ነው፤ በማለት ዋና አዘጋጁ የ100 ሺሕ ብር የኅሊና ጉዳት ካሳ እንዲከፍላቸው ክሥ መመሥረታቸው ነው፡፡
ተከሣሽ ለፍ/ቤቱ ካቀረባቸው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚዎች መካከል፣ «የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ ፓትያርኩን ወክሎ የስም ማጥፋት ክሥ ሊመሠረት አይችልም፤ አያገባውም» በሚል ያቀረበውን መቃወሚያ ፍ/ቤቱ ተቀብሎ፣ በክሡ ውስጥ ፓትርያርኩን የሚመለከት ጉዳይ ወጥቶና ክሡ ተሻሽሎ እንዲቀርብ በሰጠው ብይን መሠረት ክሡን አሻሽሎ አቅርቧል፡፡
ዳኛ ዮሲያድ አበጀ የተሠየሙበት ፍ/ቤት፣ በክሡ ላይ ግራና ቀኝ ወገኖችን ሲያከራክር ከቆየ በኋላ ተከሣሽ በጋዜጣው ላይ ያቀረበው ጹሑፍ፣ የስም ማጥፋት ይዘት የለውም፤ በዚኽም ምክንያት የሚከፍለው ካሳ የለም፤ በማለት ውሳኔ ሰጥቶ ጋዜጠኛውን በነጻ አሰናብቷል፡፡
ቀደም ሲል፣ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቂርቆስ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የቀረበለትን የስም ማጥፋት ወንጀል ክሥ ሲመለከት ቆይቶ፣ ጥር 17 ቀን 2009 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ክሥ ውድቅ በማድረግ ጋዜጠኛ ፍሬው አበበን በነጻ እንዳሰናበተ መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡
ዳኛው፣ በንባብ ያሰሙት የችሎቱ ውሳኔ ከ15 ገጾች ባላነሰ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በቀጣይ ዝርዝር ዘገባ የሚቀርብበት ይኾናል፡፡

Wednesday, April 26, 2017

ሃይለማርያም ደሳለኝ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መሃል መጠራጠርና አለመተማመን አንደነበረ አመነ! (ክፍፍሉ አሁንም አንዳለ ግን መቀበል የፈለገ አይመስልም)



 
ምን ቢደግፉት ቢይዙት በባላ
 አንዴ ከዘመመ ቤት የለውም መላ !
በአገራችን ባለፉት ሁለት አመታት የተካሄዱት ህዝባዊ  ትግሎች በገዥው ቡድን ውስጥ መከፋፈልን ፈጥረው አንደነበረና ፣ የመግዛትም አቅሙን በመፈታተናቸው ለስልጣኑ ስሱ የሆነው ኢህአዴግ፣  በአንድ ወገን ሕዝባዊ ትግሉን ለማፈን፣ በሌላ ወገን ደግሞ የትግሉ ስፋትና ጥንካሬ በመሃላቸው የፈጠረውን ሽብረክ ማለት ለመቋቋም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ  የሚታወቅ ነው ።
ለስድስት ወር ተብሎ የታወጀው አዋጅ በቅርቡ ለተጨማሪ አራት ወራት ተራዝሟል ቢባልም፣ ለሕዝባዊ ትግሉ መቀጣጠል ምክንያት የሆኑትን ችግሮች ከስሩ ለማስተካከል ወይንም  ለመቅረፍ አቅሙ፣ ፍላጎቱም ሆነ ቅንነቱ የሌለው ኢህአዴግ፣ አዋጁ ቢነሳ ሕዝባዊ ትግሉ አንደገና ሊያገረሽ ይችላል የሚል ፍራቻ ስላለው በርግጠኝነት አዋጁን በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ  ሊያነሳ ይችላል የሚል ግምት የለም።
ሆኖም በቅርቡ ለአገር ውስጥ ጋዜጦች መግለጫ የሰጠው ሃይለማርያም ደሳለኝ በአገሪቱ ከሞላ ጎደል  ሰላም ሰፍኗል አገር አማን ነው ፣ በተጨማሪ  ደግሞ  አንደ  ሪፖርተር ዘገባ “ኢህአዴግ አንዣበውበት የነበሩ ውስጣዊ  መደናገሮችን በማጥራት ወደ ጤናማነት ” ተሸጋግሯል   ወዘተ  የሚል ፉከራ ቢያስተጋባም፣ በዚሁ መግለጫው በሁሉም አባል ድርጅቶች መሃል፣ ደረጃው የተለያየ መጠራጠር ተፈጥሮ አንደነበር ሊሽሽገው የማይችል በመሆኑ ለማመን ተገዷል። ሃይለማርያም በመሃከላቸው ግልጽ ውይይት በማካሄድ መተማመን ፈጥረናል የሚል  አስተያየት ቢሰነዝርም መሬት ላይ ያለው ውነታ ግን አስተያየቱ ተአማኒነት የሌለው ተራ ፕሮፓጋንዳ መሆኑን ያጋልጣል ።
በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መሃል ያለው አለመተማመንና መወነጃጀል ጠንከር ብሎ የታየው በብአዴን፣ ኦህዴድና ህወሃት መሃል አንደነበረ፣ ለዚህም ዋናው ምክንያት በሁለቱ ክልሎች ተካሂዶ የነበረው፣ በኢህአዴግ የአገዛዝ ዘመን ያልታየ መጠነ ሰፊ  ሕዝባዊ ትግል በድርጅቶቹ ላይ የፈጠረው ጫና  በመሆኑ፣ ለሕዝባዊ ትግሉ መንስኤ የሆኑት ጉዳዮች አጥጋቢ መልስ አስካላገኙ ድረስ በአስተማማኝ ደረጃ በመሃላችን ሰላም ሰፍኗል የሚለው የሀይለማርያም ገላጻ ብዙ አያስኬድም ።
አርግጥ ነው ምንጠራ በሚመስል መልኩ ብአዴን ላይ በተካሄደው ዘመቻ (ገዱ አንዳርጋቸውን ይብላ አይብላ አስካሁን በገሃድ ባይታወቅም) ለህወሃት ማስፈራሪያና አጅ ጥምዘዛ ያጎበደደ የሚመስለው የብአዴን የአመራር ክንፍ፣ “አህት ድርጅቴ ህወሃትን ያላግባብ  ጠርጥሬ ነበር ይቅር በሉኝ” የሚል እንድምታ ያለው ጽሁፍ በመጽሄቱ አውጥቷል መባሉ ቢታወቅም፣የዚህ ቡድን አቋም፣ ልቡ የሽፈተውን የበታችና መሃከል አመራሩን አንዲሁም  አብዛኛው አባላቱን ይወክላል ለማለት አዳጋች ነው። ድርጅቱ ላይ ይሄ ወከባና እጅ ጥምዘዛ ቢካሄድም በክልሉ አሁንም ሰላም እንደሌለና ፣ ትጥቅ አንስቶ እስከመፋለም የደረሰ ተቃውሞ እየጎለበተ እንደሆነ ጭምር ይታወቃል ።
በሌላ በኩል ኦህዴድ የድርጅቱን 27ኛ ዓመት በአል ምክንያት በማድረግ ባደረገው ስብሰባ ላይ፣ የድርጅቱ ሊቀመንበር ለማ መገርሳ የህዝቡን ጥያቄ በቅጡ መመለስ ካልቻልን  እንደ ድርጅት፣እንደ መንግስት እያንዳንዳችን ከገባንበት ጓዳ ውስጥ አንገታችንን ይዞ አውጥቶ የፈለገውን ነገር ሊፈጽምብን እንደሚችል እንዲህ አይነት እርምጃ ሊወስድብን እንሚችል አይተናል፡፡በፊልም ሣይሆን በተጨባጭ ውስጥ ኖረን አይተናል ይሄ ቲያትር አይደለም፡፡ ጎበዝ ሌላ አማራጭ የለንም፣  በሚል ጠንከር ያለ ንግግር  አገራችን በተለይ ደግሞ የኦሮሚያ ክልል  ያለበትን ተጨባጭ ሁኔታ በግልጽ አስቀምጦት ነበር።
በሱ አባባል ህዝብ የሰጠውን የመጨረሻ እድል ተጠቅሞ የህዝብን ጥያቄ ከመመለስ ውጭ አማራጭ እንደሌላቸውም የተገነዘበ መሆኑን ለማስረገጥ” በእውነት ሁሉ ነገር ድኗል ሁሉ ነገር ምላሽ አግኝቷል ሁሉ ነገር አልቆለታል ብለን የምናስብ ከሆነ ሞኝነት ነው” ብሎም ነበር።
በቅርቡ ደግሞ ኦሮሚያ ውስጥ  ስለነበረው፣ ስላለውና ወደፊትም ስለሚኖረው የባለሀብቶች ተሳትፎ አስመልክቶ “በግልባጭ ” መልአክት አንደማይቀበል፣ የ ክልሉ ውስጥዊ ጉዳዮችም  የሚካሄዱትና የሚወሰኑት በሚመለከተው ክፍል ብቻ የሚወሰን መሆኑን ሲናገር፣ የነፍስ አባትነት ሚና የነበራቸውም ከአንግዲህ ስፍራ አንድሌላቸው ሲገልጽ ፣  አንጻራዊ ነጻነትን እያንጸባረቀ እንደሆነና፣ የሃይለማርያም እንደቀድሞው በመሃላችን ሰላም ሰፍኗል፣ በአስተማማኝ ሁኔታ ፓርቲው ወደ ጥንካሬው ተመልሷል …ወዘተ ምኞት አንጂ በመሬት ያለውን ሁኔታ ገላጭ አለመሆኑን የሚያመላክት ነው ።
ከዚህ በተጨማሪ ፣ ለስሙ ለጠ/ሚሩ  ተጠሪ የሆነ፣ በአባይ ፀሃዬ(በግልባጭ ኃይለማርያምን የሚቆጣጠር የወታደራዊና ደህንነት ጁንታው የሲቪል ተጠሪ  ነው የሚሉ አሉ) የሚመራ የጥናት ማእከል ከአመት በላይ አስጠንቼ አቀረብኩት ለሚለው ሪፖርት ሰፊ የህዝብ መገናኛ ሽፋን ተሰጥቶት፣ሃይለማርያም የሚመራው የአስፈጻሚ ኃይል ” ዜጎችን በግላቸውም ሆነ በማህበር ተደራጅተው ወይም ባላቸው ኃላፊነት በሚመለከታቸው ጉዳይ ሲሳተፉና ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ  በዛቻ፣ በማስፈራሪያ፣በጥቃትና  አድሎዓዊነት የሚያይ ፣ ሁሉ ነገር ላይ የበላይ” ካልሆንኩ ብሎ የሚውተረተር ብሎ  አብጠልጠሎታል።
ማአከሉ ከላይ አንዳልኩት ተጠሪነቱ ለጠ/ሚር ነው ቢባልምና፣ ያቀረበውም ሪፖርት ሃይለማሪያም ከሚያቀርበው ትርክት ሙሉ ለሙሉ የሚላተም ቢሆንም፣ በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሃይለማሪያም ሪፖርቱ እኔ ጋ አልደረሰም በሚል የመለሰው መልስ “መተማመን ፈጥረናል “ የሚለው ሃሰት መሆኑን ከበቂ በላይ  የሚያረጋግጥ ነው።
ሁኔታ ካመች  ጋብ ያለው ሕዝባዊ ትግል አገርሽቶ ከቁጥጥር ውጭ ሊሄድ ይችላል  የሚል ፍራቻና፣ በድርጅቶቹ መሃል ያለው አለመግባባትና ጥርጣሬ በቅጡ አለመርገብ ተዳምሮም ነው  ነሐሴ ላይ መካሄድ የነበረበት የኢህአዴግ ስብሰባ አንዲተላለፍ  ያስገደደው ።
ለማጠቃለል  ህዝባዊ አመጽን ፍራቻና ለስልጣን በመሳሳት፣ የሚፎከርበትን ህገ መንግስት አሽቀንጥሮ ጥሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ በኮማንድ ፖስት ስም ስልጣኑን ለወታደራዊና ደህንነት ጁንታ አሳልፎ የሰጠው የሃይለማሪያም መንግስት ከእንግዲህ ውስጣዊ ሰላም የማግኘቱና እንደትላንትናው የህወሃት የበላይነት አጠያያቂ ያልሆነበት ኢህአዴግ የሚኖርበት አጋጣሚ ይመጣል ብሎ ለመናገር የማያስችል ሁኔታ ውስጥ እንገኛለን።

አበጋዝ ወንድሙ

ኃይሌ ገ/ስላሴ ከመጋረጃው ጀርባ የሚሰራውን ምን ያህል ያውቃሉ?

