Monday, November 13, 2017

በኢትዮጵያ ማናቸውንም የተቃውሞ ስልፍ ማድረግ ተከለከለ

ዋዜማ ራዲዮ- የሀገሪቱ የፀጥታና ደህንነት ምክር ቤት ትናንት ባደረገው ስብስባ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚስተካከል አዲስ ስልፍና ተቃውሞ የማድረግ መብትን የሚያግድ ክልከላ ጥሏል።
አዲሱ የሰልፍ ገደብን የኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ ቢያቀርብበትም ከብዙ ክርክር በኋላ ስምምነት ተደርሶበታል።
በተለይ የፀጥታ ሀይሎች “እርምጃ መውሰድ እንዲችሉ” መባሉ የኦሮሚያን ክልል እንደሚያሳስበው ገልጿል።
በአዲሱ የፀጥታ ዕቅድ መሰረት ሀገሪቱን በተለያዩ ዕዞች በሚመሩ የፌደራል መከላከያ ስራዊት አመራር ስር በማድረግ ለመቆጣጠር ታቅዷል።
አደረጃጀቱ ከዚህ ቀደም የኮማንድ ፖስት በመባል የሚጠራውን መዋቅር የሚከተል መሆኑን በስብሰባው የተካፈሉና ስለ እቅዱ በቅርበት የሚያውቁ የዋዜማ ምንጭ ነግረውናል።
በተለይ የክልልና የልዩ ሀይል እንዲሁም የፌደራል የፀጥታ ሀይሎች መካከል ያለውን አለመናበብ ለማስወገድ ማናቸውም መመሪያ በፌደራሉ ዕዝ ብቻ የሚወሰን እንደሚሆን ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል።
“አስቸኳይ አዋጅ ተብሎ ያልወጣው አለማቀፉ ማህበረሰብ ሀገሪቱ አደጋ ላይ ናት ብሎ ያስባል፣ኢንቨስትመንትና ቱሪዝምንም ያዳክማል” በሚል መሆኑን ምንጫችን ተናግረዋል።
በፌደራል ፀጥታ አካላቱና በክልል ርዕሰ መስተዳድሮች መካከል ከፍተኛ አለመግባባትና አለመተማመን መከሰቱንም ከስብሰባው የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
“ሰው በመግደል ተቃውሞን ከማባባስ በቀር መፍትሄ አይመጣም፣ ፖለቲካዊ መፍትሄ ቢበጅለት የተሻለ ነው” በሚል የተከራከሩም ነበሩ።
በተለይ ብሄርን ማዕከል ባደረገ ጥቃት ከፍ ያለ አደጋ ተጋርጦብናል ያሉ ክልሎች መለዮ ለባሹ ጣልቃ ካልገባ ብዙ ጥፋት ይደርሳል ሲሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል።
ማህበራዊ ሚዲያን በሚመለከትም ስፊ ክርክር ተደርጓል። “እንደ አስፈላጊነቱ እርምጃ እንዲወሰድ” ከስምምነት ተደርሷል።
ከምክር ቤቱ አባላት የቀረቡትን ሀሳቦች በማካተት አዳዲስ የፀጥታ እርምጃዎች በተከታታይ የሚገለፁ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Sunday, November 12, 2017

አንዳንድ የገዢው ፖርቲና የሼህ አላሙዲ ደጋፊዎች ሼሁ ነገ ከእስር ተፈተው ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ በማለት በመዘገብ ላይ ናቸውዜናውን ከገለልተኛ ወ ገ ን ማረጋገጥ አልቻልንም!

አንዳንድ የገዢው ፖርቲና የሼህ አላሙዲ ደጋፊዎች ሼሁ ነገ ከእስር ተፈተው ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ በማለት በመዘገብ ላይ ናቸው
ዜናውን ከገለልተኛ ወ ገ ን ማረጋገጥ አልቻልንም!
አልቻልንም! ይህ ዘራፊ  ወንጀለኛ ሙሰኛ ዛሬ እንኳን ቢለቀቅ ኢትዮጰያ ውስጥ ለሰራው ወንጅል ግን አንድ ቀን የህዝብ መንግስት በሚቋቋምበት ጊዜ ግን ፍርዱን ያገኛል ምንም አትጠራጠሩ አገራችን እንዲህ አይነቱን ወንጀለኛ ዘራፊ ለማስጠጋት ቦታ ሊኖራት አይገባም!

Thursday, November 9, 2017

በኢትዮጵያ የተከሰተው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደረሰ


Filed under:   
      
ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደረሰ፡፡ በአሁን ሰዓት በመንግስት ካዝና ውስጥ ያለው የውጭ ምንዛሪ አንድ ግለሰብ ባለሀብት ካለው ገንዘብ ጋር እንኳን የማይወዳደርበት ደረጃ ላይ መድረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ በዚህም የተነሳ አገዛዙ ለመስራት አቀድኳቸው ካላቸው ፕሮጀክቶች መካከል አብዛኞቹ ቀጥ ብለው መቆማቸው ታውቋል፡፡ ጉዳዩ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነም፣ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አስደንጋጭ ነገር ሊከሰት እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በኢትዮጵያ የተከሰተው ከባድ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ጥላውን ካጠላባቸው የመንግስት ተቋማት አንዱ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም፣ በውጭ ምንዛሪ እጥረቱ የተነሳ ከፊል ስራውን ማቆሙም ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ ከውጭ የተበደረውን ገንዘብ መክፈል አቅቶት፣ የአበዳሪዎቹ ዓይን እየገረፈው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ተቋሙ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ለመስራት አቅዶት የነበረው ዕቅድ በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ ሳይሳካ መቅረቱን የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር አንዱዓለም አድማሴ ተናግረዋል፡፡ ዋና ስራ አስፈጻሚው እንዳሉት፣ በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ የተቋሙ አጠቃላይ የስራ መዋቅር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
‹‹የካፒታል ወጪያችን አፈጻጸም ዝቅተኛ ነው፡፡›› ያሉት ዶ/ር አንዱዓለም፣ ቀጠል አድርገው ‹‹በአሁኑ ጊዜ አብዛኛዎቹ ግዥዎቻችን በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት ተይዘው ነው የተቀመጡት፡፡  ግዥዎቻችን የሚከናወኑት ከውጭ ገበያ ነው፡፡ እነዚህን ዕቃዎች ለማስገባት የውጭ ምንዛሪ ይጠይቃሉ፡፡ ነገር ግን የእነዚህ ዕቃዎች ግዥዎች ባንክ ውስጥ ሠልፍ ላይ ነው ያሉት፡፡›› በማለት በሀገሪቱ ውስጥ ምን ያህል የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንደተከሰተ ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቀደም ከውጭ ተገዝተው የመጡ የባቡር ሐዲዶች በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ ከጅቡቲ ወደብ ወደ ሀገር ቤት ሳይገቡ ቀርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ ኢትዮ ቴሌኮም በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ ስራውን መስራት እንዳልቻለ ያማረረ ሲሆን፣ በሌሎች የመንግስት ተቋማት ያለው የውጭ ምንዛሪ እጥረትም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ወደኋላ እየጎተተው እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ብሔራዊ ባንክ በጥቅምት ወር መጀመሪያ የአንድ ዶላር ዋጋ በ27 የኢትዮጵያ ብር እንዲመዘነር አዲስ ህግ ካወጣ በኋላ፣ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ሙሉ በሙሉ መቃወሱን መረጃዎች እየጠቆሙ ናቸው፡፡
ከመንግስት ተቋማት በተጨማሪ በኢንቨስትመንት ስራ ላይ የተሰማሩ የግል ባለሀብቶች፣ በውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ ስራቸውን በአግባቡ እየሰሩ እንዳልሆነ በመናገር ላይ ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ስራ ላይ ከተሰማሩ ሰዎች አንዱ የሆነው አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ ከሶስት ሳምንት በፊት ከሀገር ውስጥ ሚዲያ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ፣ ከባንክ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት ያለው ውጣ ወረድ እና ሰልፍ አሰልቺ መሆኑን በምሬት ተናግሮ ነበር፡፡ ኃይሌ ‹‹በዚህ ሁኔታ ስራ መስራት ይከብዳል›› ሲልም ተማሮ ተናግሮ ነበር፡፡
BBN News November 9, 2017

ሳውዲ በሙስና ካለአግባብ የባከነው ገንዘብ 100 ቢሊየን ዶላር መሆኑን አጋለጠች ።

ኢሳት ዜና–ጥቅምት 30/2010) በሳውዲ አረቢያ እየተካሄደ ያለው ጸረ ሙስና ዘመቻ ምርመራ ካለአግባብ የባከነው ገንዘብ 100 ቢሊየን ዶላር መሆኑን አጋለጠ። በሌብነት ተጠርጥረው የተያዙት ሰዎች ቁጥርም 199 መድረሱን የሀገሪቱ ጠቅላይ አቃቢ ህግ አስታውቋል። ባለፈው ቅዳሜ ምሽት የተጀመረው ተጠርጣሪ ልኡላንን፣ሚኒስትሮችንና ነጋዴዎችን ኢላማ ያደረገው የጸረ ሙስናው ዘመቻው በ32 አመቱ አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሳልማን የተመራ ነው። በዘመቻው ተጠርጥረው ከተያዙት ውስጥ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆኑት ሼህ መሀመድ አላሙዲን እንደሚገኙበት ይታወቃል። ጠቅላይ አቃቢ ሕጉ ሼህ ሳውድ አል ሞጀብን ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው 100 ቢሊየን ዶላር የሚሆን ገንዘብ በሀገሪቱ በተደራጀ መንገድ በተፈጸመ ዝርፊያ ባለፉት ጥቂት አስርት አመታት ባክኗል ብለዋል። ዝርፊያ ስለመፈጸሙ...ም ጠንካራና አስተማማኝ መረጃ አለን ብለዋል። በዝርፊያው የተጠረጠሩት የንጉሳዊ ቤተሰቦችና ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር መዋላቸው በሀገሪቱ ያለውን የዕለት ተዕለት የንግድ እንቅስቃሴ እንዳላወከው አስታውቀዋል። የተጠርጣሪዎቹ የግል የባንክ ተቀማጭ ሂሳብ መዘጋቱንም ተናግረዋል። እስካሁን 1700 የባንክ ተቀማጭ የሂሳቦች መዘጋታቸውም ታውቋል። የጸረ ሙስና ኮሚቴውም ወደ ሚቀጥለው የምርመራ ደረጃ ለመንቀሳቀስ ሕጋዊ ፍቃድ እንዳለው ተናግረዋል። አቃቢ ሕጉ አክለውም እስካሁን 208 የሚሆኑ ሰዎች ለጥያቄ መቅረባቸውንና ሰባቱ ሳይከሰሱ በነጻ መለቀቃቸውን አስታውቀዋል። በሐገሪቱ ንጉስ ትዕዛዝ የተዋቀረው የጸረ ሙስና ኮሚቴም ስራውን በተቀላጠፈ ሁኔታ እያካሄደ መሆኑን አስታውቀዋል። ባለፉት ሶስት አመታት በተካሄደው ምርመራም 100 ቢሊየን ዶላር በተደራጀ ዘረፋ መባከኑን የሀገሪቱ አቃቢ ህግ ጨምረው ገልጸዋል። የተጠርጣሪዎቹን የሕግ መብት ለመጠበቅ ሲባልም በግለሰብ ደረጃ እያንዳንዳቸው ፈጽመውታል ተብሎ የሚጠረጠረውን ወንጀል ግን ከመግለጽ እንቆጠባለን ሲሉ ተናግረዋል አቃቢ ሕጉ። ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ከዋሉት አንዱ የሆኑት የሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲ ጉዳይ በኢትዮጵያ ትልቅ የመነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑ ሲቀጥል የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ዝምታን መርተዋል። የሕወሃት ድምጽ የሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ግን ጉዳዩን በተመለከተ ዘገባዎችን ሲያወጣ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ዛሬ ለመንግስትና ለገዢው ፓርቲ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ መንግስት ጉዳዩን በተመለከተ በዲፕሎማሲ መንገድ የሚመጡ መረጃዎችን እየተከታተለ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከዚህ ውጪ ግን ሳውዳረቢያ ሉአላዊ ሀገር እንደመሆኗ መጠን ሌላ ሊያደርጉት የሚችሉት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።

መረጃ በጨፌ ዶንሳ ው ተቃውሞ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በቃጠሎ ወድመዋል።

መረጃ
በጨፌ ዶንሳ ተቃውሞው ዛሬም ቀጥሎ ውሎአል። በርካታ ትምህርት ቤቶች፣ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና የመንግስት መስሪያ ቤቶች በቃጠሎ ወድመዋል። እስከ 15 የሚደርሱ ወጣቶች ተይዘው ታስረዋል። ከከተማዋ በ500 ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ሚሳኤል ምድብ እየተባለ የሚጠራው የአየር መቃወሚያን ጨምሮ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች የተከማቹበት ቦታ፣ በልዩ ሁኔታ እየተጠበቀ ነው። ተቃውሞው ነገም ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል።

Wednesday, November 8, 2017

ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ ለአደጋ የተጋለጠው የባለሀብቶቹ ንብረት 33 ቢሊየን ዶላር መሆኑ ተመልክቷል።

