Monday, October 24, 2016

‹‹ጦርነት›› ከፊታችን የተደቀነ ልንጋፈጣው የሚገባ ዕውነት!


‹‹ጦርነት›› ከፊታችን የተደቀነ ልንጋፈጣው የሚገባ ዕውነት! 
ኧረ ጥራኝ ጫካው ኧረ ጥራኝ ዱሩ!
ላንተም ይሻልሃል ብቻን ከማደሩ፡፡
በሕዝባዊ እምቢተኛነትና ተቃውሞች አገዛዙ የሕዝብ ጥያቄዎችን ሊመልስ ይችላል የሚል ተስፋ የነበራቸው ወጣቶች አሁን ተስፋ ቆርጠዋል፡፡ ሽህዎችን ገድሎ ሽዎችን አካለ አጉድሎ አሁን ምንም የማይመስለው ሥርዓት መሆኑን እያየን ነው፡፡ ሥርዓቱ ፋሽስታዊነቱን የበለጠ አጠናክሯል፡፡ በየቀኑ የምንሰማው ስለሚገደሉ፣ ስለሚታሰሩና ስለሚሰደዱ ዜጎች ነው፡፡ ግን እስከ መቼ?
‹‹እኛ ርሀባችን ችለን ዝም አልናቸው፤ እነርሱ ግን ጥጋባቸውን መቻል አቃታቸው›› ያለው ማን ነበር ባያሌው? ከተራበ ለጠገበ እዘኑ እንዳሉት አበው ቀጣይ ጊዜያት ከተገዥዎች ይልቅ የገዥዎች ፀሐይ እንደምትጨለም ምንም ጥርጥር የለውም፡፡
የጠገቡት ጥጋባቸውን መያዝ አልቻሉም፤ የሚገድሉ ሰዎች አገዳደላቸውንም መመጠን አልሆነላቸውም፡፡ የሚገዙ ፋሽስቶች በተገዥዎች ላይ የጫኑት ቀንበር ቀሊል አይደለም፡፡ የሰላም በሮች በሙሉ ተዘግተዋል፡፡ በገዥዎችና በተገዥዎች መካከል ያለው ልዩነት መጥበብ የሚችል አልሆነም፡፡ ገዥዎች በሚያዩት ምልክት ማመን አልቻሉም፡፡ ሥልጣን ያሳብዳል፤ ኅሊናን ያሳውራል፡፡ በምልክት ብዛት ሕዝብ የሚለቅ ቢሆን ወያኔ ባለፈው ክረምት ብቻ የግብጹ ፈርዖን ካየው ምልክት የበለጠ አይቶ ነበር፡፡ ግን የወያኔ ግብዝነት ከፈርዖን እልፍ ጊዜ ይበልጣል፡፡
የዐማራ ወጣቶች ሆይ አስከፊ የሆነ ነገር ከፊታችን ተጋፍጧል፤ ልንሸሸው የማንችለው- ጦርነት፡፡ ጦርነቱን እኛ ስለፈለግነው የሚመጣ ወይም የሚቀር አይደለም፡፡ አገዛዙ አፈሙዙን ስቦብናል፡፡ በዚህም ከሁለት አስቀያሚ ምርጫዎች ጋር ልንጋፈጥ ግድ አለን፡፡ ሁለቱም መጥፎ አማራጮች ናቸው፡፡ ወይ ዝም ብሎ መገደል አሊያም እየገደሉ መሞት፡፡ የትኛው ይሻላል?
ሁለቱም መጥፎች ናቸው፡፡ ግን የተሻለ መጥፎ አለ፡፡ ሊገድል የሚመጣን ጠላት እየገደሉ መሞት የአባቶቻችን ስለሆነ ምርጫው ይህ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ የተሻለው መጥፎ ይህ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለንም፡፡ ግን የምንገብረውን የሰው ሕይወት መቀነስ ይኖርብናል፡፡
የምገብረውን የሰው ሕይወት ለመቀነስ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? ደግመን ደጋግመን እንደተናገርነው ጊዜ ሳናባክን ደም እንለግስ፡፡ የሕክምና ባለሙያዎች ድንገተኛ ሕክምና ዕርዳታ ለመስጠት ዝግጁ እንሁን፡፡ ይህም ልናደርገው ከሚገባን ጥንቃቄ በጣም ትንሹ ነው፡፡
በመጨረሻም የዐማራ ወንድሞች ሆይ የዘንድሮ ቀጠሯችን ገና ለመጫወት፣ በጥምቀት ሎሚ ለመወርወር እንዳልሆነ እናውቃለን፤ የገናው ሜዳ ወደ ጦር ሜዳ ተለውጧል፡፡ በቀጠሯችን ለመገናኘት የአባቶቻችን አምላክ ያብቃን፡፡

No comments:

Post a Comment