   


ኃይሌ ገ/ስላሴ ከመጋረጃው ጀርባ!!
ኃይሌን በአደባባይ የምናውቀው በእግሮቹ ፍጥነት ነው፡፡ ከአደባባይ በመለስ ከመጋረጃው ጀርባ የሚሰራውን ምን ያህል ያውቃሉ?
ኃይሌ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ጤፍ (The Ethiopian endemic crop) ከወንድሙ ጋር በመሆን እና ከሆላንድ ባለሀብቶች ጋር በመመሳጠር ባለቤትነቱ በሆላንዳዊያን አንዲ መዘገብ አድርጓል፡፡ሀይሌ እና ወንድሙ ከሆላንድ ባለሀብቶች ጋር በፈጠሩት ሽርክና ጤፍን ከኢትዮጵያ ውጭ በማምረት እና በማሰራጨት ሀገሪቱ በዚህ ብርቅየ አዝዕርት ማግኘት የነበረባትን ጥቅም አሳጥቷታል፡፡
ኃይሌ በወቅቱ ስለዚህ ጉዳይ የወያኔውን ሪፖርተር ጋዜጣን ጨምሮ የተለያዩ ሚዲያዎች ጥያቄን ቢያቀርቡለትም መልስ ለመስጠት ፍቃደኛ አልነበረም፡፡ “የኢትዮጵያ የዘረመልህ ባንክ” የሚባለው ተቋም የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች የኃይሌን ተግባር ቢቃወሙም፤ የህወሓት የዘረፋ ሸሪክ በመሆኑ ምንም የተባለው የለም፡፡ እንዲያውም ይህ ጉዳይ በVOA ቀርቧል፡፡
የኢትዮጵያ አንጡራ የተፈጥሮ ፀጋን የዘረፈው እና ያዘረፈው ኃይሌ፤ እንደ መደኃኔት በአለም አቀፍ ደረጃ ከሚሸጠው ጤፍ ላይ ሀብት እያካበተ ነው፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ አንድ ሀገር በብቸኝነት ላላት የተፈጥሮ ፀጋ ልዩ መብት የሚሰጥ የባለቤትነት መብት አለ፡፡ ኃይሌ ኢትዮጵያ ያሳጣት ይህንን ልዩ መብት ነው፡፡ የማምረት እና የመሸጥ ፍቃድ በመስጠት ብቻ ኢትዮጵያ በአመት ሚሊዮን ዶላርሮችን ማግኘት የምትችልበትን መብት ነው ያሳጣት፡፡
ሌላኛው የኃይሌ እና የወያኔ የንግድ ሽርክና “ማራቶን ሞተርስ” ነው፡፡ ይህ የኮሪያን ቅንጡ ተሽከርካሪዎችን የሚያስመጣው ተቋም ዋንኛ ሸማቾች የወያኔ መከላከያ ሚንስቴር መስሪያ ቤት ነው፡፡ ሌሎችም የወያኔ የመንግስታዊ ተቋማት ሸማቾች ናቸው፡፡ኃይሌ በአንድ ወቅት የመኪና ንግድ በወራት በመቶ ሚሊዮኖች የሚታፈስበት ነው ብሏል ለሪፖርተር ጋዜጣ፡፡ በመቶ ሚሊዮኖች የሚታፈሰው ለኢትዮጵያ ህዝብ ሸጦ ሳይሆን ለመንግስታዊ ተቋማት በተመቻቸለት የልዩ ተጠቃሚነት መብት ነው፡፡ በኢትዮጵያ አንደኛ የመኪና ሻማቾች የመንግስት ተቋም ተብየዎች መሆናቸው ግልፅ ነው፡፡
ኃይሌ ከሩጫ የተሸለመው ጥቂት ምሊዮኖች ነው፡፡ ከስፖንሰር የሚያገኘውም ቢሆን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ምክነያቱም ስፖንሰር የሚያደርጉት አለማከፍ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያጓጓ የገብያ ድርሻም የላቸውም፤ ምርታቸውም ለአብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች የሚቀመስ ዋጋ አይደለም፡፡ የኃይሌ ሀብት ግን በቢሊዮኖች የኢትዮጵያ ብር ነው፡፡
ስለዚህ የኃይሌ የሀብት ምንጭ ከወያኔዎች ጋር የሚደረግ የዝርፊያ ሽርክና ነው፡፡
ሌላው የሀይሌ ገራሚ ነገር ለአፍሪካውያን በተለይም ለኢትዮጵያውያን ያለው የተዛባ አመለካከት ነው፡፡ ይህንንም በBBC ላይ ለአፍሪካውያን ዲሞክራሲ አያስፈልግም ብሏል፡፡ ምክነያት እሱ ከጨቋኞች እና ከዘራፊዎች ጋር መሞዳሞድ ስለሚችል ነው፡፡

Tuesday, April 25, 2017

በተለያዩ የአማራ አካባቢወች የመሰሪት ድንጋይ ተቀምጦላቸው የውሀ ሽታ ሁነው የቀሩ 47 ፋብሪካዎችና የልማት እቅዶች

    


ባለፉት አመታት በተለያዩ የአማራ አካባቢወች የመሰሪት ድንጋይ ተቀምጦላቸው የውሀ ሽታ ሁነው የቀሩ 47 ፋብሪካዎችና የልማት እቅዶች ለመጥቀስ ያህል;
1ደብረ ማርቆስ ከተማ – በኤሌክትሪክ የሚሰራ የመኪና ፋብሪካ – በድያስፓራ ነገር ግን ተከልክሏል
2 . ደሴ – ቴሪሽየሪ ሆስፒታል
3. ወልደያ – የጅንስ አልባሳት ፋብሪካ – በሸክ አል አላሙዲ
4 . ባህር ዳር – የዘይት ፋብሪካ – በሸኩ
5. ባህር ዳር – የወረቀትና ፐልፕ ፋብሪካ
6. ኮምቦልቻ – የብረታ ብረት ፋብሪካ – በሼኩ
7. ጨሞጋ የውሀ ሀይል ፕሮጄክት (ከደ/ማርቆስ ከተማ ወጣ ብሎ የሚገኝ) – ግንባታው ከተጀመረ በሃላ የተቋረጠ
8. ሞጣ አካባቢ – የስሚንቶ ፋብሪካ – በሼኩ ቃል የተገባ
9. ፍኖተ ሰላም አካባቢ – የስኳር ፋብሪካ
10.ደብረታቦር – የችቡድና የብርጭቆ ፍብሪካ
11. ሕብር ስኳር ፋብሪካ – አገው ምድር (አዊ)
12. Mineral water factory – Gonda
13. sesame oil factory – Gonda
14. expansion of Gondar Hospital (by the Shekih)
15. Territory Hospital (Gondar, Belesa)..በአዲሱ ለገሰ በተደጋጋሚ ቃል የተገባ
16. Train (Finoteselam -Sudan)
17. Train Gondar-Metema-Sudan
18. Biggest Industry park (Kombolicha-Wollo)
19. Airport (Debariq)…መሬት ተዘጋጅቶለት የነበር አሁን ከፊሉ ለባልሀብት ከፊሉ ለዩኒቨርሰቲ የተሰጠ
20.Biggest still factory (Kombolicha-Wollo)
21. ደጀን የመድሃኒት ፋብሪካ (በሁዋላ ወደ አዲግራት የተሸጋገረ)
22. የርብ ግድብና መስኖ ፕሮጀክት (ደቡብ ጎንደር)
23. መገጭ ግድብና መስኖ ፕሮጀክት (ሰሜን ጎንደር)..መጀመርያ የተመደበዉን በጀት ወያኔ ሰለቀጠዉ
24. የአሳ እርባታና ማቀነባበርያ (ጎርጎራ)
25. የሽንፋ ወንዘ መስኖ ፕሮጀክት (መተማ-ቐራ)
26. የጎጃም ባህል ማዕከል (ደብረማርቆስ)….ቲሸርት ሁሉ ተሰርቶ በመቶሽዎች ተሸጦ ወያኔ ዉስኪ ጠጣበት
27. ጎንደር የወጣቶች ሰፖርት ሴንተር (ጎንደር)…የመሰረት ድንጋይ በ መላኩ ፈንታ (አሁን ወያኔ እሰር ቤት) ከ 6 አመት በፊት ተጣለ
28. ደጀን ስሚንቶ ፋብሪካ (አሁን ለሁለተኛ ግዜ ወያኔ እሰራዋለዉ እያለች ነዉ)
29. ወልደያ እብነ በረድ ፋብሪካ (ሰሜን ወሎ)
30. ጋፋት ብረታ ብረት ፋብሪካ (ደብረታቦር)…አሁን ወያኔ በባህርዛፍ እንጨት ጣዉላ ቤት ቀይሮታል
31. የበለስ መስኖ ፕሮጀክት (ጎጃም)፣..ተጀምሮ የቀረ
32. መና ወንዝ የመስኖ ፕሮጀክት (በለሳና ሰቆጣ)
33. የብርጭቆና መስታዉት ፋብሪካ (ደብረ ማርቆሰ)…በሁዋላ ወደ ትግራይ ተወስዶ በዚህ አመት ስራ የጀመረ
34. የአበርገሌ-ዝቐላ ተከዜ ተፋሰስ መስኖ ፕሮጀክት (ሰሜን ወሎ-ሰቆጣ)
35. ደረጃዉን የጠበቀ አስፓልት መንገድ በሞጣ-ባህርዳር (የዛሬ 15 አመት በሚቀጥለዉ አመት ይሰራል ሲባል የቆየ)
36. ከጋሸና ላሊበላ ደረጃዉን የጠበቀ የአስፓልት መንገድ ((የዛሬ 15 አመት በሚቀጥለዉ አመት ይሰራል ሲባል የቆየ)
37. በደብረብርሀን ከተማ የብርጭቆ ፋብሪካ
38. በጎንደር አዘዞ አዳሪ ት/ቤት ለክልሉ ተማሪዎች (ብአዴን ከህወሃት ጋር ሲያኮርፍ አኛም ቀላሚኖ ይኖረናል እያለ ሚያስፈራራበት)
39. ጎንደር ስታድየም (በደርግ ተጀምሮ በሁዋላ ህወሃት ገንዘቡን ዘርፎ አስቀረዉ)
40. ደረጃዉን የጠበቀ መንገድ ከጎንደር-ላይ አርማጭሆ አድርጎ ወደማህል አርማጭሆ የሚደርስ (አሜሪካ የሚኖሩ የአካባቢዉ ተወላጆቸ ብዙ ሚሊየን ብር አዋተዉ ቢልኩ ወያኔ ተከፋፈለዉ)
41. አሜሪካ የሚኖሩ የጎንደር ተወላጆች ደረጃዉን የጠበቀ ተሪሸሪ ሆስፒታል ለመገንባት መሬት ከወሰዱ በሁዋላ ወያኔ ብሩ በኔ በኩል ዪምጣና እኔ እሰራዋለዉ በማለቱ ሳይጀመር የቀረ
42. አልማ ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች እገነባለዉ ብሎ ከ አማራዉ ማህበረሰብ 1.6 ቢሊየን ብር ከ 6 አመት በፊት ሰብስቦ የት እንዳስገባዉ አይታወቅም
43. ከደባርቅ -በየዳ ደረጃዉን የጠበቀ መንገድ (በየዳ ሚባለዉ አካባቢ አሁንም በፈረስ ብቻ ሚኬድበት ወረዳ ነዉ ጎንደር ዉሰጥ
44. ከደባርቅ – ጠለምት መንገድ (ጠለምት ለመሄድ በትግራይ በኩል ዙረዉ ነዉ…መንገድ ባለመኖሩ)..በየአመቱ ይሰራል ይባላል
45. ግዙፍ የብቅል ፋብሪካ (ጎንደር)…አሁን ዳሽን ቢራ ለራሱ ትንሽየ ፋብሪካ አስተክሎ ገብስ ከፈረንሳይ በማስመጣት የአካባቢዉን ገበሬ ምርት አልቀበል ያለ…ወያኔ ከፍተኛ ኮሚሽን ከፈረንሳዩ ኩባንያ ስለሚያገኝ ብቻ ገብስ ከዉጪ ያስመጣል
46. ጎንደር ኢንደሰትሪ ፓርክ (ጎንደር)
47.ጎንደር የወጣቶች ማዕከል (በመላኩ ፋንታ የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ የነበረ)

ፓትርያርኩ ተሸነፉ? “ሙስናን ተዉ፤ ማለት ከአንበሳ አፍ ሥጋ እንደ መንጠቅ ነው፤ አቅሙም ጉልበቱም የለንም” አሉ



  • ሙስናን ለማስቀረት፣ በቤተ ክርስቲያን ምንም እንዳልተደረገ መናገራቸው አጠያያቂ ነው
  • የአንድነት ዕጦት፣ የአሠራሩ መሥመር አለመያዝና ቸልታ ፕትርክናውን አክብዶባቸዋል
  • ለቤተ ክርስቲያን የሚያስብ እንደሌለ እና ኹሉም በገንዘብ መሸጡንና መለወጡን ጠቅሰዋል
  • ባለጉዳዩ ኹሉ ወደ በላይ አካል መሮጡ፣ የመዋቅሩንና አደረጃጀቱን ውድቀት አመላክቷል
  • መነኵሴ ዘመድ እንደሌለውና “በመንፈሳዊነት” ቢታወሱ ደስ እንደሚያሰኛቸው ጠቁመዋል