(ኢሳት ዜና–ጥቅምት 29/2010)የሳውዲ አረቢያ መንግስት ባለፈው ቅዳሜ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ የሌሎች ታሳሪዎችን የባንክ ተቀማጭ ሒሳብ አገደ። ከእስሩ ጋር በተያያዘ በአጠቃላይ ለአደጋ የተጋለጠው የባለሀብቶቹ ንብረት 33 ቢሊየን ዶላር እንደሚገመትም ከብሉምበርግ ዘገባ መረዳት ተችሏል። የሼህ መሀመድ አላሙዲን ቃል አቀባይ ከብሉምበርግ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ርምጃው በሳውዲ አረቢያ ውስጥ የተገደበና በሌሎች ሀገራት ያላቸውን ንብረት የማይመለከት መሆኑን ገልጸዋል። ቋሚ መኖሪያቸውን በሳውዳረቢያ ጅዳ ያደረጉት ሼህ መሀመድ አላሙዲን እስካለፈው ሳምንት መጨረሻ በሳውዳረቢያ ሪያድ በተካሄደው ግሎባል ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ከተገኙ በኋላ መያዛቸውና መታሰራቸውም ተመልክቷል። ከሳውዲ ባሻገር በሞሮኮ፣በሲውዲን...ና በኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢንቨስትመትን ያላቸው ሼህ መሀመድ አላሙዲን የሳውዲው እስራትና እገዳ በሌሎች ሀገራት ኢንቨስትመንታቸው ላይ ተጽእኖ አይኖረውም ሲሉ ቃል አቀባያቸው ቲም ፓንደር ተናግረዋል። በሳውዲ የተፈጠረውም ሁኔታ የንጉሳውያን ቤተሰቦች የውስጥ ችግር ነው ሲሉ ለብሩምበርግ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የ10 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር ሀብት ባለጸጋ በሆኑት በሼህ መሀመድ አላሙዲንና በሌሎች ታሳሪዎች ላይ የተጣለው እገዳ የግል ተቀማጭ ሂሳባቸውን ብቻ የሚመለከት መሆኑንም የሳውዳረቢያው ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል። የታሳሪዎቹ ኩባንያ ተቀማጭ ሒሳብ አለመታገዱንና ሕጋዊውን የባንክ ስርአት ተከትለው ገንዘባቸውን ማንቀሳቀስ እንደሚችሉም ይፋ ሆኗል። የብሪታኒያው ዴይሊ ሜል ይፋ ያደረገውና በታዋቂው ሪትዝ ካርልተን ሆቴል ወለል ላይ ፍራሽና ብርድልብስ ታድሏቸው የታሰሩት ባለስልጣናት፣ባለሃብቶችና ልኡካን በቁጥር 50 ያህል መሆናቸው ተመልክቷል። የሳውዳረቢያ ጠቅላይ አቃቢ ህግ እንደገለጹት ደግሞ ይህ እስራት የመጨረሻው ሳይሆን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን በቀጣይ የሚታሰሩ መኖራቸውንም አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዲቪ ቪዛ ሎተሪ እንዲሰረዝ በጠየቁት መሰረት ኢትዮጵያ ተጎጂ ነች ተባለ።

(ኢሳት ዜና–ጥቅምት 29/2010) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዲቪ ቪዛ ሎተሪ መርሃ ግብር እንዲሰረዝ በጠየቁት መሰረት ተግባራዊ የሚሆን ከሆነ በአፍሪካ ኢትዮጵያ፣ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ግብጽ ዋነኛ ተጎጂዎች ይሆናሉ ተባለ። እነዚህ ሀገራት በመርሃ ግብሩ መሰረት ብዙ ኮታ ከሚያገኙት ግንባር ቀደሞቹ መካከል መሆናቸውም ታውቋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጥያቄውን ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት አንድ የኡዝቤክስታን ተወላጅ ኒዮርክ ውስጥ ባደረሰው ጥቃት 8 ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ ነው። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገሪቱን የተወካዮች ምክር ቤት የዲቪ ቪዛ ሎተሪ መርሃ ግብር እንዲሰረዝ በጠየቁት መሰረት መርሃግብሩ የሚቀር ከሆነ በአፍሪካ ኢትዮጵያ፣ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ግብጽ ዋነኛ ተጎጂዎች እንደሚሆኑ ታውቋል። ባለፈው ሳምንት አንድ ...የኡዝቤክስታን ተወላጅ በእቃ መጫኛ መኪና ባደረሰው ጥቃት 8 ሰዎችን በኒዮርክ ከተማ ከገደለ በኋላ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወዲያውኑ የሀገሪቱ ምክር ቤት የዲቪ ቪዛ ፕሮግራምን እንዲሰርዝ ጠይቀዋል። የኡዝቤክስታኑ ተወላጅ ሳይፉሎ ሳይፓቭ የዲቪ ሎተሪ እድለኛ በመሆን እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2010 ወደ አሜሪካ መምጣቱ ታውቋል። በዲቪ ሎተሪ ወደ አሜሪካ የመጡ ሰዎች ጥቃት ሲፈጽሙ ይሄ ለ6ኛ ጊዜ መሆኑ ነው። በዚህም ምክንያት ይመስላል የዲቪ ሎተሪ ጉዳይ በአሜሪካ የፖለቲካ ሰዎች ዘንድ እንደገና መነጋገሪያ እየሆነ ነው። በተለይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ሰዎች የዲቪ ሎተሪው ወንጀለኞች ወደ አሜሪካ እንዲገቡ ቀላል መንገድ ፈጥሯል ባይ ናቸው። በአሜሪካ ምክር ቤት ያሉ አባላት የፕሬዝዳንቱን ሃሳብ እንደሚቀበሉትም ባልፈው ሰኞ አስታውቀዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኒዮርክ የደረሰውን ጥቃት እንደሰሙ ይህ የሎተሪ መርሃ ግብር ሰዎች በችሎታቸው ሳይሆን እንደ እድል ዕጣው ስለደረሳቸው ብቻ የሚመጡበት ነው ብለዋል። አፍሪካ በአንደኝነት የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ስትሆን አውሮፓና ኢሲያ ደግሞ ይከተላሉ። ባለፈው አመት ከአፍሪካ ከግብጽ 2 ሺ 855 ሰዎች የዕጣው አሸናፊ ሲሆኑ ከዲሞክራቲክ ሪፖብሊክ ኮንጎ 2 ሺ 778 ሰዎች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ደግሞ 2 ሺ 143 ሰዎች የዕጣው እድለኞች በመሆን በ3ኛ ደረጃ ተመዝግባለች። በየአመቱ ወደ 50ሺ የሚጠጉ ሰዎች የዕድሉ ተጠቃሚ እንደሆኑም ታውቋል። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2001 በኒዮርክ ከደረሰው የአሸባሪዎች ጥቃት 10 አመት ቀደም ብሎ በ1990 በፕሬዝዳንት ጆርጅ ኤች ደብሊው ቡሽ ፍርማ ህግ ሆኖ የወጣው የዳይቨርሲቲ ቪዛ ሎተሪ መርሃ ግብር የዕድሉ ተጠቃሚ ሆነው የሚመጡ ጥቂት ሰዎች እያደረሱ ባለው የሽብር ጥቃት ምክንያት መርሃ ግብሩ እንዲያከትም ግፊት እየተደረገ ይገኛል።

መረጃ በ ቄሮዎች በጨፌ ዶንሳ ከተማ የኦህዴድ ጽ/ቤትን ጨምሮ በርካታ ድርጅቶች ወድመዋል።

መረጃ
በጨፌ ዶንሳ ከተማ የሚገኙ ቄሮዎች ለሁለተኛ ቀን ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ እያደረጉ ነው። ከሸንኮራ ምንጃር ወጣቶች ጋር በመደዋወልና በመነጋገር ተቃውሞውን አጠናክረው ቀጥለዋል። የኦህዴድ ጽ/ቤትን ጨምሮ በርካታ ድርጅቶች ወድመዋል።
መከላከያና ፌደራል ፖሊስ ገብቶ በህዝብ ላይ መተኮስ ጀምሯል። የቻይና አረርቲ እንዱስትሪ ፓርክ ከፍተኛ ወድመት ደርሶበታል።

20 ሚሊየን የሚሆነዉ የደቡብ ህዝብ ለምን ዝም አለ?



ሁልጊዜ ስለ አማራና ኦሮሞ ነዉ የሚወራዉ ሌላ ብሄረሰብ በኢትዮጵያ የሌለ እስኪመስል ድረስ::
የደቡብ አክቲቪስትወች የሉምወይ??በ2ቱ ብሄር ትግል ብቻ ነፃ መውጣት የስርአት ለዉጥ ማምጣት ይቻላል ወይ? ደቡብ ላይ የሚሰራ በደል የለም ወይ? የራሳቸው አካባቢያዊ ችግርወች እንዳሉባቸዉ ይታወቃል ትምህርታቸዉን አቁዋርጠዉ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ በዝቅተኛ ስራወች ላይ በሰፊው ተሰማርተው የሚታዩት ህፃናትና ታዳጊወች በተለይም የወላይታ ታዳጊወች ጉዳይ በአንድ ወቅት የአዲስ አበባ ህዝብ መነጋገሪያ ነበር መንግስትትም አምኖ የተለያዩ የደቡብ ወረዳዎች በመሄድ ዶክመንተሪ የሰራበት አንዳንድ አካባቢዎች አዛውንቶች ብቻ የቀሩበት ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚደረገዉ ለከፍተኛ ስቃይና ሞት የሰውነት አካላት ዝርፍያ የተጋለጠ ዘግናኝ ጉዞ መነሻው የደቡብ አገራችን ክፍል ነዉ የደቡብ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ትግል በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ ለምን ደካማና ቀዝቃዛ ሆነ? በኦሮሚያ ና በአማራ የተነሳውን አመፅ ተከትሎ 76 የኦሮምኛ ወደ15 የአማራ የትግል ዘፈኖችና መዝሙር ወች ሲሰሩ የደቡብ አርቲስቶች ዝምታን ነዉ የመረጡት ተመችቱዋቸዉ ይሆን? አደራጅ አንቀሳቃሽ ማጣት???ምንድነዉ ምክንያቱ???የደቡብ ህዝብ ለመብትና ለኩልነት የሚደረገዉን ትግል ለምን መቀላቀል አልቻለም?? የደቡብ ምሁራንስ ልክ እንደ አሰፋ ጫቦ ለምን ድምፃቸዉን አያሰሙም አገር እየፈራረሰ……

አስተያየትዎን ይፃፉ

ዜና ሰበር በምንጃር እየተካሄደ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ የቻይና ፋብሪካ እየወደመ ነው


መረጃ
በምንጃር እየተካሄደ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ የቻይና ፋብሪካ እየወደመ ነው
የፋብሪካው ዘበኛ ተኩስ በመክፈቱ እስካሁን 3 ሰዎች መጎዳታቸው ታውቋል።
ተጨማሪ መረጃ
የአረርቲ እንዱስትሪ ፓርክ ሃላፊዎች ወታደሮች እንዲላኩላቸው ጥያቄ ቢያቀርብም እስካሁን ከገዢው ፓርቲ በኩል የተሰጠ መልስ የለም። የቻይና ዜጎችን ለማስወጣት መኪኖች ተንቀሳቅሰዋል።

Tuesday, November 7, 2017

ኬንያ 132 ኢትዮጵያውያንን እስር ቤት ከተተች


      
  

 
በኬንያ 132 ኢትዮጵያውያን ለእስር ተዳረጉ፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ለእስር የተዳረጉት እንደተለመደው በህገ ወጥ መንግድ ድንበር አቋርጣችሁ ገብታችኋል በሚል ምክንያት ነው፡፡ ስደተኞቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በአንድ ቤት ውስጥ ተቀምጠው ሳለ ሲሆን፣ ባይያዙ ኖረ ወደ ታንዛንያ የማቅናት ዕቅድ ነበራቸው፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ከሀገራቸው ተነስተው መንገድ የጀመሩት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት ሲሆን፣ ሆኖም ወደ ታንዛንያ ከማቅናታቸው በፊት ናይሮቢ ላይ በቁጥጥር ስር ለመዋል ተገድደዋል፡፡

ኢትዮጵያውያኑ ከሀገራቸው የተነሱት በደላሎች አማካይነት ሲሆን፣ ደላሎቹ እስከ ደቡብ አፍሪካ እንደሚያደርሷቸው ውል እንደነበራቸውም ታውቋል፡፡ ስደተኞቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላም፣ በድለላ ስራው ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉ ሁለት ኬንያውያንም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ስደተኞቹ በቀጣይ ፍርድ ቤት ቀርበው ቅጣት ሊተላለፍባቸው እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ቅጣቱ ወደ ገንዘብ ተቀይሮ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ሊደረግ እንደሚችልም ተገምቷል፡፡
የኢትዮጵያ ወጣቶች በሀገራቸው ያለውን የስራ አጥነት፣ የአገዛዙን አምባገነንነት እና መሰል ጉዳዮች ሸሽተው እንደሚሰደዱ ይታወቃል፡፡ ፊደል ያልቆጠረውን ጨምሮ እስከ ባለ ድግሪ ድረስ በስራ አጥነት የተነሳ ሀገር ጥሎ የሚሰደድባት ኢትዮጵያ፣ ለዜጎቿ አጅግ አስከፊ ሀገር እየሆነች መምጣቷን በሀገር ቤት ያሉ ዜጎች ይገልጻሉ፡፡ ‹‹በሀገር ቤት ያለው ኑሮ ከአቅም በላይ ባይሆን ኖሮ፣ ሰው እንደ ቅጠል የሚረግፍበትን በረሃ እና ውቅያኖስ አቋርጦ ስደት የሚወጣ አይኖርም ነበር፡፡›› ይላሉ-በሀገር ቤት ኑሮ የተማረሩ አስተያየት ሰጪዎች፡፡ በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ በኑሮውም በፍትሐዊ አስተዳር በኩልም ያልተዋጣለት እና ከቀን ወደ ቀን እየባሰበት የመጣ ስርዓት መሆኑን የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ የአገዛዙ ዕድሜ ካላጠረ በቀር በቀጣይ ዛፍ እና ወንዙ ጭምር ሳይሰደድ አይቀርም እንኳን ሰዉ ይላሉ- አስተያየት ሰጪዎቹ፡፡
BBN News November 7, 2017

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች የተሳሳተ መረጃ ሰጠ

  


 