ሐራ ዘተዋሕዶ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ከአራት ዓመት በፊት፣ ወደ መንበረ ፕትርክናው በመጡበት በዓለ ሢመት ባሰሙት ቃለ በረከት፥ በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የሚሠራው ሥራ እግዚአብሔር እና ምእመናን በደስታ የሚቀበሉትና የሚወዱት፤ በመንፈሳዊነት የተደገፈ፤ ሓላፊነትን፣ ተጠያቂነትን፣ ብቃትን፣ ንቃትን፣ ጥራትን፣ ታማኝነትን፣ ሐቀኝነትን፣ ፍትሐዊነትን የተጎናጸፈ ፍጹም ጤናማ የኾነና እንከን የሌለበት መኾን እንደሚኖርበት ተናግረዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያን፥ የእውነትና የሐቅ አስተማሪ እንጅ ተማሪ መኾን እንደሌለባት ከጠቆሙ በኋላ፣ “ሐቀኝነት፣ ታማኝነትና መልካም ሥነ ምግባር ከቤተ ክርስቲያን ካልተገኙ ከየት ሊገኙ ይችላሉ?” ሲሉም ጠይቀዋል፡፡
ቅዱስነታቸው፣ በዚያው ዓመት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በርእሰ መንበርነት በመሩት የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ባሰሙት ቃለ ምዕዳን ደግሞ፦ ከቤተ ክርስቲያን ክብርና ቅድስና ጋራ የማይጣጣመውን ሙስና ለማጥፋትና ቤተ ክርስቲያንን ለመታደግ ሥር ነቀል የለውጥ ርምጃ በቆራጥነትና በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲኾን አሳስበዋል፤
“ሥር ሰዶ የሚታየው አሳፋሪና አሳዛኝ ብልሹ አሠራር ሳይታረም ቢቀጥል፣ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ችግር ላይ እንደምትወድቅ በግልጽ እየታየ ነው፤” ያሉት ቅዱስነታቸው፣ ሊወሰዱ ይገባል ያሏቸውን ሦስት መሠረታዊ ርምጃዎች ጠቁመዋል፡፡ እነርሱም፡-
  1. ብልሹ አሠራርን ለማረምና ለማስወገድ፡- የፀረ ሙስና ዐቢይ ኮሚቴ፣
  2. አስተዳደሩን በዐዲስ መልክ ለማዋቀር፡- የአስተዳደር መሻሻል ዐቢይ ኮሚቴ፣
  3. የፋይናንስ አያያዝና አጠቃቀም ሥርዓት፥ ዘመናዊ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው መልኩ ለማደራጀት፡- የገንዘብ አያያዝ ሥርዓት ማሻሻያ ዐቢይ ኮሚቴ
እንዲቋቋምና ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ አንድ ወጥ የኾነ ሥርዓት ለመዘርጋት እንዲቻል ሐሳብ አቅርበዋል፡፡
እጅግ የተንዛዛ ቢሮክራሲ፤ ከቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ተልእኮ ጋራ ያልተቀናጀ የሰው ኃይል ምደባ፤ ዕውቀትና የሥራ ችሎታ ሳይኾን ሙስና፣ ወገንተኝነትና የሥነ ምግባር ብልሽት በስፋት የሚንጸባረቅበት አሠራር፣ በካህናትና በምእመናን ላይ ቅሬታንና እምነት ማጣትን እያስከተለ እንዳለ ገልጸው፣ “በፍጥነት ማስተካከል ካልቻልን፣ በቅድሚያ በእኛ ላይ የሚፈርድ የገዛ ራሳችን ኅሊና ነው፤ በይቀጥላልም እግዚአብሔርም ሌላውም ይፈርድብናል፤” ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
ቅዱስነታቸው አክለውም፣ “በአጭር ጊዜ የተፈለገውን ለውጥ ለማምጣት ቢያዳግት እንኳ፣ የለውጡን መሠረት ግን በአስቸኳይ ማስቀመጥና አቅጣጫውን መቀየስ እጅግ አስፈላጊ መኾኑ ሊሠመርበት ይገባል፤” በማለት ነበር፣ የብፁዓን አባቶችን አጋርነት የተማፀኑት፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስም፣ በዚያው ዓመት (ማለትም በ2005 ዓ.ም.) የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤው፣ የቅዱስነታቸውን ማሳሰቢያ ተቀብሎና በአጀንዳ ቀርጾ ከተወያየ በኋላ ባወጣው መግለጫ ኹለት ዐበይት ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ እነርሱም፡-
  • የመጀመሪያው፥ ብልሹ አስተዳደርና አሠራር፤ ዘመኑን ያልዋጀና ጥራት የጎደለው የፋይናንስ አያያዝ፣ እንደዚኹም ለሙስናና ብክነት የተጋለጡ አሠራሮችን ኹሉ ወሳኝ በኾነ መልኩ ለመቅረፍና ለማድረቅ፤ ከዚኽም ጋራ ቤተ ክርስቲያን በመሪ ዕቅድ መሥራት የምትችልበትን አሠራር ለመቀየስ፥ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምሁራን የተካተቱበት ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጉዳዩን የማጥራትና የማጥናት ሥራ እንዲቀጥል፤
  • ኹለተኛው፡- የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሌሎች አህጉረ ስብከት በመልካም አስተዳደርና በፋይናንስ አያያዝ፣ እንደዚሁም በስብከተ ወንጌልና በአገልግሎት አሰጣጥ ለሌሎች አህጉረ ስብከት በሞዴልነት የሚጠቀስ ሀገረ ስብከት መኾን ስለሚገባው፣ በአንድ ሀገረ ስብከት፣ በአንድ የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀ ጳጳስ እየተመራ እንደዚኹም በመልካም አስተዳደር፣ በፋይናንስ አያያዝና በሰው ኃይል አመዳደብ የሕግ የበላይነትን አክብሮ እንዲሠራ አስፈላጊው ክትትል ኹሉ በቋሚ ሲኖዶስና በመንበረ ፓትርያርኩ እንዲደረግ፤ የሚሉ ከፍተኛ ውሳኔዎች ነበሩ፡፡
በዚኽም መሠረት፣ ዐበይት ኮሚቴዎቹ ተቋቁመው፣ መዋቅራዊ አደረጃጀቱና የአሠራር ሥርዓቱ ዘመኑን በዋጀና ስትራተጅያዊ በኾነ መልኩ ለማሻሻል የሚያስችሉ ወሳኝ ጥናቶች ተዘጋጅተው ከአተገባበር ስልታቸው ጋራ ለምልአተ ጉባኤው ቀርበው ከመጽደቃቸውም በላይ፣ የማስፈጸሚያ በጀትም ተመድቦ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
በተለይ አዲስ አበባን በተመለከተ ቀርቦ የነበረው፥ የመዋቅር፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናት፣ በምልአተ ጉባኤው አቅጣጫ መሠረት፣ በሀገረ ስብከቱ ማኅበረ ካህናትና ማኅበረ ምእመናን ለውይይት በተዘረጋበት ወቅት፣ የብዙኃኑን ጠንካራ ድጋፍ ከማረጋገጡም ባሻገር፣ “የቤተ ክርስቲያንን ትንሣኤ ተስፋ ያየንበት ነው” በሚል በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲኾን በብርቱ ሲጠይቅ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡
ይኹንና፣ ለውጡ ተግባራዊ ሲኾን የሚሰፍነው የግልጽነትና የተጠያቂነት አሠራር፣ ሕገ ወጥ ጥቅማቸውን የሚያስቀርባቸው አማሳኝ የአጥቢያ ሓላፊዎች እና በለውጡ፥ የሐዋርያዊ ተልእኳችን መጠናከር ያስደነገጣቸው መናፍቃንና አድርባይ ፖሊቲከኞች ግንባር ፈጥረው በነዙት ውዥንብር፣ ሒደቱ ለጊዜውም ቢኾን ተስተጓጉሏል፡፡
በእጅጉ አሳዛኝ የነበረውና ለታሪክ ትዝብት የሚቀመጠው ግን፣ የፓትርያርኩ አቋም 180 ዲግሪ መዞሩና አማሳኞቹ በሽፋን የተገለገሉበት መኾኑ ነበር፡፡ የመዋቅር፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ፣ ቅዱስነታቸው ራሳቸው በሰጡት ቀጥተኛ መመሪያ ጭምር እንዳልተዘጋጀ ኹሉ፣ በአማሳኞች ውዥንብር የአፈጻጸም ሒደቱ ሲታጎልና ሲታገት፣ ቅዱስነታቸው ለማስተካከል ያደረጉት በይፋ የሚታወቅ ግፊትና ጥረት አልነበረም፡፡
ከዚያም በኋላ ሌሎች መለስተኛ ጥረቶች የተሞከሩ ቢኾንም፣ የቤተ ክርስቲያናችንን ክብርና ልዕልና ጠብቆ ለማቆየትና የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ችግር ፈቺ ሕግ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ መዋቅራዊ አደረጃጀትና የአሠራር ሥርዓት ለመዘርጋት አልተቻለም፤ የመልካም አስተዳደር ዕጦቱ፣ የሀብት ብክነቱና የፍትሕ መዛባቱ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡
በተለይ፣ “የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት” የኾነው አዲስ አበባ፣ በቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ እንደተመለከተው፣ ለሌሎች አህጉረ ስብከት በሞዴልነት በሚጠቀስበት መልኩ መደራጀቱ ይቅርና ዋና ክፍሎቹ እንኳ የሚያከናውኗቸው ተግባራት በዝርዝር አልተለየላቸውም፤ ዐቅዶ ለመሥራትና ለመገምገም የሚያስችል የአሠራር ሥርዓት የለውም፡፡ እንዲያውም፣ “የቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት” የሚለው ድንጋጌ ግልጽ ባለመኾኑ የበርካታ ውዝግቦች መነሻ ኾኗል፡፡ ይህን በመጠቀምና “ተጠሪነታችን ለፓትርያርኩ ነው” በሚል ከሕግና ሥርዓት ውጭ በመኾን የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን አመራር ያለመቀበል አዝማሚያ ይታያል፡፡
ይባስ ብሎ፣ የሚመለከተውን አካል በማግለል፣ በጎሠኝነትና በጥቅመኝነት ላይ ተመሥርቶ፣ ከሠራተኛ አስተዳደር ደንቡ ውጭ የመቅጠር፣ የማሳደግ፣ የማዛወር፣ የማገድና የማሰናበት አሠራር ተባብሶ የውስጥ ደላሎች ሽሚያና ፉክክር ይታይበት ጀምሯል፡፡ ይህም፣ ከመሠረታዊ ተልእኳችን ጋራ ሳይቀናጅ፣ የእምነት አቋሙና የሥነ ምግባር(ዲስፕሊን) ይዞታው በቅጡ ሳይፈተሽ ወደ መዋቅር የሚገባው የሰው ኃይል ቁጥር ከልክ በላይ እንዲከማች ከማድረጉም ባሻገር፣ ለአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ የፋይናንስ ሥርዓት መናጋት መንሥኤ እየኾነ ነው፡፡