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ለሚገኙ የውጭ ሀገር ዲፕሎማቶች የተሳሳተ መረጃ ሰጠ፡፡ የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በተገኙበት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በተካሔደው ወይይት ላይ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተገኝተው ነበር፡፡ ሚኒስትሩ በሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ገለጻ ለማድረግ በስብሰባው ላይ ቢገኙም፣ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል የተለያዩ ነባራዊ ሁኔታዎችን አዛብተው ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ በአሁን ሰዓት የፖለቲካ ምስቅልቅል እና የህዝብ ተቃውሞ እየበረታ ቢመጣም፣ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ግን ለዲፕሎማቶቹ ገለጻ ባደረጉበት ሰዓት፣ ሀገሪቱ ፍጹም ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ነው የተናገሩት፡፡ ‹‹በሀገሪቱ የተከሰተውን ግጭት አስቁመናል፡፡›› ሲሉ የተናገሩት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ህዝብ ላነሳው ጥያቄዎችም መንግስታቸው ምላሽ እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ሆኖም የዶ/ር ወርቅነህ መንግስት ለህዝብ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፣ ንጹኃንን በአደባባይ እየገደለ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ስለ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገለጻ ባደረጉበት ሰዓት ደግሞ፣ ‹‹መንግስት ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር እየተደራደረ እንደሚገኝና፣ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ እንደተደረሰም›› ተናግረዋል፡፡ ከመንግስት ጋር እየተደራደሩ ይገኛሉ የተባሉት ተቃዋሚዎች ግን፣ በህዝብ ዘንድ ፍጹም ተቀባይነት የሌላቸው፣ ከሊቀ መንበራቸው እና ከራሳቸው ሰራተኞች በቀር ሌላ ደጋፊም ሆነ ተከታይ ህዝብ የሌላቸው ፓርቲዎች መሆናቸው ሲነገር ቆይቷል፡፡

ዶ/ር ወርቅነህ ከእነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪም፣ በሀገሪቱ በጠቅላላ አሁን ላይ የሚያሰጋ ነገር እንደሌለ፣ የህዝቡም ጥያቄ በመንግስት አመራሮች እየተመሰለ እንደሆነ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ አስተዳደር እንደሰፈነ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የውጭ ሀገር ዲፕሎማቶች እና የተለያዩ ድርጅት ተወካዮች ገለጻ አድርገዋል፡፡ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገለጻ ያደረጉበት ውይይት እጅግ የሚያሳፍር እና አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን በዲፕሎማቶች ፊት በዚህ ደረጃ ይዋሻሉ ተበሎ ያልተጠበቀበት እንደነበር ውይይቱን የተከታተሉ ታዛቢዎች ተናግረዋል፡፡ ወይይቱ በጠቅላላ በተሳሳተ መረጃ እና የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ በማይገልጹ ቃላት የታጨቀ እንደበር ታዛቢዎቹ አክለው ተናግረዋል፡፡

በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለው መከላከያ ወታደር እየከዳ መምጣቱ ታወቀ

 

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)
ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወታደር መከላከያውን እየከዳ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በመከላከያ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ስጋት ተፈጥሯል። በጄነራል ሳሞራ የኑስ የተመራው ከፍተኛ የጦር አዛዦች የተገኙበት ስብሰባ ላይ ከወታደሮች መክዳት ጋር በተያያዘ ሰፊ ውይይት እንደተደረገ ለማወቅ ተችሏል።
በተለያዩ ክፍለ ጦሮች ውስጥ የወታደሩ መክዳት በከፍተኛ ሁኔታ መስተዋሉንና ባሉትም ወታደሮች መሀል የመንፈስ ጥንካሬ መዳከሙ በስብሰባው ላይ በሰፊው ውይይት የተደረገበት ጉዳይ ሆኗል። የክፍለ ጦር አዛዦች የወታደሮችን መክዳት የመከላከል ሃላፊነት የነሱ ድርሻ እንደሆነና ከአሁን በኋላም እድገት የሚሰጠው ወታደሮችን በማቆየት አመርቂ ውጤት ላመጡ አዛዦች እንደሚሆን ጄነራል ሳሞራ ገልጿል። በመከላከያ ውስጥ ከመክዳት ጋር ተያይዞ እየተፈጠረ ያለው ችግር ሃገሪቷ ከገባችበት የፖለቲካ ምስቅልቅል ጋር የተቆራኘ እንደሆነ መከላከያ ውስጥ ያሉ የጦር አዛዦች እርስ በርስ ሲያወሩ የሚገልጹት ቢሆንም በስብሰባው ላይ ደፍሮ የተናገረ እንደሌለ ለማወቅ ተችሏል። እንዲሁም የመከላከያ ሃይል ከምንጊዜም በላይ ጠንካራ እንደሆነ በሳሞራ የኑስ የቀረበው ገለጻ በስብሰባው ላይ የተገኙ አዛዦችን ሊያሳምን እንዳልቻለ ጉዳዩን በቅርብ ሲከታተል የነበረ ወኪላችን ተመልክቷል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የጄነራል ሳሞራን ስም እያነሱ ሲያሞጋግሱ ተስተውሏል። ከስብሰባው በኋላ የጦር አዛዦች እንዴት ተኩኖ ነው እየከዳ ያለውን ሰራዊት ማስቆም የሚቻለው፤ ሰራዊቱ ልቡ ከኛ አይደለም፤ በዚህ ሁኔታ መከላከያ አደጋ ውስጥ እየገባ ነው በማለት ጭንቀታቸውን ሲገልጹ ተስተውለዋል። በመከላከያ የተለያዩ ክፍለ ጦሮች ውስጥ የሚገኙ ወታደሮች በከፍተኛ ቁጥር መከላከያውን እየለቀቁ መምጣታቸውን ተከትሎ በአሁኑ ሰአት አንድ ሬጂመንት ጦር መያዝ ከሚገባው 700 የሰራዊት ቁጥር ውስጥ ከ400 በላይ እንዳልሆነ ከመከላከያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

አላሙዲንን በሆቴሉ ወለል ፍራሽ ታድሏቸው በአንድ ቦታ መታሰራቸውን በምስል የተደገፉ ሪፖርቶች አመለከቱ።

(ኢሳት ዜና–ጥቅምት 28/2010)ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ በቁጥጥር ስር የዋሉት የሳውዲ ባለሃብቶችና ባለስልጣናት የታሰሩበት ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል መሆኑ ቢረጋገጥም በሆቴሉ ወለል ፍራሽ ታድሏቸው በአንድ ቦታ መታሰራቸውን በምስል የተደገፉ ሪፖርቶች አመለከቱ። የሼህ መሀመድ አላሙዲን በሙስና ተጠርጥሮ መታሰር በኢትዮጵያ ባላቸው ኢንቨስትመንት ላይ የሚኖረው አንድምታ አነጋጋሪ ሆኗል። የሼህ መሀመድ አላሙዲን ከሳውዲ ልኡላንና ነጋዴዎች ጋር መታሰር በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በስፋት መዘገቡ ቢቀጥልም በኢትዮጵያ ውስጥ የመንግስትና የፓርቲ መገናኛ ብዙሃን በዝምታቸው ቀጥለዋል። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሳውዲ ከሙስና ጋር በተያያዘ እስራት መከተሉን ቢዘግብም የሼህ መሀመድ አላሙዲንን መታሰር ሳይጠቅሰው አልፏል። ዳሽን ባንክ ባለፈው ቅዳሜ በአዲስ አበባ ከተ...ማ ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ባስገነባው ግዙፍና ዘመናዊ ሕንጻ ምርቃት ላይ ይገኛሉ ተብለው የተጠበቁት ሺህ መሀመድ አላሙዲን በዕለቱ በሳውዲ አረቢያ ውስጥ በመታሰራቸው ሕንጻው እሳቸው በሌሉበት ተመርቋል። በኢትዮጵያ ሕግ በባንክና ኢንሹራንስ ዘርፍ ለመሰማራት የተፈቀደው ለኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ በመሆኑ ሼህ መሀመድ አላሙዲን ዳሽን ባንክን በቤተሰቦቻቸው አማካኝነት ማቋቋማቸው ተመልክቷል። በኢትዮጵያ በዋናነት በሆቴልና በማዕድን እንዲሁም በእርሻና በሲሚንቶ ኢንቨስትመንት ላይ መሰማራታቸው የተገለጸው የ71 አመቱ ባለሃብት ሼህ መሀመድ አላሙዲን በተለይ ከ1997 ምርጫ ወዲህ ስልጣን ላይ ላለው ቡድን በግልጽ በሚያሳዩት ድጋፍ ተቃውሞ ይሰነዘርባቸዋል። በተለይ በማዕድን ዘርፍ በሚሰሩት ኢንቨስትመንት የሀገሪቱን የወርቅ ሀብት በከፍተኛ ደረጃ እየመዘበሩ ነው በሚል ትችቶች እየቀረበባቸው ይገኛል። ይህም ለስርአቱ ለሚያሳዩት አጋርነት ስልጣን ላይ ባለው ቡድን በሚደረግ ድጋፍ የሚከናወን መሆኑም ተመልክቷል። በሌላም በኩል ባለሃብቱ ለስርአቱ ከሚሰጡት ድጋፍ ባልተናነሰ የሚያደርጉት በጎ አድራጎት ለሀገር ይጠቅማል በሚል ባለሃብቱን በበጎ የሚያነሷቸውም አልጠፉም። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የመንግስትና የገዢው ፓርቲ መገናኛ ብዙሃን የሼህ መሀመድ አላሙዲንን መታሰር በተመለከተ በዝምታ መቀጠላቸው የባለሃብቱ መታሰር በስርአቱ ውስጥ ድንጋጤ ስለመፍጠሩ የተገለጸውን የሚያጠናክር ሆኖ ተገኝቷል። የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ የሰፈነውን የፖለቲካ አፈናና የሰብአዊ መብት ረገጣ እንዲያሻሽል ያግዛል በሚል የአሜሪካ ኮንግረስ እንዲያጸድቀው የቀረበውን ረቂቅ ህግ ለማክሸፍ ከመንግስት ጋር ሎቢስት በመቅጠር ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውና በዚህ ረገድ የሚፈጠረው ክፍተት የመንግስት ባለስልጣናትን ሳያሳስብ እንዳልቀረ የሚገልጹ ወገኖች አሉ። በሌላም በኩል ብዙዎቹ ባለስልጣናት ገንዘብ የሚያሸሹት በርሳቸው አማካኝነት በመሆኑም ይህም ተጨማሪ ምናልባትም ዋና ስጋት እንደሆነባቸው ታውቋል። የሼህ አላሙዲን መታሰር በርሳቸው የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረው አንድምታ በእስሩ ርዝመትና ውጤት እንደሚወሰንም ባለሙያዎች ይናገራሉ። ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ ባለፈው ቅዳሜ የተያዙትና አሁንም በመያዝ ላይ የሚገኙት ባለሃብቶችና ባለስልጣናት በሪያድ እጅግ ውድ በተባለው ሪዝ ካርተን ሆቴል ወለል ላይ የነፍስ ወከፍ ፍራሽ ታድሏቸው መታሰራቸውን አለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን በምስል አስደግፈው ይፋ አድርገዋል። የሆቴሉ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡም ይፋ ሆኗል።

የአማራ ብሄር ተወላጆች ከአሶሳ ከተማ እንዲወጡ እየተደረገ ነው

(ኢሳት ዜና ጥቅምት 28 ቀን 2010 ዓም) ኤች አይቪ ቫይረስ አለባቸው የተባሉ የአማራ ብሄር ተወላጆች ከአሶሳ ከተማ እንዲወጡ እየተደረገ ነው
በቤንሻንጉል አሶሳ ከተማ የሚኖሩ ምግብ ና የጀበና ቡና በመሸጥ የሚተዳደሩ የአማራ ሴቶች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአስገዳጅ ሁኔታ የኤች አይቪ ምርመራ እንዲያደርጉ እየተገደዱ ሲሆን፣ ቫይረሱ ተገኝቶባችሁዋል የተባሉት ሴቶች ከስራ ቦታቸው ተፈናቅለው ወደ ክልላቸው እንዲሄዱ መገደዳቸውን ለአማራ ክልል ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እንዲሁም ለአማራ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ ማመልከታቸውን ከቢሮው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። የሴቶችን አቤቱታ ተከትሎ ከክልሉ ቢሮ አጣሪ ኮሚቴ ተመድቦ ወደ አሶሳ መላኩን ለማወቅ ተችሎአል። ድርገቱ የክልሉን ተወላጆች ከቤንሻንጉል ክልል ለማስወጣት የተቀየሰ አዲስ ስልት መሆኑን ምንጮች ገልጸዋ...ል።
በሌላ በኩል ሰሞኑን በሳምንቱ መጨረሻ በፋሲል ከነማ እና ውልዋሎ አዲግራት መካከል የተካሄደውን ጨዋታ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት ደማቸው የፈሰሰውን ወጣቶች ደም ደም እንመልሳለን በማለት ሁከት ለመቀስቀስ እንቅስቃሴ ጀምረዋል የተባሉ ወጣቶች ተለይተው በክትትል ውስጥ እንዲገቡ እና የእጅ ስልካቸውም እንዲጠለፍ መደረጉን የፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል።
ትናንት በነበረው የፖሊሶች ስብሰባ ላይ ኮማንደር ተኮላ " ደህና ወደ ሰላም የመጣውን ህዝብ እራሳቸው እየነካኩ ሌላ ችግር እየፈጠሩብን ነው፣ አሁን እንደገና የሞተ ሴል ነፍስ እየዘራ ነው፣ ካሁን በሁዋላ እነሱ እዛ እየነካኩ እዚህ ችግር ቢፈጠር እኛ ተጠያቂ አንሆንም” በማለት መናገሩን የፖሊስ ምንጮቻችን ገልጸዋል።


ከአዲስ አበባ ዙሪያ ካሉ ኦሮሚያ ከተሞች የወላይታ ተወላጆች እየታፈሱ ነው።





በአዲስ አበባ ዙርያ የኦሮምያ ክልል ልዩ ዞን ውስጥ የሚኖሩ የኦሮምያ ተወላጅ ያልሆኑ በብዛት የወላይታ ተወላጆችን ከከታ አካባቢ በመንግስት የፀጥታ ሀይሎችና ባለስልጣናት አስገዳጅነት በመኪና ተጭነው እንዲወጡ ከተደረገ በሁዋላ በአዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6  የወጣቶች ማዕከል ህንፃና በወረዳው ፅ፨ቤት ቅፅር ግቢ ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ፥፥ ቁጥራቸው በግምት ከ400 - 500 ይደርሳል፥፥ የተፈናቀሉበት ምክንያት ለጊዜው በውል የታወቀ አይደለም፥፥

ሰበር_መረጃ ደሴ ነጋዴዎች የስራ ማቆም አድማ ጀምረዋል፡፡



#ሰበር_መረጃ
#በዛሬው እለት በደሴ ከተማ ልዩ ቦታው አራዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የደሴ ከተማ ትልቁ የንግድ ማእከል በሆነው ቦታ አምስት ትልልቅ ህንፃዎች በድምሩ ከአንድ ሺህ በላይ ሱቆች የስራ ማቆም አድማ ጀምረዋል፡፡
************
#አገዛዙ በህዝብ ላይ ጥሎት የቆየው ካቅም በላይ የሆነ የግብር ክፍያን በመቃወም በአካባው ይነግዱ የነበሩ ባለሱቆች ሱቆቻቸውን መዝጋታቸውና ስራ ማቆመማቸው ታውቋል፡፡ ነጋዴዎቹ እንደሚሉትም አገዛዙ ያለ ሃቅማችን መክፍል የማንችለውን ግብር ጥሎብናል የተጣለብን ግብር ከጠቅላላው ገቢያችን የበለጠነው በማለት ቅሬታቸውንም አሰምተዋል የአገዛዙ አገልጋይ የሆኑ የቀበሌው ሹሞችም በቦታው በመሆን ሱቃችሁን ካልከፈታችሁ እርምጃ እንወስዳለን እያሉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ነጋዴዎቹም በበኩላቸው የዚህ ስርዓት አምባገነንነትና ዘራፊነቱን ተገንዝባችሁ ሌሎቻችሁም የአካባቢው ሰዎች የነዚህን ነጋዴዎች ፈለግ በመከተል አገዛዙን እምቢ አልገዛም ያለ አግባብ ግብር አልከፍልም ለሹሞች መበልፀጊያ ይሆን ዘንድ የልጆቼን ጉሮሮ አልዘጋም በማለት የዚህ ትግል አካል እንድትሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ውድ ተከታታዮቻችን ከስፍራው የሚደርሱንን መረጃዎች እየተከታተልን የምናቀርብ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ
አስተያየትዎን ይፃፉ

የዝቅጠት መጨረሻ!