በዚኽ መሰሉ አጠቃላይ ሥርዓታዊ ቀውስ ውስጥ በምንገኝበት በአኹኑ ወቅት፣ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ለሸገር ኤፍኤም102.1 ሬድዮ፣ የጨዋታ እንግዳ ፕሮግራም፣ የሰጡትና ባለፉት ኹለት ተከታታይ ሳምንታት የተላለፈው ቃለ ምልልሳቸው፣ ፀለምተኛነትና ተስፋ መቁረጥ በግልጽ የተንጸባረቀበት እንደኾነ ብዙዎች የተገነዘቡት ኾኗል፤ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን በአስቸኳይ ስለማረምና መልካም አስተዳደርን ስለማስፈን አስፈላጊነት በየመድረኩ ከሚያስተጋቡት አቋም ፍጹም የተለየ፤ የተደረጉ ጥረቶችን እንዳልተደረጉ የሚቆጥርና ድካም የተጫጫነው ድምፅ ኾኖ ተገኝቷል፡፡
መንበሩ ላይ እንደተቀመጡ፣ “ሙስና መጥፋት አለበት” በማለታቸው የተሣቀቁ እንደነበሩና ስለ ሙስና በገሃድ እንዳያነሡባቸው ይሹ እንደነበር ያወሱት ቅዱስነታቸው፣ “አኹን አኹን ለምደውታል” ብለዋል፡፡ የቃሉ መለመድ ግን የተግባር ለውጥ አላመጣም – “ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚያስብ የለም፤ ኹሉም ሰው በገንዘብ ተሽጧል፤ ተለውጧል፤ ጭልጥ ብሎ ሒዷል፤” ያሉት ቅዱስነታቸው፣ ሙስናን ተዉ ማለት ከአንበሳ አፍ ሥጋ የመንጠቅ ያኽል አደገኛ እንደኾነ ተናግረዋል – “ይኼን ተው ማለት፥ ከአንበሳ አፍ ሥጋ እንደ መንጠቅ ነው፡፡ ያ ኾኖ ነው ያለው፡፡ ጨርሶ አይሰማም ሰዉ፤ ጆሮ የለውም፤ ጨርሶ፡፡”
ሌላው አነጋጋሪ የፓትርያርኩ ምላሽ፣ ሙስናን ለማስቀረት በቤተ ክርስቲያን ምንም የተደረገ ነገር የለም፤ ማለታቸው ነው፡፡ ሌላውን ትተን፣ በቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔና በራሳቸው መመሪያ ጭምር፣ ሊቃውንቱና ባለሞያዎቹ በትሩፋት የደከሙባቸው፣ ለትግበራ የቀረቡ ጥናቶች አልቀረቡምን? ካህናትና ምእመናን፥ ሙስናን፣ ብክነትንና ብልሹ አሠራርን በማጋለጣቸው ለእስርና እንግልት፣ ለእግድና ስንብት አልተዳረጉምን? ጠንካራ ሰበካ ጉባኤያትና የሰንበት ት/ቤቶች እንዲዳከሙና እንዲበተኑ አልተደረገምን?
ቤተ ክርስቲያን፥ የእውነትና የሐቅ አስተማሪ እንጅ ተማሪ መኾን እንደሌለባት በመጠቆም፣ “ሐቀኝነት፣ ታማኝነትና መልካም ሥነ ምግባር ከቤተ ክርስቲያን ካልተገኙ ከየት ሊገኙ ይችላሉ?” ማለታቸውን ፈጽሞ የዘነጉ የሚመስሉት ፓትርያርኩ፣ በቃለ ምልልሱ፣ ቤተ ክርስቲያን የመንግሥትን ያኽል እንኳ ጥረት እንዳላደረገች ነው የገለጹልን፡፡ ይብሱኑ፣ “እኛ ደግሞ ይኼን ለማድረግ ኃይሉ የለንም፤ ጉልበቱ የለንም፤” ብለው እጅ መስጠታቸው ሳይበቃ፣ “ጉልበትና ኃይል ያለው ተጠቃሚ የኾነው አካል ነው” በማለት አማሳኙ ኃይል ከቁጥጥር ውጭ የኾነ አቅም መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡
ለፓትርያርኩ ምላሽ መነሻ የኾነው ጥያቄ፣ በዓለም ላይ እየተሸረሸሩ ከመጡ ነገሮች አኳያ ቤተ ክርስቲያን ለመጪው ትውልድ ዝግጅት አድርጋ እንደኾን የሚያነሣ ነው፡፡ ከእንግዲኽ በኋላ ተስፋ በማድረግ እንጅ እስከ አኹን ድረስ፣ ሰፊ የኾነና ጥንቃቄ የተመላበት በቂ ዝግጅት አለ ለማለት እንደማይደፍሩ የተናገሩት ፓትርያርኩ፣ “ወደፊት የሚመጣውን አብረን እናያለን፤” ሲሉ ነው የመለሱት፡፡
ከዕለት ተዕለት የሥራ መርሐ ግብራቸው ጋራ በተያያዘ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፓትርያርኩ የሰጡት ምላሽም ቢኾን፤ ከመዋቅርና አደረጃጀት ችግር አኳያ የሕግና ሥርዓት መዛባቱን፣ የመልካም አስተዳደር ዕጦቱን በሌላ በኩል የሚያሳይ መጽሔት ነው የኾነው፡፡ ከጠዋት እስከ ምሽት ባለጉዳዩን ሲያስተናግዱ እንደሚውሉ የጠቀሱት ፓትርያርኩ፣ ጉዳዮች ወደየሚመለከታቸው መመሪያዎች ከመሔድ ይልቅ ወደ በላይ የመሮጥ መጥፎ ባህልና ልምድ እንዳለ ቢገልጹም፣ ግን የሚሳካላት ነገር የለም ብለዋል፡፡
ሰዉ ይመጣል፤ ተገድግዶ ይውላል፤ በየዲፓርትመንቱ አይሔድም፤ ወደ በላይ ነው የሚሮጠው ሰው ኹሉ፡፡ ግን የሚሳካላት ነገር የለም፡፡ እያንዳንዱ በየቦታው በየዲፓርትመንቱ ቢኾን ኖሮ ጉዳዩ ይፈጸምለት ነበር፡፡ ግን እሺ አይልም፤ ባህሉ ልምዱ ጥሩ አይደለም፤ ወደ በላይ መሮጥ ነው፡፡ እና ሰዉ ተገድግዶ፣ መሽቶብኛልና ልሒድ ማለት አይቻልም፡፡ ተራ አስገብቶ ማነጋገር አለ፤ እና በዚኹ እዘገያለኹ፤ በጣም እዘገያለኹ፡፡ ማታ፣ በጣም አምሽቼ ነው የምገባው፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ለሓላፊነት ደረጃቸው በማይመጥኑ በዝርዘር ጉዳዮች ላይ ሳይቀር እንደሚሰማሩና ውሳኔ እንዲሰጡ የኾነበት በርካታ አጋጣሚዎች ታይተዋል፡፡ ይህም ለሥራ ድርርቦሽ፣ ለሓላፊነት፣ ለተጠያቂነት ክፍተት፣ በሚገባ ላልታሰበበትና ላልተመከረበት ቅጽበታዊ ውሳኔ፣ ለአሠራር ሥርዓት መፋለስ፣ ለሀብት ብክነት፣ ለአገልጋዮች ወቅታዊ ውሳኔ አለማግኘት፣ መንገላታትና መጉላላት ለመሳሰሉት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምክንያት ሊኾን በቅቷል፡፡
በዚኽ ረገድ የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት በቀዳሚነት ተወቃሽ እንደኾነ ጥናቶችና ዘገባዎች ያሳያሉ፡፡ ልዩ ጽ/ቤቱ፣ ለቅዱስ ፓትርያርኩ የአስተዳደር አገልግሎት ድጋፍና ለጽሕፈት ነክ ሥራዎች የታሰበ መዋቅር ቢኾንም፣ ራሱን፣ ከፍተኛ የመዋቅርና ሥልጣን አካል አድርጎ የሚሠራ እንደኾነ ጥናቶችና ዘገባዎች ያሳያሉ፡፡ ይህም፣ ለሕግና ሥርዓት መዛባት፣ ለመልካም አስተዳደር ዕጦትና ለመሳሰሉ ችግሮች ቀዳዳ የከፈተ አሠራር ኾኖ ታይቷል፡፡
በአጠቃላይ የፕትርክናውን ሓላፊነት፣ አስበውትና አልመውት ሳይኾን በእግዚአብሔር ጥሪ እንደተቀበሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ሓላፊነቱ ከባድ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡
በሕልሜም የለ፤ ፍላጎትም የለ፤ ኧረ እንደው እባክዎትን፤ እንደው አስቸጋሪ የኾነ ነገር የኾነው፤ ምን ይደረግ?
ሓላፊነቱን ከባድ ያደረገውም፥ የአሠራራችን መሥመር አለመያዝ፣ የእርስ በርስ አንድነት አለመኖርና የሓላፊዎች ቸልተኝነት እንደኾነ አስረድተዋል፤ በተለይም፣ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃ የሚታየውን የሓላፊዎች ቸልተኝነት ጠቅሰዋል፡፡
ሓላፊነቱማ ከባድ ነው፤ የሚከብደው ደግሞ የራሳችን አንድ አለመኾን አለ፡፡ አንድነትና አኹን ደግሞ ከነጠቅላላ እንዲያው ቸልተኝነትም መጥቷል፡፡ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ያለ ነው፤ ሓላፊዎች ቸልተኛነትም እየመጣ ነው፤ በእውነቱ ቀላል አይደለም፡፡
ቃለ ምልልሱን የተከታተሉ አድማጮች በቅዱስነታቸው ምላሽ ውስጥ ያነሷቸውና መታለፍ አልነበረባቸውም ያሏቸው ሌሎችም በርካታ ነጥቦች፡፡ ሙሉ ቃለ ምልልሱን ከ… እንድትከታተሉ እያስታወስን፣ ከዚኽ ቀደም ከተሰሙት ለየት ባለ መልኩ የቀረቡትን የቃለ ምልልሱን ክፍሎች እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
************************************
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ከሃይማኖት መሪነት በተጨማሪ የታሪክና የቅርስ፤ የባህልና የትውፊት፤ የሥነ ጽሑፍ፣ የዜማ፣ የፍልስፍና ጠባቂ ናት፡፡ ከፍተኛ ሓላፊነት ይመስለኛል፡፡ የሀገራችን መነኰሳት ትልቅ የሀገር ቅርስ የኾኑ ንብረቶችን እስከ ዛሬ ጠብቀው አቆይተውልናል፡፡ ምንም ሳይፈልጉ፤ ምንም ሳያምራቸው፡፡ እነርሱ ጥብቅ አድርገው ባይዙት ኖሮ ዛሬ ምንም አይተርፈንም ነበር፡፡ አኹን ዘመኑ እየተለወጠ ይመስለኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያሉትን ቅርሶች በጥሩ ኹኔታ ለመጠበቅ ተዘጋጅታለች ወይ? ይህ ሓላፊነት ከባድ ነው፣ ብዬ ነው፡፡
ቅዱስነታቸው፡- ከአኹን ቀደም ቅርሶቹ ብዙ ባክነዋል፡፡ ቅርሶቹ ያሉባቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት፣ ቅርሱ ቁም ነገር አይመስላቸውም፡፡ ጥንቃቄ ይጎድለዋል፡፡ እንደገና ደግሞ ደንበኛ የኾነ ሙዝየም ወይም ቤት የለም፡፡ ከፊሉ አይጥ ይበላዋል፡፡ የውኃ ፍሳሽ ያበላሸዋል፡፡ እንዲያ እንዲያ እየኾነ ብዙ ባክኗል፡፡ ቁም ነገር መኾኑ ከማይገባቸው ሰዎች የሚሸጡም አሉ፡፡ በእነኚህ ምክንያቶች ኹሉ ብዙ አልቋል፤ ብዙ ጥፋት ደርሷል፡፡
አኹን፣ አኹን ግን ያ ኹሉ ብዙ የተሻለ ይመስለኛል፡፡ ደኅና ነው አኹን፡፡ መሸጥ፣ መለወጥና ነገሩን ኹሉ ችላ ብሎ ማበላሸት ትንሽ የተሻለ ነው፡፡ ግን እስከ አኹን ድረስ ያልተደረሰባቸው ቦታዎች አሉ፡፡ በመሀል ከተማና በከፍተኛ አካባቢዎች ያሉ፣ ለምሳሌ፡- እንደ አኵስም እንደ ላሊበላ ያሉት ታላላቅ አድባራት አኹን ተጠብቀዋል፤ ነገር ግን ያልተደረሰባቸው ደግሞ በየዋሻው ያሉ ቅርሶች አሉ፡፡ መንገድም የሌላቸው፤ የድሮዎቹ አባቶቻችን ከጠላትም ለመሰወር፣ ከጥፋትም ለመዳን መሰለኝ ዋሻ ቆርቁረው እዚያ ውስጥ ነው የሚያስቀምጡት፡፡ ዋሻ ውስጥ የተቆረቆሩ ገዳማትም አሉ፤ ገና ያልተደረሰባቸው አሉ፤ በአጠቃላይ፣ ጥንቃቄ ተደርጎባቸዋል ለማለት አያስደፍርም እንጅ ከነበረው መቼም ይሻላል ብዬ ነው የምገምተው፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባላት ረዥም ታሪክ፣ ብዙ አስቸጋሪ ኹኔታዎች ውስጥ አልፋለች፡፡ ካለፉት ጋራ ሲነጻጸር ይኸኛው ቀላል ሊመስል ይችላል፡፡ ወጣቶች ለሚጠይቋቸው ጥያቄዎች፤ በዓለም ላይ ኹሉም ነገር እየተሸረሸረ የመጣበት ጊዜ ይመስለኛል፡፡ ግን ቢኾንም ቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታይ አላጣችም፡፡ ጥያቄው፥ ለመጪው ትውልድ ዝግጅት አለ ወይ ነው? በእርስዎ በኩልስ ምን ያስባሉ?