የዝቅጠት መጨረሻ! የኢትዮጵያ መንግስት ስንቱን ዜጋ በፖለቲካ አቋሙና በጋዜጠኝነት ሙያው ሳቢያ አስሮ ዘቅዝቆ ሲገርፍ ትንፍሽ ያላለ ሁላ አሁን አንድ ሀብታም ያውም በወንጀል ያውም ሳውዳረቢያ ሲታሰር የፍቱልን ሰላማዊ ሰልፍ ይወጣል! እስኪ ምን ይመስላችሁዋል?

Sunday, November 5, 2017

ሰበር ዜና በአሜሪካ በቶክስ እሩምታ በጥቂቱ 27 ሰው ሞተ ::

ሰበር ዜና
አሜሪካ- ቴክሳስ በአንድ ቤተክርስቲያን በእሁድ /ሰንበት ፀሎት ላይ በነበሩ ፀላዩች ላይ ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ በተከፈተ የቶክስ እሩምታ በጥቂቱ 27 ሰው ሲሞት በርካቶች መቁሰላቸው እየተዘገበ ነው::

ሼክ መሐመድ አላሙዲ ኢትዮጵያ ውስጥ ከነበረከት ስምዖን ጀርባ ሰርተውታል ተብሎ የሚጠረጠሩበት የሙስና ወንጀሎች

 

ሼክ መሐመድ አላሙዲ ኢትዮጵያ ውስጥ ከነበረከት ስምዖን ጀርባ ሰርተውታል ተብሎ የሚጠረጠሩበት የሙስና ወንጀሎች

 

Wednesday, November 1, 2017

ህወሃት ከየመን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን እንጂ የታገሉለትን አላማ መጥለፍ አልቻለም

Print Friendly, PDF & Email
(ቢንያም ሙሉጌታ ከኖርዌ)
ዘረኞቹ ህወሃት ወያኔዎች የምንወዳትን ኢትዮጵያ ሀገራችንን ደግመው ደጋግመው እንዳያደሙት የህዝባችን መከራና ስቃይ እንዲያቆም ገዳዮቻችንን አጥፊዎቻችንን ሊፋረዳቸው በህይወቱና በቤተሰቦቹ የጨከነ የስርዓቱን የውድቀት ምዕራፍ ወደፊት ያፋጠነ ወደ ፊት እንጂ ወደ ኃላ የምንመለስባት ሌላ ኢትዮጵያ እንደሌለን እውነታውን አስረግጦ ያስገነዘበን አንዳርጋቸው ፅጌ ዛሬ በወያኔ ህወሃት ውድቀት ዋዜማ ልናስታውሰው ይገባል። ዳኛውም ዝንጀሮ ፍርድ ቤቱም ገደል እምን ላይ ተሁኖ ይነገራል በደል እንዲሉ በሀገራችን ውስጥ ምንም ዓይነት ፍትህ እኩልነትና ዲሞክራሲ እንደሌለና ዜጎች በመናገራቸው የሚታሰሩበት የሚገደሉበት በዘራቸው ምክንያት እንደ ጠላት የሚፈረጁበት ከአንድ አካባቢ የመጡ ሰዎች ብቻ ሀገሪቱን ኢኮኖሚዋን ስልጣኑን ተቆጣጥረው ሌላውን ኢትዮጵያዊ የበይ ተመልካች አድርገው ወያኔዎች ሲጨርሱት ሲያስፈልጋቸው በጥይት ሲደፉት ይህንን እውነት ቀድሞ የተረዳው ያስቆጣው ያንገበገበው አንድአርጋቸው ፅጌ ፍትህ በዛች ሀገር ላይ እንዲሰፍን በማለት የኔ የሚለውን ነገ ሁሉ ላይ ጨክኖ ህወሀት (ወያኔን) ሊፋለም እስከ ህይወት መስዋአትነት ሊከፍል እርሱ ሞቶ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ነፃ ሊያወጣ ሁሉን ጥሎ ሜዳ ገብቶ አምባገኑን የወያኔ ስርዐትን ሊታገል የወሰነና የታገለ ሁሌም በኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ያለ ታላቅ ታጋይ ነው አንድአርጋቸው ፅጌ፡፡
እርሱ ነዶ ብርሀን ሆነ የድርሻውን ያለውን ሁሉ ለአንዲት ኢትዮጵያ ከፈለ። አምባገነኑ ስርዐት የአንዳርጋቸው ፅጌን አቅምና ችሎታ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ እንቅልፍ ነስቶትና ስጋቱንም ከጫፍ አድርሶት እንደነበር ግልፅ ነው፡፡ ይህንን ታላቅ ታጋይ ወጥመድ ውስጥ ለማስገባት የህወሀት (ወያኔ) የስለላ ተቋም በሚልዮን የሚቆጠርን ዶላር ከማውጣት ጀምሮ ብዙ ድካምና ዋጋ እንዳሰከፈለው ግልፅ ነው ለዚህም ነው በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሀገራትን አቋርጦ በመሄድ ጠለፋን ያካሄደው የታጋይ አንድአርጋቸው ፅጌን ተፅእኖ ፈጣሪነትና ለሕወሀት ወያኔ ራስ ምታት እንደነበር የሚያሳይ ግልፅ ትእይንት ነው።
አንድአርጋቸው ፅጌ ዛሬም ቢሆን በልባችን ውስጥ ያለ ጀግና ነው ባለው ፅኑ አቋምና ቆራጥነት አልበገሬነት የወያኔን አምባገነንና አፋኝ ስርዐትን እንቅልፍ የነሳ የቁርጥ ቀን ልጅ እንዲሁም የኢትዮጵያዊያን ባለውለታ ነው፡፡ ለሁሉም ነፃነት ናፋቂና ታጋይ ኢትዮጵያዊ ለትግል ጉዞ አርአያ በመሆን የቆራጥነትን ጥግ ያሳየ መሪ ነው፡፡
አቶ አንድአርጋቸው ፅጌ ከማንም በተሻለ ሁኔታ የወያኔ (ሕወሀት) መሰሪ አሰራርን ጠንቅቆ የሚያውቅ እና ኢትዮጵያ ሀገራችንን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየከተትዋት እንደሆነ የተረዳ ሰው ነው ዛሬ ላይም ለነፃነት፣ ለአንድነት ፣ ለዲሞክራሲ መከበር የምንታገል ኢትዮጵያዊያን ትግል ማለት ምን እንደሆነ በደንብ የተረዳነው ከአንድአርጋቸው ፅጌ የህይወት ቆራጥነት ነው ለነፃነት የሚከፍሉ መስዋዕትነት ግራ ቀኝን ማየት መመልከት አይጠይቅም፡፡ በጠቅላላ ትኩረት እና ሀሳብን ግብ ላይ ማድረግን ብቻ ነው የሚፈልገው።
ይህ አጥፊ ስርዐት ላለፉት 26 አመታት ኢትዮጵያዊያን ላይ የቀበራቸው ፈንጂዎች ኢትዮጵያዊያን ላይ ሳይሆን ራሱ ላይ እያፈነዳ እየፈጀው ይገኛል። ጀግናው ታጋይ አንድአርጋቸው ፅጌን ቢያስሩም እርሱን የቆመለትን አላማ ማሰር አልቻሉም ለዚህም ነው ከሃገር ውስጥ ሆነ ከውጭ ሀገራት ወያኔን ገዝግዞ ሊጥለው የደረሰው አዲሱ ነፃነት ፈላጊው ትውልድ ያነገበው የፍትህ የዲሞክራሲ ጥያቄና ስርዐቱንም ከስልጣን የማስወገድ ትግል አቶ አንድአርገቸው ፅጌ ዋጋ የከፈለለትና ማየት የሚናፍቀው የነበር ነው ዛሬ ላይ ግን የእርሱ ህልም እውን ሊሆን የወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ዘመን ሊያበቃ ዘረኝነቱም ሊቋጭ ቀብሩ ሊፈፀም 11ኛ ሰዐት ላይ እንገኛለን፡፡
የነፃነት አባት የሆነውን አንድአርጋቸው ፅጌና ሌሎች ብዙ ዋጋ የከፈሉ ኢትዮጵያዊያንን የታሰሩ የተገደሉ አሁንም ድረስ በየ እስር ቤቱ የሚገኙትን ጨምሮ ሁሉንም ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ ሃገራችንን ኢትዮጵያን ሕወሀት ወያኔ አጥፍቶ ሳይጨርሳት ታጋይ አንድአርጋቸው ፅጌ እና ከፍተኛ የተቀዋሚ አመራሮችን ጨምሮ ህዝብን በማደራጀት እንዲሁም በማስተማርና ግንዛቤው እንዲጨምር በማድረግ የእያንዳንዳቸውን ድርሻ ቀድመው ተወተዋል ዛሬ የምናየው ህዝባዊ እንቢተኛነትና የነፃነት ትግል በእነ አቶ አንድአርጋቸው ፅጌ የመመካከርና የመተባበር አጀንዳ የመጣ ውጤት ነው፡፡
አሁን በምናየው የሃገራችን ሁኔታ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ እንዲያሸንፍ አንድነት ሀይል እንደሆነ ዘረኛውንና አሸባሪውን የወያኔ ስርዐት በዘረጋው የመከፋፈል እና የመበታተን ሃሳብ ውጤታማ እንዳይሆን ይህንን የሕወሀት (ወያኔ) ሴራ ቀድሞ በማጋለጥ አቶ አንድአርጋቸው ፅጌ ዋነኛና ቀዳሚ ነው፡፡
አንድአርጋቸው ፅጌ ለሃሩና ለወገኑ ቆመ እንጂ ወገኑንና ሀገሩን ለገንዘብና ለንዋይ አልሸጠም ለግል ክብሩ አልተጨነቀም የኢትዮጵያ ህዝብን እንደ መዥገር ከተጣበቀበት ስርዐት ለመገላል የከፈለውን ዋጋ እንዲሁም ለዜጎች መብትና ነፃነት መከበር የነበረውን አስተዋፅኦ የትግል አጋሮቹና ኢትዮጵያዊያን ጠንቅቆ ያውቃል፡፡
የወያኔ (ሕወሀት) ግፍና በደል የህዝባችን ሮሮ ማብቂያ ዋዜማ ላይ የደረስነው ቆራጥና ለአላማው ብርቱ የነበረው አንድአርጋቸው ፅጌ ያነገበውን አላማ ይዘን በፍጥነት በመጔዝ ስለቻልን ነው ከዚ ቡሃላ ያረጀው ስርዐት ምንም እድል ፋንታ የለውም በኢትዮጵያ ህዝብ እምቢተኛነት የተሸነፈ ነው፡፡ አርቆ መቅበር ብቻ ነው የሚያስፈልገው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Tuesday, October 31, 2017

ጭቆናን #በጭካኔ ማሸነፍ አይቻልም! — ስዩም ተሾመ

 

እኔ፣ ይህን ስርዓት የምነቅፈው፣ ሥራና አሰራሩን ዘወትር የምተቸው፣… ጠዋት ማታ የምፅፈው፣ የምናገረው፣ የማስበው፣ የዜጎች መብትና ነፃነት እንዲከበር ነው! “የአንድ ወገን የበላይነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የብዙሃኑ መብትና ነፃነት መጣስ የለበትም” ብዬ ስለማምን ነው። ይህ የአንዱ ብሔር ደጋፊ፣ የሌላው ብሔር ተቃዋሚ በመሆን ሳይሆን፣ “ሁሉም ሰው እንደ ሰው እኩል መብት፥ ነፃነትና ተጠቃሚነት ይገባዋል” የሚል ፅኑ እምነት ስላለኝ ነው። ነጋ ጠባ “የኦሮሞ ሕዝብ መብት ይከበር!” እያልኩ የምጮኸው የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን እንጂ ሰሞኑን በኢሊባቡርና በመቱ፣ ዛሬ ደግሞ በነቀምት እንደሆነው፣ በተለይ የአማራና የትግራይ ተወላጆች መንገድ ላይ ተደፍተው እንዲቀሩ አይደለም።
የኦሮሚያ #አድማ_በተኝና የአከባቢው ፖሊሶች፣ የንፁሃን ዜጎች ሕይወትና ንብረት ሲጠፋ በቅርብ ርቀት ቆመው ሲመለከቱ ማየትን የመሰለ አሳፋሪ ነገር የለም። ይሄ የመጨረሻ ስሜት አልባነት ነው! የሞራል ዝቅጠት ነው! ለኦሮሞ ሕዝብ ሆነ ለክልሉ መንግስት ታላቅ ውርደት ነው! የኦሮሞ ሕዝብ መብትና ነፃነት የሚከበረው በፖለቲካዊ ስልትና የሞራል የበላይነት እንጂ በጭቃኔና ስርዓት-አልበኝነት አይደለም። ጭቆናን በጭካኔ ማሸነፍ አይቻልም።
 

የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝባዊ ስብሰባና የባሕር ዳር እሥረኞቹ መለቀቅ


By ሳተናውOctober 30, 2017 16:26

 
የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝባዊ ስብሰባ
ሰማያዊ ፓርቲ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ላለፈው አንድ ዓመት የሚሆን ጊዜ የመጀመሪያዊን ሕዝባዊ ስብሰባ ትናንት አዲስ አበባ ላይ አካሂዷል።
ሰማያዊ ፓርቲ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ላለፈው አንድ ዓመት የሚሆን ጊዜ የመጀመሪያዊን ሕዝባዊ ስብሰባ ትናንት አዲስ አበባ ላይ አካሂዷል።በመብራት ኃይል አዳራሽ ውስጥ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ ቁጥሩ ከስምንት መቶ ያላነሰ ሰው መገኘቱን የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታነህ ባልቻ ማምሻውን ለቪኤኤ ገልፀዋል።


የፊታችን ዕሁድ፣ መስከረም 26/2010 ዓ.ም ከምኒሊክ አደባባይ ተነስቶ መስቀል አደባባይ ላይ የሚጠናቀቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግም ሰማያዊ ፓርቲ አስታውቋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባለፈው ሐሙስ፣ ጥቅምት 16/2010 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ባሕር ዳር ከተማ ላይ በነኀሴ 2ዐ1ዐ ዓ.ም. ተካሂዶ ከነበረውና ብዙ ጉዳይት ከደረበት ሰልፍ ጋር ተያይዞ በእሥር ላይ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን፣ በተለይ ደግሞ የፓርቲውን የባሕር ዳር ከተማ መሪዎች በነፃ ማሰናበቱ ታውቋል።
በፓርቲው መሪዎችና አባላት ላይ ለአሥራ አንድ ወራት ያህል ክሥ ሳይመሠረት መቆየቱን ለቪኦኤ የገለፁት የፓርቲው የባሕር ዳር ከተማ ሰብሳቢ አቶ ማሩ ዳኘው እና ምክትላቸው አቶ መልከሙ ታደሰ ክሡ ሲቀርብም ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ ከዕድሜ ልክ እሥራት እስ ሞት የሚያሰቀጣ የወንጀል ክሥ እንደነበር አመልክተዋል።

የትግሬ ነፍስ ከሌላው ይበልጣልን?


By ሳተናውOctober 30, 2017 17:02
    
ሙሉቀን ተስፋው
ሦስት ትግሬዎች ነቀምት ላይ መገደላቸውን ተከትሎ አገር ቁልቢጥ ሆናለች፤ ነገሩ በሦስት የሚቆም ቢሆን ባልከፋ! ገና ከአስቀያሚው ዘመን ዋዜማ ላይ መሆናችን ለፈርዖኖቹ አልታያቸውም፡፡
የኦሮሞን ወጣት በለው ጨርሰው እያለ የትግሬ ወታደር በአምቦ ሲገድል አላወገዙም፤ የዐማራ ስጋ በከማሽ የጅብ ቀለብ ሲሆን የትግሬ እስካልሆነ ድረስ ምንም አይደለም፡፡ በወልቃይትና ጠገዴ ዐማራን ገድለው በመኪና አስከሬን የሚጎትቱ እነዚህ አውሬዎች ዛሬ ሦስት ተጋሩዎች መሞታቸውን ተከትለው አገር ይያዝ ኡኡ እያሉ ነው፡፡ እኔ የማዝነው አንድ አስተዋይ ሽማግሌ በማጣታቸው ነው፤ መጪው ጊዜ የከፋ መሆኑን የሚነግራቸው፡፡
ግብዞቹ በጎንደር የእርቅ ኮንፍረንስ ለማካሔድ አስበናል እያሉን ነው፡፡ የወልቃይትና የራያ ዐማሮች ዐማራነታቸው ሳይከበር ዕርቅ አይደለም ከሚቀጥሉት መቶ ዓመታት በኋላ እንኳ የተገነባው የጥላቻ ግንብ መፍረስ የሚችል አይደለም፡፡ መቼም አይፈርስም! መጪው የዐማራ ትውልድ አባቱንና ወንድሙን ማን እንደገደለበት እርስቱን ማን እንደቀማው ከ‹ሀ ሁ› ፊደል ጋር እኩል እየቆጠረ ያድጋል፡፡ ከዚያ ትውልዱ በራሱ የሚያደርገውን ያውቃል፡፡



በተፈጠረው ችግር የአቶ ኃይለማርያም መንግስት ሥልጣን መልቀቅ ነበረበት – ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ በአገሪቱ ወቅታዊ ችግሮች ዙሪያ


     