ቅዱስነታቸው፡- በቂ ዝግጅት አለ ለማለት አልደፍርም፡፡ ምክንያቱም፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከ አኹን ድረስ ብዙ ዝግጅት አላደረገችም፡፡ ሀብቷንም፣ ቅርሷንም በስፋትና በጥንቃቄ መሰብሰብ አልቻለችም፡፡ የአቅም ማነስ አለ፡፡ ኹላችንም እንደምናውቀው በድኅነት የኖረ አገር ነው፡፡ እኛም ካህናቱም ከዚያው ከድኃው ማኅበረሰብ ነው የተገኘነው፡፡ ትምህርት፣ ዕውቀት፣ ሰፊ የኾነ አስተሳሰብ የለም፡፡ ለብቻ ተኣምር መሥራት አይቻልም፡፡ ድካም አለ፡፡ ከአኹን በኋላ ተስፋ እናደርጋለን እንጅ፣ እስከ አኹን ድረስ ጥንቃቄ ነበረ ለማለት አያስደፍርም፡፡
እንደ አኹኑ አእምሮ ሰፋ ባለበት ወቅት ቢኾን ብዙ ሀገሮችን መስበክ፣ ማስተማር፣ ተከታይ ማፍራት እንችል ነበር፡፡ ነገር ግን፣ ያ ኹሉ አልተደረገም፡፡ ሌላው ቀርቶ እዚኹ ሀገራችን እንኳ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ብዙ ችግሮች አሉ፡፡
አኹን ደግሞ፣ የማናውቀው ታሪክ መጥቷል፡፡ የማናውቀው ታሪክ ማለት ይኼ ሙስና የተባለው፥ ገንዘብ ዘረፋ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚያስብ የለም፤ ኹሉም ሰው በገንዘብ ተሽጧል፤ ተለውጧል፤ ጭልጥ ብሎ ሒዷል፤ ጭልጥ ብሎ ሒዷል፡፡ የሚያሳዝን ነው፣ ይኼ ራሱ፡፡ ሌላ አደጋ ነው ደግሞ የተደቀነባት ቤተ ክርስቲያኒቱ፡፡ መልካም አስተዳደር የሚባል ነገር የለም፡፡
ሙስና የቤተ ክርስቲያን ቋንቋ ነው፡፡ ማሰነ፥ ጠፋ ነው፡፡ ሙስና፥ ጥፋት ነው፡፡ እኔ እዚህ መንበር ላይ ስቀመጥ፣ በመጀመሪያ፣ ሙስና መጥፋት አለበት፤ እያልኩ አንዳንድ ነገር ስናገር፣ ይኼን ቃል አታንሣብን፤ ይሉኝ ነበር፡፡ ለምን ስል፣ በገሃድ መነገር የለበትም፤ ይሉኛል፡፡ ቋንቋው እኮ የቤተ ክርስቲያን ነው፤ ጥሩ ትርጉም ነው ያለው፤ ገንዘብን መስረቅ፣ ማማሰን፥ ማጥፋት ማለት ነው፡፡ ግሩም የኾነ ትርጉም ነው የተሰጠው በእውነቱ፡፡ ኧረ አታንሣብን ማለት ጀምረው ነበር፤ አኹን አኹን ለምደውታል፡፡
እንዲኽ ዓይነት አደጋ በቤተ ክርስቲያን ላይ መጥቷል፡፡ እግዚአብሔር ያድነን በእውነቱ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ ብቻ ሳይኾን በጠቅላላ በሀገሪቱም ያለ ነገር ነው፤ የኾነው ኾኖ መንግሥት ይኼን ለማስቀረት ይታገላል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ግን ምንም የተደረገ ነገር የለም፡፡ እኛ ደግሞ ይኼን ለማድረግ ኃይሉ የለንም፤ ጉልበቱ የለንም፤ ጉልበትና ኃይል ያለው ተጠቃሚ የኾነው አካል ነው፡፡ ይኼን ተው ማለት፥ ከአንበሳ አፍ ሥጋ እንደ መንጠቅ ነው፡፡ ያ ኾኖ ነው ያለው፡፡ ጨርሶ አይሰማም፤ ሰዉ፤ ጆሮ የለውም፤ ጨርሶ፤ ጨርሶ፡፡ ይኼ አደገኛ የኾነ ጉዳይ ነው፡፡ ወደፊት የሚመጣውን አብረን እናያለን፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ብዙ የወጣትና የጉልምስና ዕድሜዎን በገዳም ነው ያሳለፉት፤ በኢትዮጵያ ወደፊት ይኼ የሚቀጥል ይመስሎታል?
ቅዱስነታቸው፡- ገዳማቱ እየተዳከሙ ናቸው፡፡ ለምን? ድሮ መሬት ነበራቸው፡፡ በመሬት ነው የሚተዳደሩት፡፡ በመሬት ሲተዳደሩ፥ እያሳረሱ፣ እያረሱ መሬታቸው በደርግ ተወረሰ፡፡ መሬት ለአራሹ ተባለ፤ መሬታቸው ተወረሰ፡፡ አኹን ባዶአቸውን ነው የቀሩት፡፡ እና ብዙ ገዳማት ተዳክመዋል፡፡ አንዳንድ ገዳማት ደግሞ ራሳቸውን አትክልት እየተከሉ፣ ተግባረ እድ እያደረጉ የሚኖሩ አሉ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እነርሱ በተዳከሙበት ጊዜ፣ የአብነት ት/ቤቶችም ችግር ይገጥማቸዋል፤…
ቅዱስነታቸው፡- ታድያስ፣ ታድያስ፤ በሀገራችን የአብነት ትምህርት መምህራንና ተማሪዎች በጣም ብዙ ናቸው፡፡ እነርሱን መርዳት አልቻለችም፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ፤ አቅም የላትማ፡፡ ከየት ታመጣለች? እንዴት አድርጎ? እንጅ፣ ትምህርት ቤቱ በሰፊው ነው ያለው እስከ አኹን ድረስ፡፡ የትርጓሜ መጻሕፍት፣ የዜማ፣ የቅኔ፣ የአቋቋም በሰፊው ነው ያለው፡፡ ግን፣ ምግብ የሚመግባቸው የለም፤ እየለመኑ ነው፡፡ ልመና ደግሞ ተሰልችቷል፡፡ አንዳንድ አካባቢዎች ሠለጠን እያሉ፥ አንተ ተማሪ ሠርተኽ አትበላም እንዴ? ማለት ተጀምሯል፡፡ ድሮ ተማሪ ክቡር ነው፤ መንደር እየተካፈለ ነበር የሚማረው፤ ለምሳሌ፥ መአት የቅኔ ተማሪ በአንድ ጉባኤ ቤት ይቀመጣል፤ ከዚህ ወዲህ ላንተ ከዚህ ወዲያ ላንተ እየተባለ መንደሩን ይካፈላል፤ ምእመናን ደግሞ እንደ ራሳቸው ቤተሰብ አድርገው ነው ምግቡን የሚሰጡት፡፡ እንግዲህ ድሮ መምህራንም ደመወዝ የላቸውም፤ ተማሪውም ደመወዝ የለውም፤ መምህራኑ ራሳቸው ያለደመወዝ ነው የተማሩት፤ ሲያስተምሩም እየተለመነላቸው ነው፤
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ያ እንግዲህ ራስን ዝቅ ከማድረግ፣ ወደ መንፈሳዊነትምኮ የሚያስጠጋ መንገድ ነው፣ በችግር ውስጥ ማለፍ፤ እርሱም አንድ ቁም ነገር ይመስለኛል፤
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፣ መናኒ አለ፤ ማስተማሩን የእኔ ብሎ ይዟል፤ መምህራኑ፥ ለምን ደመወዝ አላገኘንም አይሉም፤ በቃ፣ እንደ ተማሪዎቻቸው መንደር ተካፍለው ለምነው ያመጡላቸዋል፤ ይህችን ትንሽ ቁራሽ ካገኙ ይህን እየተመገቡ ነው የሚያስተምሩት፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ቅዱስነትዎ ባሉበት ሓላፊነት፣ ከጠዋት ጀምሮ እስከ ማታ ሥራው ምን ይመስላል? ሰፊ ሓላፊነት ይመስለኛል፤ 35ሺሕ አብያተ ክርስቲያናት፤ 1ሺሕ500 ገዳማት፤ 50 ጳጳሳት፤ 400ሺሕ ቀሳውስት፤ 20ሺሕ ተማሪ ቤቶች አሉ፡፡ የእነኚኽ ኹሉ አባት እርስዎ ነዎት፤ ምን ይመስላል ቀኑ?
ቅዱስነታቸው፡- አይ፣ እንግዲህ፤ ችግሩ ምንድን ነው፤ መሥመር አልያዘም፤ ሥራችን አሠራራችን መሥመር አልያዘም፡፡ ለምሳሌ፡- እነዚኽን ኹሉ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ይዘን በደንብ መሥመር ማስያዝ አልቻልንም፡፡ ገዳማቱም ደግሞ፣ ገዳማዊ ሕይወታቸውን ይዘው ይኖራሉ፡፡ አንዱ ደካማ ነው፤ ሌላው ብርቱ ነው፡፡ የተለያየ ኑሮ ነው ያላቸው፡፡ የሚተዳደሩት በመሬት ነበር፡፡ መሬቱ ሲወሰድ ደግሞ መድከም መጥቷል፡፡
እና ሓላፊነቱ ከባድ ነው፤ ሓላፊነቱማ ከባድ ነው፤ የሚከብደው ደግሞ የራሳችን አንድ አለመኾን አለ፡፡ አንድነትና አኹን ደግሞ ከነጠቅላላ እንዲያው ቸልተኝነትም መጥቷል፡፡ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ያለ ነው፤ ሓላፊዎች ቸልተኛነትም እየመጣ ነው፤ በእውነቱ ቀላል አይደለም፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ጠዋት ስንት ሰዓት ይነሣሉ?
ቅዱስነታቸው፡- እኔ እንግዲኽ አምሽቼ ነው የምተኛው፤ በአራት ሰዓት፣ በአራት ሰዓት ተኩል እንደዚኽ እተኛለኹ፡፡ ለሦስት ሰዓት ያህል እተኛና እነቃለኹ፡፡ ከዚያ በኋላ የራሴን ጉዳይ እሠራለኹ፤ የጸሎቱን፣ የሚነበብ እንዳለ፤ ከዚያ በኋላ በእንቅልፍ ትንሽ አሳልፋለኹ፡፡ ኤክሰራይስ አደርጋለኹ፡፡ ያው ሥራ የምንገባው ጠዋት በሦስት ሰዓት ነው፡፡ አስቸኳይ ነገር ከሌለ በቀር በዚኹ መልክ ነው እንግዲኽ የምንነሣው፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ቀኑን ሙሉ ሲሠሩ ይውላሉ…
ቅዱስነታቸው፡- አዎ
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ከሥራ ስንት ሰዓት ይወጣሉ?
ቅዱስነታቸው፡- ኡ ኡ…(ሣቅ) እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት የምቆይበት ጊዜ አለ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- መኖርያዎም እዚኹ ነው?
ቅዱስነታቸው፡- እዚኹ ነው፤… እና ሰዉ ይመጣል፤ ተገድግዶ ይውላል፤ በየዲፓርትመንቱ አይሔድም፤ ወደ በላይ ነው የሚሮጠው ሰው ኹሉ፡፡ ግን የሚሳካላት ነገር የለም፡፡ እያንዳንዱ በየቦታው በየዲፓርትመንቱ ቢኾን ኖሮ ጉዳዩ ይፈጸምለት ነበር፡፡ ግን እሺ አይልም፤ ባህሉ ልምዱ ጥሩ አይደለም፤ ወደ በላይ መሮጥ ነው፡፡ እና ሰዉ ተገድግዶ፣ መሽቶብኛልና ልሒድ ማለት አይቻልም፡፡ ተራ አስገብቶ ማነጋገር አለ፤ እና በዚኹ እዘገያለኹ፤ በጣም እዘገያለኹ፡፡ ማታ፣ በጣም አምሽቼ ነው የምገባው፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ብቸኛ ነዎት፣ እዚኽ?
ቅዱስነታቸው፡- መነኰሳት አሉ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እንደው ዐረፍ ብላችሁ እስር በርስ የምትጫወቱበት ጊዜ አለ?
ቅዱስነታቸው፡- አይ…
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እርስዎ የሚወዱት ምንድን ነው? መጽሐፍ ማንበብ…
ቅዱስነታቸው፡- ምምም… መጽሐፍ ማንበብ… አኹንማ፣ ሆሆሆ..
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ጊዜ የት ተገኝቶ?
ቅዱስነታቸው፡- አኹንማ የት ተገኝቶ… ወይ ጉድ… አኹንማ ሆሆ.. ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ቆይቶ መሥራቱ አግባብ ነው ብዬ ሳይኾን፣ ሰዉ ዝም ብሎ እዚህ ተገትሮ ውሎ እንዲያው ዝም ብሎ ሒድ ማለቱ ስለሚከብድ ነው እንጅ በአግባቡ መሥራቱ ነው ጠቃሚ የሚኾነው፤ እንግዲህ አልቻልኩም፡፡ ያው ሰዉን ስናስተናግድ እንውላለን፤ እንደዚያ ነው፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ምን ዓይነት መጽሐፍ ማንበብ የሚወዱት? ከሃይማኖት፣ ከጸሎት መጽሐፍ ሌላ፤ ታሪክ ያስደስትዎታል?
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፣ እንዴታ! ታሪክ ያስደስተኛል፤ የታሪክ መጻሕፍት አሉኝ፤ ቅዱሳት መጻሕፍት፣ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ፤ ትርጓሜ መጻሕፍት፣ አንድምታዎቹ፣ እነርሱ፣ እነርሱን አነባለኹ፡፡ ግን ጊዜው ዛሬ ምንም አልቻልኩም፤ ድሮ ነበረ፤ እዚህ ከመግባቴ በፊት ነጻነት ነበረኝ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ የሚወዱት የትኛውን ነው? ኹሉንም ይወዳሉ፤ የሚያስበልጡት ማለቴ ነው፤
ቅዱስነታቸው፡- መቸም ቤተ ክርስቲያናችን የምትመራበት፡- ቀዳሚሃ ለጥበብ ፈሪሃ እግዚአብሔር፤ የጥበብ ኹሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ይላል፡፡ ትልቁ ጥቅሳችን፡፡ ሰው ፈሪሃ እግዚአብሔር ከሌለው ዋጋ የለውም፡፡ እንደው፣ ፈጣሪውን ካላወቀ፣ እግዚአብሔር አለ፤ ካላለ፤ ኃጢአት ብሠራ እግዚአብሔር ይፈርድብኛል፤ ካላለ ልጓም የሌለው ፈረስ ነው፤ ዋጋም የለውም፡፡ እና የጥበብ ኹሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ የሚለው ነው፤ ሌሎችም አሉ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እርስዎ ቅድም ብዙ ሥራ እንደሚበዛ ነግረውኛል፤ የቤተ ክርስቲያኒቷ መሪ ነዎት፤ ግን ሌላ ሊሠሩ፣ ሊያስተምሩ የሚፈልጉት ነገር አለ? ስለ ተፈጥሮ ጉዳይ ያሳስብዎታል፤ የተፈጥሮ ሀብትን በሚመለከት፤ ርግጥ የሰላም ጉዳይ አንዱ ሥራዎት ነው፤…
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፣ በጣም… የተፈጥሮ ማለት ዕፀዋት…
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ዕፀዋት…አዎ፣ እርስዎ በገዳም ስለኖሩ…፤
ቅዱስነታቸው፡- በጣም፤ እንግዲኽ ለሰውም ኾነ ለምድር ጌጧ ደን ነው፡፡ ለምድር የደም ሥሯ ዕፀዋት ናቸው፡፡ ዕፀዋት እንዲከበሩ፣ እንዳይቆረጡ፣ እንዲተከሉ፤ ዕፀዋት ከሌሉ ምድሪቱ እንደሌለች፤ ሰው የደም ሥሩ ከተቆረጠ ሕይወት እንደሌለው፣ ይኼን ይኼን በተቻለኝ አጋጣሚ አስተምራለኹ፤ በየአብያተ ክርስቲያናቱ፤ በየእሑዱ፣ በየወርኃዊ በዓላቱ፣ በየዐበይት በዓላቱ፤ ከዚኽ ሌላ ደግሞ ስለ ሰላም፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ አንድነት፤ አንድነትና ሰላም ከሌለ ሀገር እንደሌለ፤ ይኼን ይኼን ነው የምናስተምረው፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እንግዲኽ፣ በተለያየ ምክንያት የፖሊቲካውም ጉዳይ እየገባ፣ ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንም እንዲሁ የእርስ በርስ መከፋፈል አለ፤ በመላው ዓለምና በሀገር ውስጥ ላሉት ኢትዮጵያውያን በጉዳዩ ላይ ማለት የሚፈልጉት ነገር ካለ? የሚጠይቁት፣ የሚመክሩት ካለ?
ቅዱስነታቸው፡- መቼም፣ ቤተ ክርስቲያን ልታደርግ የምትችለው፣ ማንንም ማንንም ሳትል ሰላምን መስበክ ነው፤ የሚበጀው፣ በውስጥ ያለውንም በውጭ ያለውንም የምታስተምረው፥ ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ አንድነት፣ ስለ ሃይማኖት ጽናት ነው ምንጊዜም ቢኾን በሰፊው ነው የምናስተምረው፡፡ አኹን ደግሞ እንደ ዘመኑ ስለ ልማት ደግሞ እናስተምራለን፤ እንግዲኽ ሚዲያው ብዙ ደጋፊ የለውም እንጅ እኛ የምንለው፣ እኛ የምናስተምረው ትምህርት በሙሉ ቢሰበክ፣ በሚዲያ ቢተላለፍ ይጠቅም ነበር፡፡ ያው ይኼን ያህል አትኩሮት የሚሰጠው የለም፡፡ ስለ ፍቅር፣ ስለ አንድነት፣ ስለ ሀገር ሰላም፣ ተቻችሎና ተረዳድቶ ስለ መኖር፣ በሃይማኖት ጸንቶ ስለ መኖር ስለዚኽ ኹሉ እናስተምራለን፣ የተቻለውን ያህል፡፡ እኔ በሔድኩበት ኹሉ ሥራዬ እርሱ ነው፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ከሀገር ውስጥ ቋንቋዎች በተጨማሪ ሒብሩ፣ እንግሊዝኛ ይናገራሉ፤ ዐረብኛ ይናገራሉ፤ ሌላስ አልጨመሩም? ነው የረሳኹት አለ፣ እዚኽ ውስጥ?
ቅዱስነታቸው፡- አይ፣ የለም፤ ዕብራይስጡ እየተረሳ እየሔደ ነው፤ ዐረብኛ እንኳ ድሮም ብዙ አልነበረም፤ ዕብራይስጥ ትንሽ ትንሽ ዐውቅ ነበር፤ እየተረሳ ሔደ፤
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ቤተሰቦችዎን ያገኛሉ? እርግጥ እናት አባትዎ በሕይወት ላይኖሩ ይችላሉ፤
ቅዱስነታቸው፡- የሉም
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እርስዎ እዚኽ ደረጃ መድረስዎን እናት አባትዎ አላዩም? ጳጳስ በኾኑ ጊዜ አይተዋል?
ቅዱስነታቸው፡- የለም፤ የት ተገናኝተን፤
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- አኹን ዘመዶችዎ ይጠይቅዎታል?
ቅዱስነታቸው፡- አይ፣ አንዳንድ ሰዎች እየመጡ አይተውኝ ይሔዳሉ፤ ርግጥ፣ በከተማም ያሉ ሰዎች አሉ፤ የቅርብ ዘመድ እንኳ ብዙ የለኝም፤ አልፎ አልፎ ከሀገር ቤት ይመጣሉ፤ አይተውኝ ይሔዳሉ፤
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- መነኵሴ ዘመድ የለውም?
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፤ የለውም
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ኹሉ ዘመዱ ነው፤
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፣ ልክ ነው
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- አንድ የመጨረሻ ጥያቄ፤ ወጣቱ ካህሳይ፣ አንድ ቀን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ይኾናል ብሎ አስበው፣ ተመኝተው ያውቁ ነበር? ወይስ ሕልም አይቼሎታለኹ ያለ ሰው ነበር?
ቅዱስነታቸው፡- ኧረ በጭራሽ፤ ኧረ በጭራሽ፤ እኔ ምንም ስለዚኽ የማውቀው ነገር የለም፡፡ ርግጥ ገዳም ውስጥ ቅኔ ቤት ሳለሁ፣ አንድ ሕልም አይቼ ለአስተማሪዬ ነገርኋቸውና ገረማቸው፡፡ ያኔ ተራ መነኵሴ ነኝ፤ ግን የቅኔ ተማሪ ነኝ፤ የዜማም ተማሪ ነኝ፤ ሕልሙ ምንድን ነው፥ የቀድሞው የትግራይ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት የብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ጎርድ ምስል፣ ፀሐይዋ ላይ ቁጭ ብለው ፀሐይዋ ትታየኛለች፡፡ በእጃቸው፣ ና ይሉኛል፡፡ እርሱን፣ ዬኔታ ዕንቈ ባሕርይ ለሚባሉት አስተማርዬ ነገርኋቸው፡፡ ስነግራቸው ተገረሙና፣ እንዴ፣ ይኼ ምንድን ነው? ጳጳስ ትኾናለህ እንዳንል ከየት ወዴት?(ሣቅ)
.. እንደገና ደግሞ አስተማሪዬ፣ ዬኔታ አየለ ዓለሙ፣ እዚያ ጉባኤ ቤት ምን ይሉ ነበር.. እኔ መነኵሴ ነኝ፤ ጉባኤውን በየጠዋቱ በጸሎት የምከፍተው እኔ ነኝ፤ እርሳቸው በሌለኹበት ጊዜ፣ ጳጳሱ የት ሔዱ? ይሉ ነበር፡፡ ይህን እዚያ አካባቢ የነበረ ሰው ኹሉ ያውቀዋል፡፡ ከሹመት በኋላ፣ እዚያ ጉባኤ ተማሪ የነበሩ ኹሉ፥ የዬኔታ ዶ/ር አየለ ዓለሙ ትንቢት ደረሰ፤ ብለዋል፡፡ ይኼ ይኼ ነው እንጅ እኔ ሕልምም፣ ነገርም አልነበረኝ፡፡
የፓትርያርክ ምርጫው እስከተካሔደበት ወቅት ድረስ ኢየሩሳሌም ነው የነበርኩት፡፡ የመጨረሻው ስብሰባ እንደ ዛሬ ኾኖ በሳምንቱ ደግሞ ፓትርያርክ እንዲሾም ተወስኖ ተጠራኹና መጣኹ፡፡ በጭራሽ በሕልሜም ያልነበረ እኮ ነው፡፡ በሲኖዶሱ ተጠራኹና፣ ውድድሩ ውስጥ አስገብተነሃል፤ አሉኝ፡፡ ኧረ ብዙ ፈላጊ አለ፤ እባካችሁ ለምን እኔን? እኔ አልችለውም ይህን ጉዳይ፤ እኔ ጵጵስናም ስሾም አልፈለግኹም፤ ቅድም እንደተነጋገርነው፣ ወደ ግሪክ ሔጄ ትምህርት መቀጸል ነው እንጅ የማስበው የነበረው እንጅ መኾን አልፈለግኹም፤ አኹንም የፓትርያርክነት ጉዳይ ተመሳሳይ ነው፡፡ አንደኛ፡- ጉዳዩ በሕልሜ የለም፤ ኹለተኛ፡- ብዙ ፈላጊዎች አሉ አይደለም ወይ፤ እነርሱን አታወዳድሩም እንዴ? ብል፣ አይ አስገብተነሃል አሉ፤ እና ደግሞ የእግዚአብሔር ጥሪ ኾኖ መሰለኝ እኔ አለፍኩ፤ ከአምስት ተወዳዳሪዎች እኔ አለፍኩኝ፤ ከ806 መራጮች 500 ድምፅ አግኝቼ እንጅ በሕልሜም የለ፤ ፍላጎትም የለ፤ ኧረ እንደው እባክዎትን፤ እንደው አስቸጋሪ የኾነ ነገር የኾነው፤ ምን ይደረግ?
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ሓላፊነቱን ተሸክመዋል አኹን እንግዲኽ፤
ቅዱስነታቸው፡- ኡ ኡ ኡ… ቀላል አይደለም፤ ቀላል አይደለም፤
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ብርታቱንም ይስጥዎት፤ ትክክለኛውን መንገድ ያሳይዎት፤
ቅዱስነታቸው፡- አሜን፤ አሜን
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- በጣም ነው የማመሰግነው፤ ቅዱስነትዎ፣ መዝሙር ያዳምጣሉ?
ቅዱስነታቸው፡- መዝሙር፣ አዎ፤ ብዙ ጊዜ ከሚያጥረኝ በቀር፤ እንዲያውም ብዙ ትርጓሜ መጻሕፍትና ዜማ የያዘ አይፓድ ነበረኝ፤ አኹን ተበላሸብኝ፤ አንዳንድ ጊዜ እርሱን አዳምጥ ነበር፤ ወሬ(ዜና) አዳምጣለኹ፤ እርሱ አያመልጠኝም፡፡ ሬድዩ ግን ከነጭራሹ የለኝም፤ የእናንተን ሬድዮ እንዴት እንደማዳምጥ አላውቅም፤(ሣቅ) እንዲያውም ጎንደር ሳለሁ ሬድዮ አዳምጥ ነበር፡፡ እዚኽ ግን ዜናውን ብቻ በቴሌቭዥን እመለከታለኹ፤ ከዚያ በኋላ ወደ ሥራዬ ነው፤ በቃ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ፖፕ ፍራንሲስን አግኝተዋቸው ያውቃሉ፤ ከሌሎችም ጋራ እንደዚኹ፤
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፣ እርሳቸው አንዱ ናቸው፤ የግብጹ ፓትርያርክንም ጎብኝቻለኹ፤ እርሳቸውም እዚኽ መጥተው ጎብኝተዋል፤ የሕንድ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክንም ባለፈው ሔጄ ጎብኝቻለኹ፤ ሊባኖስ ያሉት የአርመን ፓትርያርክንም እዚያው ሔጄ ተገናኝተናል፤ የሶርያውን፥ ችግር ስለነበር በሀገሩ፣ አንዱ ዐርፈው ሌላው ሲሾሙ መሔድ ሲገባኝ አልሔድኩም፤ ኢየሩሳሌም ደግሞ ብዙ ፓትርያርኮች አሉ፤ የግሪክ ኦርቶዶክስ፣ የላቲን(ማለትም የካቶሊክ)፣ የአርመን ፓትርያርኮች አሉ፤ አብረን ኖረናል፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፥ በምን ቢታወሱ ይሻልዎታል? ስናስታውስዎት?
ቅዱስነታቸው፡- በምን ቢታወሱ!? ኧሃ.. በቃ፣ በመንፈሳዊነት፤ ሌላ ምን አለኝ፡፡
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- በዚያ ቢታወሱ ደስ ይልዎታል፤
ቅዱስነታቸው፡- አዎ፤
ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1፡- እግዚአብሔር ይስጥልኝ፤
ቅዱስነታቸው፡- እግዚአብሔር ይስጥልኝ፤ እናንተም ስለመጣችኹ አመሰግናለኹ፡፡