• በተፈጠረው ችግር የአቶ ኃይለማርያም መንግስት ሥልጣን መልቀቅ ነበረበት
• በየዞኑና በየወረዳው የሚፈጠረውን ግጭት የሚያነሳሱት ካድሬዎች ናቸው
• ህዝቡ የህግ ጥበቃ ያስፈልገዋል፤ አጥፊዎች በህግ መጠየቅ አለባቸው
• የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ዶግማ አይደለም፤መከለስ ይችላል
አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተነሳው ሰላምና መረጋጋት ሰፍኗል በሚል ቢሆንም ግጭቱና አለመረጋጋቱ በየጊዜው እየተባባሰ ነው የመጣው። ለዚህ ምክንያቱ ምን ይመስልዎታል?
ህዝብ ጥያቄዎቹን በዝርዝር አቅርቦ፣ ይመለሱልኝ ሲል፣ ገዥው ፓርቲ በተቃራኒው ራሴን በጥልቀት እየገመገምኩ ነኝ ማለቱና ይሄም ከህዝብ ቀጥተኛ ጥያቄ ጋር የሚገናኝ አለመሆኑ ነው፡፡ ፓርቲው በራሱ ጣጣ ሲገማገም ሊኖር ይችላል፤ የእነሱ መገማገም ግን  የህዝቡን ጥያቄ መፍታት ማለት አይደለም፡፡ የህዝቡ ቀጥተኛ ጥያቄ እስካልተመለሰ ድረስ ደግሞ ጥያቄዎቹ በየጊዜው ተጨማሪ ገፅታ እየያዙ ነው የሚመጡት፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቀድሞ በነበሩት ጥያቄዎች ላይ “የታሰሩ መሪዎቻችን ይፈቱ” የሚለውም ተጨምሮበታል፡፡ አሁን የህዝቡ ብሶት በላይ በላዩ እየተደራረበ ነው ያለው፡፡ የዚህ መጨረሻው ምን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ ግን ጊዜ የሚፈታው ጉዳይ ነው የሚሆነው፡፡
ገዥው ፓርቲ “ጥልቅ ተሃድሶ አደርጋለሁ” ሲል ምን ነበር  የተጠበቀው?
እንግዲህ አንዱ “አጠልቀዋለሁ” የሚለው የዲሞክራሲ ጉዳይ ነው፡፡ ዲሞክራሲን እያጠለቅን ነው ይላሉ፡፡ ነገር ግን እነሱ የሚሉት ዲሞክራሲና ዓለም የሚያውቀው እንዲሁም እኛ የምንታገልለት ለየቅል ናቸው፡፡ ምንም ግንኙነት የላቸውም፡፡ እነሱ ዲሞክራሲ የሚሉት፡- በማርክሲስት ሌኒኒስት ቀኖና የተቃኘ፣ በአንድ ፓርቲ የበላይነት ሁሉንም ፀጥ ለጥ አድርጎ፣ እኔን ብቻ ስሙ የሚለውን አስተሳሰብ ነው፡፡
እናንተ የምትሉት “ዲሞክራሲ” እና ኢህአዴግ የሚለው “ዲሞክራሲ” ትርጉሙ የተለያየው ከመቼ አንስቶ ነው? በፊትም አንስቶ ነው ወይስ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ?
አስታውሳለሁ፤ በሽግግር ወቅት ከእነሱ ጋር አብሬ ለመስራት በሞከርኩበት ወቅት አንዱ ወደ ፖሊቲካው ለማግባት መነሻ የሆነኝ፣ ኢህአዴግ የመደብለ ፓርቲ ስርአት አሰፍናለሁ የሚል ቃል በመግባቱ ነው፡፡ ነገር ግን በሂደት አቋማቸውን ቀይረው፣ የአንድ ፓርቲ የበላይነትና ፍጹማዊ አገዛዝን እውን ለማድረግ ነው የተንቀሳቀሱት። እነሱ አሁን የቻይናውን ኮሚኒስት ፓርቲ ሞዴል ለመከተል የሚፈልጉ ነው የሚመስለው፡፡ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ላለፉት 70 ዓመታት በተግባሩ የብዙዎችን ይሁንታ ያገኘ ይመስላል፡፡ የቻይና እና የእኛ አገር ሁኔታ ግን ጨርሶ የተለያየ ነው። ቻይና አንድ ህዝብ ነው፡፡ “ይሄ ብሔር ያንን ጨቆነ፣ ተጨቋቆንን” የሚባል ነገር የለም፡፡ እነሱ በዚያ መነሻ በአንድ ፓርቲ ቢመሩ ምንም ላይሆን ይችላል፡፡ ኢህአዴግ ግን ለዚያ የሚበቃ ተክለ ሰውነት የለውም፡፡ የሃገሪቱ ሁኔታም ያንን በቀላሉ አይፈቅድም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ፍላጎቶች አሉ፡፡ ያንን ማግባባት ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር አሁን እየተደረገ  ያለው ነገር ብዙም ተስፋ ሰጪ አይደለም፡፡
የመድብለ ፓርቲ ሥርአት የመመሥረት ተስፋ  ለምን የተዳፈነ  ይመስልዎታል?
እኔ ለረጅም ጊዜ አውጥቼ አውርጄ የደረስኩበት ዋናው ምክንያት፣ ደርግን ከስልጣን ማውረዳቸውን “የኢትዮጵያ ህዝብ  ሙሉ ለሙሉ  እንደ ውለታ ይቆጥርልናል” የሚል ሃሳብ ይዘው መነሳታቸው ነው፡፡ ህዝቡ እነሱን እንደ ነፃ አውጪ ቆጥሮ፣ ከማንም የፖለቲካ ፓርቲ ጋር ቢወዳደሩ፣ ማሸነፍ እንደሚችሉ አስበው  ነው የተነሱት፡፡ ወደ ተግባር ሲገቡ ነው ችግር የገጠማቸው፡፡ የመጀመሪያ ምርጫ ሲካሄድ በየቀበሌውና ወረዳው በእጅ በማውጣት ነበር፡፡ በዚያ ምርጫ ላይ ኢህአዴግ በአዲስ አበባም በክልሎችም በከፍተኛ ብልጫ ተሸንፎ ነበር። በተለይ በኦሮሚያ ኦነግ ነበር ያሸነፈው። ይሄ ምርጫ ለኢህአዴግ ከፍተኛ ምልክት ነበር ያሳየው። በወቅቱ “ዛሬ በእጅ በማውጣት ምርጫ ህዝብ እንዲህ ከጣለን በኮሮጆ ምርጫስ  ምን ሊያደርገን ይችላል?” በሚል  ግራ ተጋብተው ነበር። ይሄንን መነሻ አድርገውም ግምገማ አድርገዋል፡፡ እኛ በሽግግር መንግስቱ ውስጥ ገብተን የነበርነውንም በዚህ ምክንያት ማግለል ጀመሩ። በግልም በድርጅትም ላይ ነው ጥቃት መሰንዘር የጀመሩት። በሃዋሳ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ መሥራች አቶ ወልደአማኑኤል ላይ  የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል፡፡ አቶ አሰፋ ጫቦና ፊታውራሪ መኮንን ዶሪ፤ የሽግግር መንግስቱን ብስራት ለህዝቡ እናሰማለን ብለው፣ ደብዳቤ ከጠ/ሚኒስትሩ ተፅፎላቸው፣ ወደ ጋሞ ጎፋ ሲሄዱ፣ መኪናቸው የድንጋይ ናዳ ወርዶበታል፡፡ እነዚህ (ኢህአዴጎች) ጠባያቸውን እየቀየሩ የመጡበት አጋጣሚዎችን ማሳያዎች ናቸው፡፡
የኢህአዴግ ትልቁ ችግር የርዕዮተ ዓለሙ መሰረት ነው፡፡ ይሄ ሲስተካከል ብቻ ነው መለወጥ የሚችሉት፡፡ ከማርክሲስት ሌኒኒስት አመለካከት ሲላቀቁ ነው ለውጥ የሚያመጡት፡፡ 21ኛው ክ/ዘመን ምን ይፈልጋል የሚለውን ሲያጤኑና ለውይይትና ክርክር በራቸውን ክፍት ሲያደርጉ ነው በራሳቸው ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉት። አለበለዚያ ግድብ ገደብን፣ ፎቅ ገነባን፣ መንገድ ሰራን ወዘተ — ብቻውን ፋይዳ  የለውም፡፡ የለውጥ ተስፋ የሚኖረው ውስጣቸውን በደንብ ሲፈትሹ  ነው፡፡ በመነጋገርና በመደራደር ማመን ሲጀምሩ ነው የሚለወጡት፡፡ ኢህአዴጎች፤ “እኛ ነን ለዚህች ሀገር ያለናት” የሚለውን መመፃደቃቸውን ትተው፣ “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ በጎ ነገር ይመኛል” ብለው ማሰብ መጀመር  አለባቸው፡፡ “ባለፉት 26 ዓመታት የገነባነው ስርአት አሁንም የህዝብ ጥያቄን ማስቆም አልቻለም ወይም ምላሽ መስጠት አልቻለም” የሚለውን ግምገማ አድርገው፣ የፖለቲካ መስመራቸውን ቢፈትሹ  ሁነኛ መፍትሄ የሚገኝ ይመስለኛል፡፡
የዚህችን ሀገር  የወደፊት እጣ ፈንታ በመወሰን ረገድ የተቃዋሚዎች ድርሻ ምንድን ነው ይላሉ?
የተቃዋሚዎች ድርሻ ህዝብን ማደራጀት ነው፡፡ ያ የተደራጀ ህዝብ ጥያቄ ለመጠየቅ እስኪበቃ ድረስ አብሮ መስራት ነው ያለባቸው፡፡ አንድ የተደራጀ መሪ የሆነ አካል፣ በሌለበት ሁኔታ በአንድ ሀገር ውስጥ ስለ ለውጥ ማሰብ አይቻልም፡፡ የጎበዝ አለቃ ሁሉ ተነስቶ፣ የዘመነ መሳፍንት ሁኔታ ውስጥ እንግባ ካልተባለ በስተቀር የተደራጁ የፖለቲካ ኃይሎች ለህዝቡ አማራጩን ማሳየት አለባቸው። አሁን ከምንግዜውም በላይ ይሄ ነው በጥልቀት መካሄድ ያለበት፡፡ ዝም ብሎ የስርአት መውደቅ ብቻ አይደለም የሚታሰበው፤ በወደቀው ቦታ ማን ነው የሚተካው የሚለው መታሰብ አለበት፡፡ ይሄን ቦታ መተካት የሚችሉት የተደራጁ ኃይሎች ናቸው። የተደራጁ ኃይሎች ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ይህን ነው የ21ኛው መቶ ክ/ዘመን ፖለቲካ የሚፈልገው፡፡
በሌላ በኩል ግን አመራሩን መረከብ የሚችል ጠንካራና ብቃት ያለው ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ የለም የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከህዝብ ጋር ተቀናጅተው፣ ብቃት ያለው እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ፣ እንቅፋት የሆነባቸው አሁን ያለው ሥርዓት ነው፡፡ በሌላ በኩል በከፍተኛ ሁኔታ መስዋዕትነት እየከፈሉ ያሉ ፓርቲዎች፣ በየእስር ቤቱ እየታጎሩ ያሉ የተቃዋሚ መሪዎች— ዕድሉን ቢያገኙ ሃገር የመምራት ሚናን አይወጡም ማለት የተንሸዋረረ አመለካከት ነው፡፡ የ97 ምርጫ እኮ ብዙ ነገር አሳይቶን ነው ያለፈው። በተፈጠረችው ክፍተት የፖለቲካ ፓርቲዎች 6 ወር ባልበለጠ እንቅስቃሴ ነው ብዙ ታሪክ የሰሩት። አሁንም በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት የፖለቲካ አመራሮች፣ ጨርሶ ብቃት የላቸውም የሚለው አመለካከት ስህተት ነው፡፡ ትንሽ ክፍተት ነው የሚፈለገው፡፡
እየተጎሳቆልንም፣ እየተሳደድንም ህዝቡን አደራጅተናል፡፡ ህዝቡ ነፃነቱን የሚያንፀባርቅበት መድረክ ቢፈጠርለት እኮ ብዙ መቀስቀስም አያስፈልገንም፡፡ ስለዚህ ተቃዋሚዎች የት አሉ? ምን ተቃዋሚ አለና? የሚባለው ነገር ጨለምተኛ አመለካከት ነው፡፡ ተቃዋሚዎች አሉ። እየጠበቁ ያሉት መልካም አጋጣሚን ብቻ ነው፡፡
አዲሱ ትውልድ ከሚፈልገው ለውጥ ጋር የሚጣጣም የፖለቲካ እንቅስቃሴ በተቃዋሚውም ሆነ በገዥው ፓርቲ ማምጣት አልተቻለም ብለው የሚያምኑ  ወገኖች አሉ፡፡ እርስዎ ምን ይላሉ?
እኔ አንድ ጥያቄ አለኝ፡፡ ይሄ የኢትዮጵያ አዲሱ ትውልድ፣ ከጨረቃ የወረደ ነው እንዴ? አይደለም። የፖለቲካ ትግል መዳረሻው ዲሞክራሲ ማስፈን ነው፤ ሌላ አይደለም፡፡ አዲሱ ትውልድም በራሱ መንገድ ተደራጅቶ መታገል ይችላል፡፡ እኛም በራሳችን እንታገላለን፡፡ በኔ እምነት ያለችው አንድ ሀገር ናት፡፡ ጥያቄውም አንድ ነው፤ እሱም የዲሞክራሲ ጥያቄ ነው፡፡ የቀረው ሁሉ ትርፍ ነው፡፡ ዝንጀሮ እንዳለችው፤ መጀመሪያ የመቀመጫዬን ነው ነገሩ፡፡ ዋናው ጉዳይ ዲሞክራሲያችንን በትክክለኛ ፈር ውስጥ ማስቀመጥ ነው፡፡ የዘመኑ ትውልድ ከዚህ ውጪ ምንም ሊያደርግ አይችልም፡፡ ተቆፍሮ የሚወጣ ነገር የለም፡፡ የተለየ ጥያቄም አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ ሊግባባ የሚችለው በዲሞክራሲ ብቻ ነው፡፡ ዋናው የኔ አቋም፣ ሁሉም የየድርሻውን ያዋጣ ነው፡፡ እኛም ሆንን አዲሱ ትውልድ የምናዋጣው ተደማሪ ውጤት ለዚህች ሀገር መፍትሄ ያመጣል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙዎችን ስጋት ላይ የጣለ የድንበርና ብሄር ተኮር ግጭቶች እየተከሰቱ ነው? ይሄ አዝማሚያ ወዴት ያደርሰናል? መፍትሄውስ  ምንድን ነው?
የድንበር ጉዳይ ከሰው ልጅ ጋር አብሮ ያለ ጉዳይ ነው፡፡ መሬት ከሁሉም በላይ ዋጋ ያለው እሴት ሆኗል። አሁን የሚታየው አዝማሚያም ከመሬት መስፋፋት ጋር የተያያዘ ነው የሚመስለው። በሌላ በኩል ደግሞ ነገሩን ከብሄር ጉዳይ ጋር እያያያዙት፣ ሁኔታውን ውስብስብ እያደረጉት ነው፡፡ ይሄ  በእጅጉ የሚያሳዝን ነው፡፡ ለምሳሌ የሶማሌና የኦሮሞ ህዝብ፣ በወንድማማችነት አንዱ በሌላው ውስጥ መኖር የጀመረው በኢህአዴግ ዘመን አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ከተፈጠረችበት ጊዜ ጀምሮ ያለ ነው። በህዝቦች መካከል ድንበርን በመስመር ማስመር አይቻልም፡፡
በየዞኑና በየወረዳው የሚፈጠረውን ችግር የሚያነሳሱት ካድሬዎች ናቸው፡፡ ህዝቡ እርስ በእርሱ የተጋመደ፣ ለብዙ መቶ አመታት አብሮ የኖረ ነው፡፡ አሁን እየተፈጠረ ያለው ነገር፣ ለመናገርም የሚያሳፍር እብደት ነው፡፡ ልናፍርበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ እኔ በዚህ ጉዳይ ላይ ምሬት ነው ያለብኝ፡፡ ለዚህም ነው ይሄ ሥርአት አገር ማስተዳደር አቅቶታል፤ ይበቃዋል የምለው፡፡ እንደ ሌላ ሀገር ቢሆን እኮ የአቶ ኃይለማርያም መንግስት፣ በዚህች ምክንያት በገዛ ፍቃዱ ስልጣን መልቀቅ ነበረበት፡፡ ለዘመናት አብሮ በኖረ ህዝብ ላይ ጥቃት የሚፈፀመው እኮ በአስተዳደሩ ውድቀት የተነሳ ነው፡፡ ህዝቡ የህግ ጥበቃ ያስፈልገዋል፡፡ አጥፊዎች በህግ መጠየቅ አለባቸው፡፡
እነዚህ ችግሮች በጊዜ መፍትሄ ካልተሰጣቸው ፌደራሊዝሙ አደጋ ላይ ይወድቃል የሚል ስጋት እየተስተጋባ ነው፡፡ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
ፌደራሊዝም ለሀገሪቱ የአስተዳደር ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ የተቸገርነው ፌደራሊዝምን ከዘረኝነት ጋር እያደባለቁ፤ ህዝብን እያናቆሩ ያሉ ወገኖች በመኖራቸው ነው፡፡ ይሄ ነው ትልቅ ስጋት ውስጥ እየከተተን ያለው፡፡ እኔ የፌደራሊዝም ሥርዓት ላይ ችግር የለብኝም፤ ነገር ግን አሁን ያለው የፌደራሊዝም ሁኔታ እንደገና መፈተሽ ይኖርበታል፡፡ “26 ዓመት ተሞክሯል፤ ምን ተገኘ?” የሚለው ተጠይቆ፣መከለስ ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ዶግማ አይደለም፤ መከለስ ይችላል፡፡ አሜሪካኖች ህገ መንግስታቸውን ከ30 ጊዜ በላይ ከልሰው ነው፣ ጠንካራ ሥርዓት መገንባት የቻሉት፡፡

ለመሆኑ በብርሃን ጸዳል የተሽቆጠቆጠችው፤ ከሀገረ ቻይና እና ከብራዚል ጋር ዓለምዐቀፍ ተሸላሚዋ ዘመነኛዋ ትግራይ ግራጫ ጸጉር አላትን?


By ሳተናውOctober 30, 2017 23:32

 
ከሥርጉተ – ሥላሴ 31.10.2017 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ።/
„ … እንሆም፣ ሁሉ እሾህ ሞልቶበታል፣ ፊቱንም ሳማ ሸፍኖታል፣ የድንጋዩም ቅጥር ፈርሷል።
/ መጽሐፈ ምሳሌ ተግሣጽ ምዕራፍ 24 ከቁጥር 30 እስከ 31/“
እንደ በር።
ሥርጉተ ሥላሴ
ሥርጉተ ሥላሴ
በመጀመሪያ ጥናቱንና መቀነቱን 40 ዐመት ሙሉ በዕንባ ክርትት ለሚሉ ለኢትዮጵያ እናቶች እንዲሰጥልኝ አምላኬን እማጸነዋለሁ። በሥጋ የተለዩትንም ወገኖቼ ሰማዕትነታቸውን ፈጠሪዬ ይቀበልልኝ ዘንድም እማጸነዋለሁ።
በማስከትል … ወደ ዋናው ጉዳዬ ከመሄዴ በፊት ግን የአዋዜ አዘጋጅ ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ የሰሞናቱን የአማራን የተደራጀና የታቀደ ጭፍጨፋ አስመልክቶ የሠራው ዜና እጅግ ውስጥን የተረጎመ፤ ሩቅ አሳቢና መንገድ ጠራጊ ዕድምታ ስለነበረ እጅግ አድርጌ ላመሰግነው ፈቀድኩኝ። ደፋር፤ ጥልቅ ትንታኔ ነው። ቅርብ – ከሩቅ ጥቃትን ያዋደደ ነው። ዓለም – ዓቀፋዊ ሰቅጣጭ የጭካኔ ዕውነታዎችን፤ ሁኔታዎችን በምልሰት የቃኘበት መንገዱ ብጡል ነው። አማራ እኮ ሐገር አልባነቱ ተውጆበታል። የከፈለው ደም ከንቱም ሆኗል። ስለሆነም የአዋዜ የንጽጽሩ የአምክንዮ አቅሙ አንቱ ነው። ለህሊና ቅድመ መሰናዶ ልዩ ተቋምም ነው። ለአማራ ሥነ – ልቦናዊ አኃቲነትም በኲራት ነው። አጭር ግን ልቅም ያለ፤ ልቁን የአማራን ዬዘር ጥፋት ትልም በጥልቀት የመረመረ፤ በስፋት ያስተዋለ፤ በውስጥነት የተቀበለ፤ የጉዳቱ ልክ በአትኩሮት እንዲታይ ፈር ቀያሽ የሆነ – መጸሐፍ ነው። ተባረክ! 

ወይ አረናዎች! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው



  
By ሳተናውOctober 31, 2017 05:48

 
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
የከዚህ ቀደሙን ትተን ሰሞኑን በኢሉባቡር፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ፣ አስቀድሞም በሱማሌ ክልል በበርካታ የአማራና የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ጥቃት ሲፈጸም “ዘር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ነው!” ያላሉና ያላወገዙ፣ ያልተቃወሙ፣ ያልጮሁ፣ ሐዘን ያልተቀመጡ አረናዎች ትናንትና ጀግና ጀግና የነቀምት ወጣቶች በሦስት የወያኔ ሰላዮች ላይ ተገቢ እርምጃ መውሰዳቸውን ተከትሎ ከአሜሪካ ድምፅ እስከ ማኅበራዊው የብዙኃን መገናኛ ድረስ የብዙኃን መገናኛውን ወረው ይዘው ጥቁር በጥቁር ለብሰው ሙሾ እያወረዱ መራራ ሐዘን ተቀምጠዋል፡፡
በዚህ አሳፋሪ ተግባራቹህ እጅግ በጣም እናዝናለን! ይሄ ጠባብነትና ኢፍትሐዊነት ያወረው ድድብናቹህ ብዙ ዋጋ እንደሚያስከፍላቹህ መቸ እንደሚገባቹህ አላውቅም፡፡ ይሄ ድርጊታቹህና አስተሳሰባቹህ “ትግሬ የወያኔ ሰላዮች የፈለጉትን እያደረጉ ኦሮሞን በአማራ፣ ጉምዝን በአማራ….. ላይ እያነሣሡ ያጨፋጭፉ፣ ሥራቸውን እንቅፋት ሳያጋጥማቸው ይሥሩ! ለምን ይነኩብናል?” ማለታቹህ እንደሆነ ይገባቹሀል?
ትግሬ ስለሆኑ ብቻ ምንም ዓይነት ወንጀልና ግፍ ቢፈጽሙም መጠየቅና የሚገባቸውን ቅጣት ማግኘት የለባቸውም ማለት ነው? እኮ ለምን? እንዴት ነው ግን የምታስቡት? ለመሆኑ ጤነኞችስ ናቹህ? እንዴት ብትደፍሩን ነው ግን እንዲህ የታሰባቹህ? እንዴት ደናቁርት ብትሆኑ ነው ግን እንዲህ ያለ የደነቆረ፣ እጅግ ጠባብና ዘረኛ አስተሳሰብ ይዛቹህ እራሳቹህን ለአንድነት፣ ለእኩልነት፣ ለፍትሕ በሚታገልና በቆመ የፖለቲካ ፓርቲ ስም ስትጠሩ የማታፍሩት??? አንድነት እኩልነት ፍትሕ… የሚገባቹህና ለዚህም የቆማቹህ ቢሆን ኖሮ በነቀምት ወጣቶች የተወሰደውን ፍትሐዊ እርምጃ ታደንቁ፣ ትደግፉ ነበር እንጅ አሁን እያደረጋቹህ ያላቹህትን ነገር ፈጽሞ ባላደረጋቹህ ነበር! የነዚህን ሕዝባዊ ፍትሐዊ እርምጃ ለተወሰደባቸው የወያኔ ሰላዮችን ተግባር ደግፋቹሀልና፣ ተባባሪዎችም ናቹህና ነገ እናንተም ላይ ሕዝባዊ የሆነ ፍትሐዊ እርምጃ በተመሳሳይ መልኩ ይፈጸማል!!! ጠብቁ!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!! ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
amsalugkidan@gmail.com

አይነኬ የህወሓት ጀነራሎች!!! በኮንትሮባንድ የሰከሩ፣የደም ገንዘብ!!!