ሰበር ዜና – ሕወሓት ለሁለተኛ ጊዜ ለሁለት ተከፍሏል – ጉዳያችን



አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ፣ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ እና የኢትዮጵያ ጥንታዊ አርበኞች ሊቀ መንበር ለአስታራቂነት ተጠርተዋል።የክፍፍሉ አሰላለፍ ተለይቷል።

የህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ በውስጡ ያለው ቅራኔ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን እና አስታራቂዎችን እስከመማፀን እንደደረሰ አስተማማኝ መረጃ እንደደረሰው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ሚያዝያ 16፣2009 ዓም ፣ምሽት ባስተላለፈው የአጭር ሞገድ ራድዮ ፕሮግራሙ ላይ ገልጧል።ክፍፍሉ ኢትዮጵያን በመጠኑ በተሰጠ መብት እንግዛ ወይንስ በአዋጁ መሰረት ማሰርና በመግደል እንቀጥል? በሚል ልዩነት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
በሌላ በኩል የክፍፍሉ መነሻ በአስተዳደር ጉዳይ ላይ ብቻ ሳይሆን ከሀገሪቱ በተዘረፈ ጉዳይ ዙርያ የሁሉም እጅ ከመኖሩ አንፃር አንዱ ከአንዱ የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት እና በእዚሁም ሳብያ አንድኛው ቡድን ሌላውን ለማሰር ከማሰብ የተነሳ እንደሚሆን ሲነገር ሰንብቷል።
ኢሳት በራድዮ ፕሮግራሙ ላይ እንደገለፀው ክፍፍሉን ተከትሎ በሕወሓት በእራሱ በተመረጡ የገለልተኛ ቡድን ደረግ የነበረው ሽምግልና ፍሬ ባለማስገኘቱ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ፣ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ፣ የኢትዮጵያ ጥናታዊ አርበኞች ሊቀ መንበር ልጅ ዳንኤል ጁቴ እና ነጋዴዎችን ያካተተ መሆኑ ተሰምቷል።
የክፍፍሉ አሰላለፍ
1ኛ/ በጀነራል ሳሞራ የኑስ የሚመራው ስር የሚገኙ : –
  – በወታደራዊ መረጃ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ገብሬ ዲላ ፣
 – የሜቴከ (ብረታብረት ኢንጂነሪንግ) ኃላፊ,
– የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አባይ ወልዱ እና
– የአቶ መለስ ባለበት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ሲገኙበት
2ኛ/ በአቦይ ስብሐት የሚመራው ቡድን ስር የሚገኙ : –
 – አቶ አባይ ፀሐዬ እና
 – የደህንነት ኃላፊው አቶ ጌታቸው አሰፋ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
3ኛ/ ዶ/ር ደብረ ፅዮን እና ዶ/ር አርከበ እስካሁን ከየትኛው ቡድን እንደተሰለፉ አልታወቅም።
የኢትዮጵያ አምላክ ይፈርዳል ሳይውል ሳያድር
በድምፃዊ ኃይልዬ ታደሰ

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የ2017 የዓለም የፕሬስ ነፃነት ጀግና ሆኖ ተመረጠ (ዋዜማ)



ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የ2017 የዓለም የፕሬስ ነፃነት ጀግና ሆኖ ተመረጠ
ዋዜማ ራዲዮ- ዛሬ ሚያዚያ 17 ቀን 2009 ዓ.ም አለም አቀፍ ፕሬስ ኢንስቲትዩት ከቪየና በወጣው መግለጫ መሰረት እስክንድር ነጋ የግል ህይወታቸውን መስዋዕት በማድረግ ለንግግር ነፃነት የጎላ አሰተዋፅዎ ያበረከቱ ጋዜጠኞችን ለማክበር እና ለማወደሰ በየአመቱ የሚሰጠውን የዓለም የፕሬስ ነፃነት ጀግና ሽልማት እንዲሰጠው ተወስኗል። የሸልማቱ ሰነስርዓት በግንቦት 10 ቀን 2009ዓ.ም በጀርመን አገር ሃምቡርግ ከተማ ይከናወናል።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ተደላድሎ የጋዜጠኝነት ስራውን ከሰራባቸው አመታት ይልቅ የታሰረባቸው አመታቶች ይልቃሉ፡፡መንግስት ብቻውን ማሰር አልበቃ፣ አላጠግብ ሲልው ከነመላው ቤተሰቡ አስሮታል በ1997ዓ.ም።
እስክንድር ነጋ ብቸኛ ልጁንም ወልዶ ለመሳም እንድ ማንኛውም ዜጋ የታደለ አልነበረም፡፡ በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማርሚያ ቤት ከማዶ በተለምዶ “የእምጫት” ቤት ተብሎ በሚጠራው የሴት እስረኞች ክልል ባለቤቱ ሰታምጥጥ እስክንድር ቀበቶውን ፈቶ አብሯት አላማጠም። ለብቻዋ እስር ቤት ውስጥ አምጣ እንድትወልድ የተገደደችው ባለቤቱ ጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል በሰላም መገላገልን በወሬ ወሬ በሶሰተኛ ወገን ስማ እንጂ።
ልጁንም ክርስትና ለማስነሳት የሚያሰችል ወግ እና ማዕረግም አልደረሰው፡፡ ተወልዶ በአይኑ ያላየውን በእጁ ለማቀፍ የጓጓውን ልጁን ናፍቆት ብሎ የስየመውም ለዚሁ ነበር፡፡ ኢትዮጲያ ውስጥ በጋዜጠኝነት ሙያ እና ለንግግር ነፃነት መከበር ለሚደርስ በደል፣ ግፍ፣ መከራና ኢፍታዊነት የመጨረሻውን ፅዋ በትዕግስት በትህትና እንዲሁም በልዕልና ዜጎች የሚከፍሉትን የህይወት ዘመን ዋጋ እንድ ማሳያ ከሚሆኑ በርካታ ጋዜጠኞች መካከል አንዱና ዋንኛው ነው እስክንድር ነጋ፡፡
መስከረም ሶስት ቀን 2004 ዓ.ም ልጁን ናፈቆት ከትምህርት ቤት ወደ ቤት እያመጣ ሳለ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ፖሊሶች ከልጁ ፊት ተይዞ ለእስር የተዳረገው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከታሰረ 2 ሺህ 35 ቀናቶች ተቆጥረዋል፡፡ የህግ ጠበቃ፣ የሃይማኖት አባት፣ ቤተስብ እንዲሁም ወዳጅ ዘመድ መንገደኛ እንዳይጠይቀው እገዳም ተጥሎበታል፡፡
በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እስኪርቢቶ፣ ወረቀት እና መፀሃፍ በጭራሽ እንዳይዝ የተከለከለው ጋዜጠኛ እስክንድር፣ ቃሊቲ አብረውት የከረሙ ሁሉ ስለመልካም ትህትናው፣ ለሰላማዊ ትግል ሰላለው ቆራጥነት እንዲሁም ከፍተኛ የፍትህ ጥማት በአንድ ቃል የሚመሰክሩ ቢሆንም መንግስት ግን እስክንድርን በሽብር ክስ ከመክሰስ ወደ ኃላ አላስቀረውም።
ጦማሪ እና ጋዜጠኛው እስክንድር ነጋ የሽብር ቡድን ተበሎ በፓላማ ከተሰየመው የግንቦት ሰባት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በህቡዕ ግንኙነት በማደርግ፣ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር በማሰብ እና ቀሰቃሽ ፁሁፎቹን በመፃፍና በማሰራጨት የሚል ክስ በመንግስት ይመስረትበት እንጂ ወደ እስር ቤት እንዲገባ ዋንኛ መነሾ የሆነው የፀረ ሸብር አዋጁን መንግስት የተለየ ድምፆችን ለማፈን እንድሚጠቀምበት እስክንድር በተደጋጋሚ በመተቸቱ ነበር።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የቀደሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የፀረ ሸብር አዋጁን አላግባብ በመጠቀም ጋዜጠኞችን እና ተቃዋሚዎችን ድምፅ ለማፈን እየተጠቀሙበት ሰለመሆኑ፤ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ርዕዮት አለሙ እንዲሁም የኢትዮጲያ መንግስት ያሰራቸው ሁለቱ የስዊዲን ጋዜጠኞች ማርቲን ሽብዬ እና ጆሃን ፐርሰን የፀረ ሽብር አዋጁ ተገን በማደረግ መንግስት የንግግር ነፃነታቸውን ተጠቅመው በመፃፋቸው ለእስር እንደዳረጋቸው በተደጋጋሚ ተችትና አሰተያየት መሰነዘሩን ተከትሎ እርሱም ለእስር ተዳርጓል።
የጋዜጠኞቹን መታሰር አሰመልክቶ እስክንድር በጊዜው ለአለም አቀፍ ፕሬስ ኢንስቲትዩት “የጋዜጠኞቹ መታሰር የፍራቻን ዘር ለመዝራት በስሌት የተደረገ እስራት ነው፡፡ አምባገነኖች የሚተማመኑበት መቋሚያቸው በህዝባቸው ውስጥ ፍርሃትን መንዛት ነው” ብሎ ነበር።
ጋዜጠኛ ውበሸት ታዬ በከፍተኛው ፍርድ ቤት የ14 ዓመት እስራት ሲፈረድበት፣ ሁለቱ የሲውዲን ጋዜጠኞች ማርቲን ሽብዬ እና ጆሃን ፐርሰን ድግሞ አስራ አንድ አመት ተፈረዶባቸው ነበር፤ እስክንድር ነጋ ከሁሉም ከፍተኛ የሆነውን የአስራ ስምንት አመት ፍርድ ተሸክሟል።
የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት እስክንድር ላይ በ 2004 ዓ.ም የአስራ ስምንት ዓመት ፅኑ እስራት እና የአምስት አመታት ህዝባዊ መብቶች እግድ ቢጥለበትም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘፈቀደ እሰራቶችን የሚመለከተው ክፍል የጋዜጠኛ እስክንድር እሰራት ዓለም አቀፍ ህግጋቶችን የሚፃረር እንድሆነ በመገለፅ እስራቱን ኮንኗል
የፍርድ ቤቱ አሰራር ከፍትህ የአሰራር ስርዓት ውጪ በአሰፈፃሚው ኢህአዴግ እንድሚዘወር ለማንም ሰው ግልፅ ቢሆንም ሁለቱ የሲውዲን ጋዜጠኞች ማርቲን ሽብዬ እና ጆሃን ፐርሰን በይቅርታ እንዲፈቱ ገዢው መንግስት ሲፈቅድ ጋዜጠኛ ውበሸት ታዬ እና እስክንድር ነጋ ግን በዝዋይ እና በቃሊቲ እስር ቤቶች መንግስትን  በፅኑ በመተቸታቸው ብቻ አመታትን ይቆጥራሉ።
“አምባገነኖች ፊት ለንግግር እና ለሃሳብ ነፃነት ሲል ያለፍርሃት በእውነት በመቆሙ እና ለዓላማው ፅናት ፣ የኢትዮጲያ መንግስት የፀረ ሽብር አዋጁን ተቃዋሚዎችን እና የተለየ አተያይ ያላቸውን ወገኖች ለማፈን እየተጠቀመበት ስለመሆኑ በድፍረት በመናገሩ ለዚህም ላሳየው ትጋት ተሸልሟል፡፡” ብለዋል በመገለጫቸው የአለም አቀፍ ፕሬስ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ባርባራ ትሪዊኒፊ።
ሽልማቱ የእስክንድር ነጋ ጀግንነትን ለማሰብ፣ መንግስት በተደጋጋሚ የሚያደርስበትን ጫናና ጭቆና እንዲያቆም ለመጠየቅ እንዲሁም መንግስት እስክንድር ነጋን እና ሌሎች እንደ እርሱ ሃሳባቸውን በነፃነት በመግለፃቸው ብቻ የታሰሩ ጋዜጠኞችን እንዲፈታ ለማሳሰብ እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ኢትዮጲያ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር የገባችውን ቃልኪዳን እንድታከብር ጥሪ እንዲያቀርብ ለማስታወስ ያለመ ነው።
የእስክንድር ነጋ ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርክዓለም ፋሲል በበኩሏ እስክንድር የተሸለመውን ሽልማት አሰምልክታ በመግለጫው “ለመናገር ነፃነት የከፈለው ከፍተኛ ዋጋ በአለም አቀፍ መደረኮች ትኩረት ሰላገኘ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል። የሚከፈለው መሰዋዕትነት እንደሁ በከንቱ አልቀረም። “
“እርሱ በእስር ቤት የሚከፍለው ዋጋ እና መሰዋዕትነት ምንም እንኳን ለእኔ እጅግ አሰቸጋሪ ቢሆንም ሌሎችን ስለሚያበረታ እና ተከታዬችንም ሰለሚያፈራ ያሰደሰተኛል። ይህም ሽልማት የእርሱን ነፃነት የሚያፋጥን እና ለረጅም እስሩ መቋጫ እንድሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።”ብላለች።
ለንግግር ነፃነት መከበር ዝብ ለቆሙ  በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚሰጡ ከፍተኛ ሽልማቶችን ሁሉ በየዓመቱ የሚሸለመው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ መንግስት ለስምንተኛ ጊዜ ሲያሰረው በተቃራኒው በ2004ዓ.ም ፔን አሜሪካ ከተባለ አለማቀፍ ድርጅት በአደገኛ የመገናኛ ብዙሐሓን ድባብ ውስጥ ሆኖ በመፃፍ ላደረገው አስተዋፅዎ “የመፃፍ ነፃነት ሽልማትን” ስጥቶታል
በድጋሚ በዚሁ 2004 ዓ.ም አለማቀፉ የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እስክንድር ነጋ የህሊና እስረኛ ስለመሆኑ አውጇል፡፡
በታህሳስ 2005ዓ.ም ደግሞ የሂውማን ራይትስ ዎች የነፃ ንግግር ሽልማት አሸናፊ ነውበ36ተኛው አለማቀፍ የፀሃፊዎች ፌስቲቫል ላይም እስክንድር ነጋ የፔን ካናዳ “የአንድ ስብዓዊነት ሽልማት” አሸናፊ ነው
አለም አቀፍ ጋዜጦች እና ዜና አታሚዎች ማህበር በበኩሉ  በጥር ወር 2006 ዓ.ም የጎለደን ፔን ፍሪደም ሽልማትን ለእስክንድር ሸልሟል።
የአርባ ስምንት አመት ጎልማሳው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በመሰከረም ወር 2004 ሲታሰር አብሮት የታሰረው እና በጋራ ክስ የተመሰረተባቸው የቀደሞ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አንዱዓለም አራጌም የእድሜ ልክ እስራቱን በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እየገፋ ይገኛል

በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት ጥረት ተጀመረ




በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት የሃገር ሽማግሌዎች እንቅስቃሴ ጀመሩ።
በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅና በአትሌት ሃይሌ ገ/ስላሴ የተጀመረው ይህ ጥረት የአርበኞች ማህበር ሊቀመንበር/ ልጅ ዳንዔል ጆቴንም እንዳካተተ መረዳት ተችሏል።
በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) አመራር ውስት ረጅም ጊዜያት የዘለቀና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ገያድ እየወጣ የሚመጣውን ልዩነት ለመሰምገል ከራሱ ከህወሃት የተውጣቱ ገለልተኛ ቡድኖች ያደረጉት ጥረት አልተሳካም። ሆኖም ችግሩ ከህወሃት አጥር ወጥቶ በአደባባይ ምልክት እያሳየ መገኘቱን ተከትሎ እና ፕ/ር ኤፍሬም የሽምግልና ጥረቱን ጀምረዋል። ይህም ጥረት ከቀድሞዎቹ የሽማግሌ ቡድን አባላት ከ እነ አትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ በተጨማሪ የአርበኞቹ ማህበር ሊቀመንበር የሆኑትን ልጅ ዳንዔል ጆቴን እንዲሁም ነጋዲውዎችን እንደጨመረ መረዳት ተችሏል።
በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክልልፍ በተመለከተ ያለው የሃይል አሰላለፍ አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንደኛው ወገን በጄኔራል ሳሞራ የኑስ የሚመራ ሲሆን፣ የወታደራዊ መረጃ ሃላፊው ሜ/ጀኔራል ዲላን ጨምሮ እንዲሁም የሜቴክ ስራ አስኪያጅ ሜ/ጄኔራል ክንፈ ዳኘው የዚህ ቡድን ዋና ተዋናዮች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ወታደሩ በዚሁ ቡድን ስር እንደሆነ ተመልክቷል።
ከፖለቲከኞቹ ውስጥ የዚህ ቡድን አባላትና ተዋናዮቹ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት አቶ አባይ ወልዱ እንዲሁም የቀድሞው ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ባለበት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ተጠቃሽ ሆነዋል።
በሌላ ወገን ተሰልፈዋል በሚል በመረጃ ምንጮች የሚጠቀሱት በአቶ ስብሃት ነጋ የሚመራ ሲሆን፣ አቶ አባይ ጸሃዬ ተጠቃሽ ሆነዋል የደህንነት ዋና ሃላፊው አቶ ጌታቸው ከዚሁ ቡድን ጋር በመሆን ለቡድኑ የጥበቃና የመረጃ ሽፋን እንደሚሰጠው ተመልክቷል። ዶ/ር ጸብረፅዮን ገ/ሚካዔል አርከበ ዕቁባይ አሰላለፋቸው እስካሁን በውል እንዳልለየ ተመልክቷል።

Monday, April 24, 2017

የፈንጅ ጥቃት በጎንደር ዛሬ ደርሷል – አስናቀው አበበ



ቁጥር 11 የፈንጅ ጥቃት በጎንደር ዛሬ ደርሷል።
ቀበሌ 03 ፊት ሚካኤል አካባቢ በሎጅ ፋሲል አቅራቢያ ነው ፍንዳታ እንደደረሰ መረጃ ያለን።
አካባቢው በፍጥነት በወታደር ተጥለቅልቋል። ወሬው እንዳይሰማ እየጣሩ ነው። ሰው በሰፈሩ እንዳይንቀሳቀስ ታግዷል። በማሰርም ላይ ናቸው። ወያኔ የከተሞች ቀን ብሎ ጎንደር ውስጥ ለማክበር ማሰቡ ህዝቡን እንዳስቆጣ በተከታታይ ስንዘግብ ቆይተናል።
የህዝብ ጥያቄ በአፈና አይመለስም!
ህዝብ ያሸንፋል©!

ግብፅ 130 ሺህ ጦር በኤርትራ ልታሰፍር ነው ተባለ

ግብፅ 130 ሺህ ጦር በኤርትራ ልታሰፍር ነው ተባለ – ግብፅ በኤርትራ የጦር ሠፈር በመገንባት ከ20 ሺህ እስከ 130 ሺህ የሚደርስ ጦር ለማስፈር ማቀዷ የተዘገበ ሲሆን የኤርትራ መንግስትም ፈቃደኝነቱን መግለጹ ተጠቁሟል፡፡ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው በሰጡት ማብራሪያ፤ግብፅም ሆነ ሌሎች አገራት በአካባቢው የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለኢትዮጵያ ስጋት እንደማይሆን ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ግብጽን እንዲጎበኙ በፕሬዚዳንት አብደል ፈታህ ኤልሲሲ መጋበዛቸውን የጠቆመው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፤ ጠ/ሚኒስትሩም ግብዣውን እንደተቀበሉት አስታውቋል፡፡
የቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ለሱዳን ትሪቡን በሰጠው መረጃ፤ በቅርቡ በኤርትራ ጉብኝት ያደረገው የግብፅ ልኡካን ቡድን፣ግብጽ በኤርትራ ምድር የጦር ሰፈር ለመገንባት በሚያስችላት ሁኔታ ላይ የመከረ ሲሆን የኤርትራ መንግስት፤ግብጽ በዳህላክ ደሴት ላይ የጦር ሃይሏን እንድታሰፍር ፈቅዷል ብሏል፡፡
ግብፅ ቀደም ሲል ተመሳሳይ የጦር ሰፈር ጥያቄ  ሶማሊያን፣ ሶማሌ ላንድንና ጅቡቲን ጠይቃ የነበረ ቢሆንም እንዳልተሳካላት ይታወቃል፡፡
ግብፅ በአፍሪካ ቀንድ ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን እያሰፋች መምጣቷ፣ በአባይ ወንዝ ላይ የሚገነባውን የህዳሴውን ግድብ ለማስተጓጎል ነው ሲሉ አንዳንድ ወገኖች ስጋታቸውን ይገልጻሉ፡፡
ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በዚህ አይስማሙም፡፡ ግብፅን ጨምሮ ሳኡዲ አረቢያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ በኤርትራ የጦር ሰፈር ማቋቋማቸው በኢትዮጵያ ላይ ስለሚፈጥረው ስጋት የተጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የባህረ ሠላጤው አገራት እንቅስቃሴ ለኢትዮጵያ ስጋት እንደማይሆን ጠቁመው፣ ጉዳዩ በሶማሊያና በኤርትራ ካለው ሁኔታ ጋር መገናኘቱም ተገቢ አይደለም ብለዋል። የሚያመጣውን ተፅዕኖ ለመገምገም ከአጠቃላይ የአካባቢው ጂኦፖለቲካ አንፃር ማየት እንደሚገባ የገለፁት ጠ/ሚኒስትሩ፤ከዚህ አንፃር የአገራቱ እንቅስቃሴ ስጋት አይሆንብንም ብለዋል፡፡
ከግብፅ ጋር ከጊዜ ወደ ጊዜ ግንኙነታችን እየተጠናከረ ነው ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ፤ እንዲያውም መቀመጫቸውን ግብፅ አድርገው ኢትዮጵያን ለማተራመስ የሚሰሩ የሚዲያ ተቋማት ላይ ሀገሪቱ በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ እርምጃ መውሰድ ጀምራለች ብለዋል፡፡ OMN በተባለው ሚዲያ ላይ የነበሩ ግለሰቦችም በህግ ተጠያቂ እንደሚደረጉ፣የተወሰኑትም በግብጽ መንግስት  መታሰራቸውን ገልጸዋል – ጠ/ሚኒስትሩ፡፡
በሌላ በኩል የግብጹ ፕሬዚዳንት ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም አገራቸውን እንዲጎበኙ ጥሪ እንዳቀረቡላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ለአዲስ አድማስ ያስታወቀ ሲሆን ጠ/ሚኒስትሩም ግብዣውን እንደተቀበሉት ጠቁሟል፡፡
ሰሞኑን በግብጽ የሥራ ጉብኝት ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ባደረጉት ንግግር፤”ኢትዮጵያና ግብጽ ዕጣ ፈንታቸው የተያያዘ ነው፣አንዱ ለምቶ ሌላው ችግር ውስጥ እንዲሆን መፍቀድ ተገቢ አይደለም፤ የሁለቱ አገራት ዕጣ ፈንታ የተሳሰረ ነው፤ ወይ አብረን እንለማለን ወይ አብረን እንጠፋለን፤ ወይ አብረን እንዋኛለን ወይ አብረን እንሰጥማለን፤ ስለዚህ አማራጩ ተባብሮ መሥራት ነው” ብለዋል – የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ባደረሰን መረጃ፡፡ በግብጽ ሳንታና አሌክሳንደርያ አይሲስ በክርስትያን ምዕመኑ ላይ የፈጸመውን የሽብር ጥቃት የኮነኑት ዶ/ር ወርቅነህ፤ የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት በዚህ ፈታኝ ወቅት ላይ ከግብጻውያን ወንድሞቹና ወገኖቹ ጎን ይቆማል ብለዋል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በተደጋጋሚ በአዲስ አበባ መገናኘታቸውን የጠቆሙት የግብጹ ፕሬዚዳንት፤ ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር በተለያየ ወቅት ያደረጉት ውይይት ግንኙነቱ በመተማመን መንፈስ ላይ እንዲሆን አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል። “ኢትዮጵያና ግብጽ ታሪካዊ ወዳጆች ናቸው፤ ሥልጣኔ ያላቸው አገራት ናቸው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስና የግብጽ ኮፕቲክ ቤ/ክርስቲያን እንዲሁም የእስልምና ሃይማኖት የተሳሰሩ ናቸው፤ ይሄን ወዳጅነት የበለጠ ማጠናከር ለሁለቱ ህዝቦች ጠቃሚ ነው” ብለዋል፤የግብጹ ፕሬዚዳንት –