     
      
ክፍልአንድ | / ፂዩን ዘማርያም

ላንባው ተነቃነቀ!!!

የሳኦል መንግሥት ወደቀ!!!


‹‹በፊት በፊት እኛን መመርመር አይቻልም” ያሉ የዘመናችን የመንግስት ተቋማትን አይተናል፡፡ ይሄ እንግዲህ የፖለቲካ አይነኬዎች መፈጠራቸውን ያረጋግጥልናል፡፡ መሬት የዘረፉ እጃቸውን ቸብ ቸብ ተደርገው፣ ተቀጡ ተብለው ወዲያው ይለቀቃሉ፡፡ አንድ ሞባይል የመነተፈ ግን አደገኛ ቦዘኔ ተብሎ ከ2 ዓመት በላይ ይታሰራል፡፡ የፖለቲካ ኃይልና የዘረፋ ኃይል ውህደቱ ከፍተኛ ነው፡፡ “ይሄ የኔ ሰው ነው፤ አትንካው” የሚባልበት የአይነኬዎች ስርአት ነው የምለው ከዚህ አንፃር ነው፡፡›› ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

የህወኃት የጦር አበጋዝ  መንግስት፣“ይሄ የኔ ዘር ነው፤ አትንካው” የሚለውን ወያኔ የኢትዩጵያ ህዝብ ከስሩ መንግሎ መጣል በሃገር የመኖርና ያለመኖር የህልውና ጥያቄ ነው፡፡ ዘውጌኛ የትግራይ፣የሶማሌ ወዘተ ጠባብ ብሄረተኛነት በሰፊ ኢትዩጵያዊ ብሄረተኛነት መተካት አለበት፡፡ በሕወሓት በተቀናበረው ሴራ፣ የሱማሌ የጦር አበጋዞች በኦሮሞ ህዝብ ላይ ያደረሱት አደጋ፣ የሞት፣ የስደት፣ የመፈናቀል፣ የእርስ በእርስ ጦርነት ጥቃቶች አብሮ በኖረው ህዝብ ዘንድ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ ያልፋል፡፡ የወያኔ የፖለቲካ ሴራ ተጋልጦ የሱማሌና የኦሮማ ህዝብ አብረው ይኖራሉ፡፡ የህወኃት ጄነራሎች እነ ጄነራል አብርሃም ወልዴ (ካርተር) በሱማሌ ክልል ውስጥ ስውር መሪዎች በመሆን፣ አብዲ ኢሊ በመሾም  ልዩ የፖሊስ ኃይል በማደራጀት የፖለቲካ አይነኬዎች በመፍጠር  ከሱማሌ የጦር አበጋዞች ጋር ሽርክና መስርተዋል፡፡ የኢኮኖሚ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ በኮንትሮባንድ ንግድ በተለይም በጮት፣ ማእድን ኃብት፣ የቁም እንሰሳትን ወዘተ በድንበር ዘለል ንግድ በማካሄድ የውጪ ምንዛሪ ዶላር በማከማቸት የሃገሪቱን ኢኮኖሚ ተቆጣጥረዋል፡፡ ለዘመናት አብረው የኖሩትን የሱማሌና የኦሮሞ ህዝብ በማጣላት ከሱማሌ ክልል የኦሮሞ ተወላጆችን በብዙ መቶ ሽህ የሚቆጠር ህዝብ ከኖረበት ቀየ እንዲፈናቀል አድርገዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ የእንቢተኝነት ትግልን ለማኮላሸት ህወኃት የጠነሰሰው ሴራ በመሆኑ የመከላከያ ሠራዊቱ ጣልቃ አልገባም፣ እንዲውም ከፍተኛ የኦህዴድ አመራሮች ከግድያ ሙከራ አምልጠዋል፡፡  የህወኃት በትረ ሥልጣኑን የማቆየት አንዱን ብሄር ከሌላው በማጋጨት በተለይም የአማራና የኦሮሞ ህዝብን በማጣላት ስልቱ ከሽፎበታል፡፡ በዚህም የተነሳ የህወኃት የጦር አበጋዞች መንግሥት በምድረ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የሱማሌ የጦር አበጋዞች መንግስት በመፈልፈል የአናሳ ብሄራት ህብረት በመፍጠር፣ ለልዩ ፖሊስ ኃይል መሣሪያ በማሳታጠቅ የኦሮሞ ህዝብ ላይ በማዝመት ታሪክ ይቅር የማይለው በደል በመፈጸም ላይ ይገኛሉ፡፡ በሌሎችም የኢትዩጵያ ክልሎች ተመሳሳይ የጦር አበጋዞች መንግስት፣ በህወኃት መፈጠራቸው አይቀሬ ነው፡፡
{1} የጦር አበጋዝ ማለት የግል ወታደራዊ ኃይል በማደራጀት፣ ለግል ጥቅም ስልጣንና ኃብትን የሚያካብት ተዋናይ ሲሆን በአንድ ሃገር፣ያለው መንግስትና መንግስታዊ መዋቅሮች ጠንካራ ባልሆነበት አካባቢ የሚፈለፈል የጦር አበጋዝ ነው፡፡(ማኪንሌይ፣2007)‘Warlord’ is a term which used to describe a specific period of China’s history but which has re-emerged as a label during the last three decades (MacKinlay, 2007). The definition of a warlord differ, but most authors agree that a Warlord is an actor who accumulate power and wealth for private means by using military force in an environment where the formal state has little or no control (Reno, 1998, MacKinlay, 2007). በኢትዮጵያ ወታደራዊው መንግስት ሲዳከምና በየቦታው ከአማፂያን ጋር ጦርነት ሲገጥም ድንበር ላይ ያሉ ግዛቶች የሚያገናኛቸው መስረተ ልምት መንገድ፣ ባቡር ወዘተ ያልዘመነ በመሆኑ ምክንያት የመንግስት ሥልጣንና ኃላፊነት እየተዳከመ ሲሄድ ቀየው በአካባቢው በሚገኙ የጎሳ የጦር አበጋዞች (የጎበዝ አለቃዎች) ህወኃት፣ሻብያ፣ኦነግ ወዘተ ቁጥጥር ስር ወደቀ፡፡ በዚህም መሠረት በኢትዩጵያ ታሪክ ከ1960 እስከ ከ2010ዓ/ም እስካሁን ያለው አገዛዝ የወያኔ ‹‹ዘመነ-ጦር አበጋዞች  መንግስት›› እንደ አሸን የተፈለፈሉበት ዘመን  እንደሆነ ጥናታዊ ፁሁፉ ያስረዳል፡፡
2} ‹‹የፖለቲካ የማንነት ጥያቄ›› Identities Politics
በአፍሪካ የዘመነ-ጦር አበጋዞች ‹‹የማንነት ጥያቄ›› ዘውጌ ብሄረተኛነት ፅንሰ ሃሳብ ዋነኛና አንገብጋቢ የፖለቲካ ጥያቄ የሆነው ለዚህ ነው፡፡ ዘውጌ ብሄረተኛነት፣‹‹በማህበራዊ ጭብጦች ላይ ሳይሆን፣ በዝርያ፣ በወገን መመሳሰል ላይ የተመሠረተ ብሄርተኛነት››ነው፡፡ (አንዳርጋቸው ፅጌ ገፅ310) በዘመነ-ጦር አበጋዞች በጎሳ፣ በነገድ፣ በዘር፣ በዘውግ፣ በክልል (የደም ግንኙነት፣ የዘር ሃረግ፣ የቌንቌ፣ ወዘተ) ላይ የተከለሉና የተመሠረቱ አንድ ዘርን  በውትድርና በማሠልጠን፣ በማደራጀትና ተዋጊዎች በመመልመልና በሌሎች ዘሮች ላይ በማስነሳት፣የፖለቲካ ሥልጣን ለመጨበጥ የማንነት ጥያቄን ሽሮ መብሊያቸው አደረጉት፡፡ ማርክሲዝም ሌኒኒዝም፣ ማኦይዝም ቀመስ የሆኑ የጦር አበጋዞች በስመ ሶሻሊዝም የብሄር ብሄረሰብን ጥያቄ በማራገብ የጀሌውን ደቀ መዝሙር ህሊና አጠቡት፡፡ የጦር አበጋዞቹ እልፍ አእላፍ ገበሬዎችን በወታደርነት በመመልመልና አንዱን ዘር በሌላው ዘር ላይ ጥላቻ በመቀስቀስ፣ የራሳቸውን ታማኝ ጦር ማደራጀት ቻሉ፡፡ የጦር አበጋዞቹ  የማንነት ጥያቄ ኢንተርፕሬነር ፈላስፎች ሆኑ፡፡

አፈትልኮ የወጣ መረጃ፦ “ስዩም ተሾመን ጨምሮ ሁለት ፀሃፊዎችን ለመግደል ታቅዷል!”



  
By ሳተናውOctober 31, 2017 07:33

 
ስዩም ተሾመ
ስዩም ተሾመ
ይህ “ከከፍተኛ የደህንነት ኃላፊዎች አፈትልኮ ወጣ” የተባለው መረጃ ለመጀመሪያ ግዜ የደረሰኝ ባለፈው ሳምንት ሲሆን የስልክ ቃለ ምልልስ ይህን ማያያዣ (Link) በመጫን ማዳመጥ ይቻላል። በተደጋጋሚ እንዲህ ያለ የማስጠንቀቂያና ማስፈራሪያ ስለሚደርሰኝ ብዙም ትኩረት አልሰጠሁትም። ባለፈው ሳምንት መረጃውን ያደረሰኝ ግለሰብ ትላንትም በድጋሜ ከአሜሪካ በቀጥታ የስልክ መስመር ደውሎ ስለሁኔታው በዝርዝር ገለፆልኛል። ከግለሰቡ ጋር ያደረኩትን የስልክ ቃለ ምልልስ ቀድቼዋለሁ። ሁለተኛውን የስልክ ቃለ ምልልስ ይህን ማያያዣ (Link) በመጫን ማዳመጥ ይቻላል፡፡
ከላይ የቀረቡት የስልክ ቃለ ምልልሶች የድምፅ ጥራታቸው ዝቅተኛ በመሆኑ የቃለ ምልልሱን ዋና ሃሳብ እንደሚከተለው በአጭሩ እገልፃለሁ። ከላይ የተጠቀሰው ግለሰብ ከከፍተኛ የደህንነት ኃላፊዎች እና የኢህአዴግ ባለስልጣናት ጋር ቅርበት እንዳለው ይናገራል። ለምሳሌ፣ ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ፣ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ ሬድዋን ሁሴን እና ከከፍተኛ የደህንነት ሃላፊዎች ጋር በአካል ተገናኝቶ እንደሚወያይ ገልጿል፡፡ ይህ ውስጥ አዋቂ እንደሚለው፣ በሀገሪቱ ወቅታዊ ፖለቲካ ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርጉ፣ እኔን ጨምሮ በሦስት ፀሃፊዎች ላይ “መወገድ አለባቸው” የሚል ትዕዛዝ መተላለፉን ገልጿል። ከላይ ከተጠቀሰው ግለሰብ በተጨማሪ፣ ለደህንነት ሰዎች ቅርበት ያላቸው ሌሎች ጓደኞቼ “ስዩም ተሾመ መወገድ አለበት” የሚለው ውሳኔ መተላለፉን እንደሰሙ በመጠቆም ስጋታቸውን ገልፀውልኛል።
ይህን ከመስማቴ በፊት፣ ትላንት ጠዋት ብዙ የፌስቡክ ጏደኞቼ ከአሉላ_ሰለሞን ገፅ ላይ የተወሰደ ምስል ልከውልኝ ነበር። ከታች እንደሚታየው አቶ አሉላ ሰለሞን እኔ እንድታሰር በይፋ ጥሪ አቅርቧል። ውስጥ አዋቂው “ከአሉላ ሰለሞን ጋር እንዴት ስዩም ተሾመ ይወገድ ትላለህ” ብሎ ለረጅም ሰዓት እንደተከራከረው በመግለፅ ከፅሁፉ በስተጀርባ ያለውን እውነታ፣ በተለይ የአቶ አሉላ ሰለሞን የፖለቲካ አቋም በግልፅ ያሳያል፡፡ በዚህ መሠረት፣ አቶ አሉላ ሰለሞን እንደ እኔ የተለየ አቋምና አመለካከት የሚያራምዱ ግለሰቦችን ያለምንም ጥፋትና ማስረጃ እንዲታሰሩ በይፋ ጥሪ ከማቅረብ ጀምሮ ያለፍርድ “መገደል አለባቸው” ብሎ እንደሚከራከር ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህም ህግ በሰፈነበት አሜሪካን ሀገር ተቀምጦ በኢትዮጲያኖች ላይ የሽብር ወንጀል እንዲፈፀም ጥሪና ቅስቀሳ እያደረገ እንደመሆኑ በህግ ሊጠየቅ ይገባል፡፡

የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በቀለ ገርባን በሰበብ በእስር ለማቆየት የጻፈው ደብዳቤ

የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በቀለ ገርባን በሰበብ በእስር ለማቆየት የጻፈው ደብዳቤ

          
      
(ዘ-ሐበሻ) የተከሰሱበትን የሽብር ወንጀል በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ በዋስ እንዲወጡ የተወሰነላቸው አቶ በቀለ ገርባ ይህ ዘገባ እስከተሰራጨበት ጊዜ ድረስ አልተፈቱም:: ለዋስትና የሚሆነ 30 ሺህ ብር ወዲያውኑ የተከፈለ ቢሆንም የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ለምን እስካሁን እንዳልፈታቸው ሰበብ የያዘ ደብዳቤ ለፍርድ ቤት ጽፏል::
ደብዳቤው ይኸው:-

66

ንግስት ይርጋ በማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣት ገለፀች


Filed under|


ከኢትዮጵያ ሰብ አዊ መብቶች ፕሮጀክት
በእነ ንግስት ይርጋ የክስ መዝገብ ብይን ለመስጠት በሚል በድጋሜ ቀጠሮ ተሰጥቷል
የቃሊቲ ማረሚያ ቤት የፍ/ቤት ትዕዛዝ አላከበረም ተብሏል
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት የሽብር ክስ የቀረበባቸውን የእነ ንግስት ይርጋ የክስ መዝገብ የአቃቤ ህግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሾች የቀረበባቸውን የወንጀል ክስ መከላከል ያስፈልጋቸዋል ወይስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ሊሰናበቱ ይገባል የሚለውን ብይን ለማሰማት ለዛሬ ጥቅምት 21/2010 ዓ.ም ቀጠሮ ይዞ የነበር ቢሆንም፣ ዳኞች መዝገቡን መርምሮ ለመስራት ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገናል በሚል በድጋሜ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡
አክቲቪስት ንግስት ይርጋን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾችን የያዘው የእነ ንግስት ይርጋ መዝገብ ነሐሴ 12/2009 ዓ.ም ለብይን በሚል ቀጠሮ ከተያዘ በኋላ ብይኑ አልደረሰም በሚል ለዛሬ ተላልፎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ሆኖም ግን ዛሬም መዝገቡ ተመርምሮ ብይኑ ባለመሰራቱ ለሁለተኛ ጊዜ ለህዳር 01/2010 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ቃሊቲ ማ/ቤት የምትገኘው አክቲቪስት ንግስት ይርጋ በእስር ቤት የጥየቃ ሰዓትና የጠያቂ ገደብ ተጥሎብኛል የሚሉና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አቤቱታ አቅርባ ይህ እንዲስተካከል ፍ/ቤቱ ለቃሊቲ ማ/ቤት አስተዳደር ትዕዛዝ ሰጥቶ የነበር ቢሆንም ማ/ቤቱ ትዕዛዝን አለማክበሩ ተገልጹዋል፡፡
‹‹ሐምሌ 21/2009 ዓ.ም ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቶልኝ ነበር፡፡ ሆኖም ማ/ቤት አስተዳደሩ የፍ/ቤቱን ትዕዛዝ አክብሮ መብቶቼን ባለማክበሩ በድጋሜ ነሃሴ 12/2009 ዓ.ም አቤቱታ አቅርቤ፣ ለዛሬ ማ/ቤት አስተዳደር ለምን ትዕዛዙን እንዳላከበረ መልስ እንዲሰጥ ታዝዞ ነበር፡፡ ይባስ ብሎ በማ/ቤቱ አስተዳደር ቢሮ እየተጠራሁ ‹አንቺ ማን ስለሆንሽ ነው ማ/ቤቱን የምትከሽው፣ አንቺ ከማን ትበልጫለሽ እየተባልሁ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠኝ ነው›› በማለት ንግስት ይርጋ ስላለው ሁኔታ አቤቱታ አሰምታለች፡፡
ሌሎችም ተከሳሾች አቤቱታ እንዳላቸው ቢገልጹም ፍ/ቤቱ አቤቱታቸውን በጽሁፍ ካቀረቡ ብቻ እንደሚቀበላቸው በመግለጽ እንዳይይገሩ ከልክሏል፡፡
ፍ/ቤቱ የቃሊቲ ማ/ቤት አስተዳደር ቀደም ሲል በንግስት ይርጋ አቤቱታ ላይ የተላለፈውን የፍ/ቤቱን ትዕዛዝ ለምን እንዳላከበረ በቀጣይ ቀጠሮ ቀርቦ እንዲያስረዳ በድጋሜ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡


Monday, October 30, 2017

የወያኔ “ዕዉራን” ምሁራን የሚጠነስሱት ሴራ


ቢንያም ሙሉጌታ ከኖርዌ




የወያኔ ህወሃት ባለስልጣናት የኛ የሚሏቸውን የትግራይ ምሁራንና ካድሬዎቻቸውን
ብቻ ለይተው ለመጥቀም እንዲሁም ሌላኛውን ለመጉዳትና ለማሸማቀቅ ላለፉት 26
ዓመታት በሁሉም ኢትዩጵያዊ መታወቂያ ላይ ዘር እንዲጠቀስ በማድረግ ከፍተኛ
የሆነ አገርን የማፍረሻ ቫይረስ ሲረጩ ቆይተዋል።
ይህ ህወሃት ወያኔ የረጨው የዘር ቫይረስ የትግራይ ህዝብ ሙሉ በሙሉ
እንደተስማማው እርግጠኛ መሆን ባይቻልም ነገር ግን ትግራይ ውስጥ ምንም
አይነት ተቃውሞ የማይሰማው አንዳንድ የትግራይ ፀሀፊዎች እንደሚሉት በትግራይ
ብዙ ጭቆና አለ በትግራይ የሌለውና የጠፋው ጭቆናውን የሚያጋልጥ ነው እያሉ
ሲሉ እንሰማለን። ሆኖም ግን ሌላው ኢትዩጵያዊ በወያኔ ህወሀት ቀንበር ተጭኖበት
ሲገደል ሲታሰር ብዙ በደል ሲፈፀምበት የትግራይ ህዝብና ምሁራን ዝምታ የተለመደ
ነው።
ህወሀት ወያኔ በመታወቅያ ወረቀት ላይ የጠመደው የዘር ፈንጂ ሌላውን ኢትዮጵያዊ
እያጠፋ እየበታተነ እየከፋፈለ እንዳለ የትግራይን ህዝብና ሙሁራን እንደሚያቁ
ግልፅ ነው። ገዢው ፓርቲ ኢትዩጵያን በዘር የመከፋፈል ክፉ አጀንዳ ብዙዎችን ዋጋ
አስከፍሏል። በቅርብ ግዜያት እንኳን ብዙ ታዝበናል። በጉራ ፈርዳ የአማራ
ተፈናቃዮች ከ20 ዓመታት በላይ ከኖሩበት መሬታቸው አማራ ስለሆናችሁ በዚህ ክልል
መኖር አትችሉም ተብለው ተፈናቅለዋል እንዲሁም በኦሮሚያ እና ሶማሊያ አካባቢ
ህወሀት ወያኔ ሆን ብሎና አቅዶ የእርስበርስ ግጭት በመፍጠር በሁለቱም
አካባቢዎች የሚገኝ በብዙ ሺህ የሚቆጠር ዚጎቻችን ህይወታቸውን ንብረታቸውን
አጥተዋል። ለዘመናት ከኖሩበት የመኖርያ አካባቢያቸውም ተሰደዋል።
ወያኔ ህወሀት እንደዚህ የመሳሰሉ የእርስ በእርስ ግጭቶችን በብዙ ኢትዩጵያ
አካባቢዎች ላይ ተግባራዊ አድርጓል እያደረገም ነው። አሁን ግን ግጭቱም በማንና
ለምን እንደሚፈፀም ሁሉም ኢትዩጵያዊ ጠንቅቆ ተረድቶታል። ይህ አምባገነን ገዢ
በሀገሪቱ ላይ ያለው የህዝቦች አንድነት፣ሰላም እና መግባባት እንዲቀጥል ፈፅሞ
አይሻም። ለምሳሌ በኦርቶዶክስ ሀይማኖት በየገዳማቱ ላይ እያደረሰ ያለው ጥቃት እና
በሀይማኖቱ መሪዎች መካከል በጳጳሳቱ እንዲሁም በሊቀ ጳጳሳቱ ብሎም በሲኖዶሱ
መካከል ሰርጎ በመግባት ሀይማኖቱን ለማበጣበጥ እና ለመከፋፈል ባደረገው
እንቅስቃሴ አሁንም ድረስ ህዝበ ክርስቲያኑን እንዳሳዘነ እና እንዳስቆጣ ይገኛል።
በየእምነት ተቋማቱ ውስጥ ወያኔ እጁን በማስገባት ችግር ፈጣሪዎቹ እነሱ
መሆናቸው እየታወቀ መፍትሔ አፈላላጊ አካል ነን ብለውም ከፊት የሚቆሙት
ራሳቸው ናቸው። በኢትዩጵያዊው ሙስሊሙ ህብረተሰብ ውስጥ አክራሪነትንና
ሽብረተኛነትን ለመዋጋት በሚል የይስሙላ ፖሊሲ ነድፈው ሙስሊም ህብረተሰብን
ለመከፋፈል ለመበታተን ለማጋጨት ብዙ ደክመዋል። በእነዚህና መሰል ብዙ
ቀውሶች ወቅት ከትግራይ ተወላጅ ሙሁራን የአገዛዙን የተዛባ ፍትህ የሚያወግዝ
ድምፅ እረጭ ፀጥ ማለቱ ያሳዝናል። ከፋሺስት ወራሪ ጦር ኢትዩጵያ ሀገራቸው
ለመታደግ የተዋደቁት ቀደምት የትግራይ ተወላጆች አጥንት ይወቅሳቸዋል። የፈሰሰ
የደማቸውም ጩኽትም ከተኙበት ወያኔያዊ አዚም ያነቃቸው ዘንድ እመኛለሁ።
አምባገነኑ የትግራይ ወያኔ በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ያለው ግልፅ የሆነ ደባ ከዚህ
በኋላ ሊቆም ይገባል። ሀገሪቱን እንደነ ዮጎዝላቪያ፣ሶማሊያ፣ሩዋንዳ እና ሶሪያ
ለመበታተን አንግቦ የተነሳውን አጀንዳ ማስቆም የግድ ነው። ይህንን አምባገነን
ሰይጣናዊ ስርዓት በጊዜ ካለመወገዱ የተነሳ ለአዲሱ እና ተተኪው ትውልድ ተሻጋሪ
ጥፋትና ቀውስ ፈፅሟል። በአማራው፣በጋምቤላው በኦሮሞው በአፋሩ በተቀረው
ኢትዮጵያዊ ላይ እያነጣጠረ በመፈፀም ላይ የሚገኘው ጥቃት ፈተናውና መዘዙ
ውሎ አድሮ የኋላ ኋላ ለራሱ ለትግራዮም ተወላጅ መትረፉ የማይቀር ነው።
የኢትዮጵያ መከራ እንዳያበቃ በማድረግ እና የህወሀት ወያኔ መሪዎችን እድሜ
የሚያረዝመው ዘረኝነት ህሊናቸውን ያሳወራቸው የትግራይ ዕዉራንምሁራን
የሚጠነስሱት ሴራ የበለጠ ሀገሪቱን ወደ ውስብስብ ችግር ውስጥ እየከተተ ይገኛል።
እነዚሁ ህጋዊ የሆኑ ዘራፊ ቡድኖች የሀገሪቱ ሀብት ምዝበራ ላይ በዋና ተጠቃሚ
ስለሆኑ ስለሚፈጠረው ቀውስ እና ስለ ነገይቱ ኢትዮጵያ ምንም አይገዳቸውም።
እነርሱ የሚረጩት መርዝ ብዙ ታማሚዎችንም አፍርቷል። ዛሬም ህልማቸው መዋለ
ንዋይ ብቻ ነው። መዝረፍ ማድከም ባዶ ማድረግ አላማቸው ነው። የትግራይ ህዝብ
ከወያኔ ጋር አብረው ኢትዮጵያዊነትን የሚያፈርሱ ዘረኝነትን የሚያስፋፉ
በመሆናቸው ታሪክ ይፋረዳቸዋል።
በአሁን ወቅት ገዢው ፓርቲ ከግብር አበሮቹ ጋር በመሆን ኢትዮጵያዊነት ትርጉመ
ቢስ ደረጃ ያደረሱት መስሎ ቢሰማቸውም፤ ኢትዮጵያዊነት ግን በደም ውስጥ ያለ
የማይቀየር ማንነት ነው። በህወሀት ወያኔ እና በትግራይ ዕዉራን ምሁራን ጥምረት
የሚመራው የዘር ማጥፋትና ኢትዮጵያዊነትን ማፅዳት ዘመቻ የረዘመ ዘመን
ያስቆጠረ መሆኑ ግልፅ ቢሆንም፤ገና የትጥቅ ትግል ሲጀምር ኢትዮጵያዊነትን
ማዳከም አማራውን እና ኦሮሞውን በማጣላት ማህበራዊ ህይወቱንም ማናጋት
አጀንዳው ነበር። ይህንን በሀገሪቱ ላይ ለ26 ዓመት በአምባገነንነትና በዘረኝነት
ስልጣንን ለብቻው በመያዝ የሚገዛው ወንበዴ ቡድን ማንና ምን እንደሆነ
ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ጠንቅቆ ስለተረዳው በተባበረ ክንድና በአንድ ኢትዯጵያዊት
የሚያምን ሁሉ ከፊት ለፊቱ ያለውን ሀገር አድኑን ተጋድሎ እየተባበረ ወያኔ ህወሀትን
የሚማርክበት ዕዉራንምሁራን ትግራዮችን የሚስቆምበት ወሳኙ ጊዜ አሁን
ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!