Sunday, July 31, 2016

የወያኔ የጎሳ ፖለቲካና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የተዋረደበት ህዝቡ አገዛዙን መጥላቱን ሕዝብ ያስመሰከረበት ሰልፍ ተካሄደ


እናቶች በሰልፋ ለደከሙ ወጣቶች ውኃ እያቀረቡ ነው፤ የሃይማኖት አባቶች ተጋድሏችንን እየባረኩ ነው! አማራነት እኮ እንዲህ ነው! እቴጌ ባአድዋ ያደረጉትን አስታውሱ!
የወያኔ የጎሳ ፖለቲካና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የተዋረደበት ኣገዛዙን መጥላቱን ሕዝብ የመሰከረበት ሰልፍ
ፖለቲከኞችን ያሳፈረው ሕዝብን ያነገሰው ዛሬ በጎንደር የተካሄደው ሰልፍ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል ሂደት ውስጥ ራሱን የቻለ ጫና እንዳለው ያረጋግጣል።ሕዝብ በራሱ ያሰናዳውና የተሳካ ታላቅ ሰልፍ በጎንደር ደሞቆ ውሏል።ሕዝባዊ ኣንድነት ጎልቶ የታየበት የወያኔ የጎሳ ፖለቲካና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የተዋረደበት ኣገዛዙን መጥላቱን ሕዝብ የመሰከረበት ሰልፍ ነበር፤የሕወሓት ኣገዛዝ በቃኽን የተባለበትም ሰልፍ ነው፥ ሚሊዮኖች ኣደባባይ ወጥተው ወያኔን ልክ እንደሚያስገቡት ነግረውታል።
Minilik Salsawi's photo.
ሕዝብን በሃይማኖት ለመከፋፈል ሞከሩ ኣልተሳካም። ሕዝቡ ሃይማኖታችንን እንደያዘን የሌላውን ኣክብረን ቤታችን በታቸው ሆኖ የኣንዱ ደስታና ሃዘን የኣንዳችን ሆኖ በተሳሰረ የኢትዮጵያዊነት ሰንሰለት ላይፈታ ታስሯል ብሎ በተደጋጋሚ እያረጋገጠ ነው። የብሄረሰብ መብት ሽፋን በሚል ኣንዱን ጨቋኝ ሌላውን ተጨቋኝ ኣድርጎ ለማቅረብ ቢሞክርም ሰሚ ጆሮ ኣላገኘም ወያኔከኦሮሞ ሕዝብ ጎን መቆሙን ኣማራው በተግባር በሚሊዮኖች ድምጹ ኣረጋግጧል፤ በሕዝብ ዘንድ ጥላቻና ዘረኝነት እንዳሌለ የጎንደሩ ሰልፍ ለገዢዎች ኣሳይቷል። ችግሩ ወያኔና ፖለቲከኞቹ እንደሆኑ እንጂ በሕዝቦች መካከል ችግር እንደሌለ ኢትዮጵያዊነት እንዳስተሳሰረ በተግባር ከመመስከሩም በላይ የወያኔን ባንድራ ተቀባይነት እንዳሌለው ታይቷል በጎንደሩ ሰልፍ።

የጎንደር ህዝብ ቃሉን ጠብቆ አደባባይ ወጥቷል።


የጎንደር ህዝብ ቃሉን ጠብቆ አደባባይ ወጥቷል። (የጎንደር ዘገባ)
የጎንደር ከተማ በሰላማዊ ሰልፈኞች ተጥለቅልቃለች ሕዝቡ ወደ መስቀል ኣደባባይ መጓዙን ይዟል ። የሕወሓት ወታደሮችና ፖሊሶች በግርምት ኣፍጥጠው እያዩ መንገድ እየዘጉ ሰልፈኛውን ለመቁረጥ ጥረት እያደረጉ ነው። ፤በፍርሃት እንዳይወጣ እያደረጉት ያለው ሕዝብ በልበሙሉነት ኣደባባዩ በሚሊዮኖች እየሞላ ነው፤የኢንተርኔት ኣገልግሎት ኣይሰራም።
የወልቃይት ጉዳይ የኣማራና የኣማራነት ማረጋገጫ እንደሆነ በተግባር እየታየ ነው። አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ ይሄ ባንዲራ ያንተ አይደለም ወይ በሚለው ከፍተኛ ጩሀት ያሰማል የክልሉ ፓሊስ ከህዝብ ጋር ሙሉ ለሙሉ ተቀላቀለ አንድነት ሀይል ነው ህዝብ ሀይል ነው።ሁለም አቅጣጫ በተለይም በፒያሣ አካባቢ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሠልፋ ታዳሚ በመፈክሮችና በቀሥቃሽ ሙዚቃዎች ታጅቦ ወደ መሥቀል አደባባይ እየተመመ እንደሚገኝ የሠልፋ ተሣታፊ ከሥፍራው ነግሮኛል።ከኦሮሞ ሕዝብ ጎን መቆሙን ኣማራው በተግባር በሚሊዮኖች ድምጹ ኣረጋግጧል፤ በሕዝብ ዘንድ ጥላቻና ዘረኝነት እንዳሌለ የጎንደሩ ሰልፍ ለገዢዎች ኣሳይቷል። ችግሩ ወያኔና ፖለቲከኞቹ እንደሆኑ እንጂ በሕዝቦች መካከል ችግር እንደሌለ ኢትዮጵያዊነት እንዳስተሳሰረ በተግባር ከመመስከሩም በላይ የወያኔን ባንድራ ተቀባይነት እንዳሌለው ታይቷል በጎንደሩ ሰልፍ።
የአማራ ክልል ልዩ ሀይል ከሥፍራው እንደሌሉ እና አጋዚ ግን ከትናንት ጀምሮ ቢኖርም ህዝቡ ፍጹም ጨዋነት በተሞላበት ሠላማዊ መንገድ የሠልፉን ግብ ልማሣካት እርብርብ ላይ መሆናቸውን ለማወቅ ችያለሁ።
ሰልፋን እየመሩት የሚገኙት የሀይማኖት አባቶች(የክርስትያኑ እና የሙስሊሙ) ሲሆኑ ምንም የሌለው የኢትዬጽያ ባንዲራ እየተውለበለበ ይገኛል፡፡ በዚ ሰዓት አንድም ፌደራል አይታይም፡፡ አሁን የሚሰማኝ ስሜት ልክ አባቶቻችን ጣልያንን ሲያሸንፉ፤ ልክ እንደ አድዋ ድል በማለት ደስታውን ገልፆልኛል፡፡ በቦታው ኮረኔል ደመቀ የላከው መልክት ሊነበብ እንደሆነም ገልፆልኛል፡፡
በአደራ የሰጠናችሁን ልጃችን ኮለኔል ደመቀ ዘውዱን መልሱልን!
በግፍ የታሰሩ የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በአስቸኳይ ይፈቱ

Saturday, July 30, 2016

የወያኔ መንግስት እስረኞችን ለማሰቃየት በቃሊቲ እስር ቤት 4 የጨለማ ክፍል እንዳሰራ ታወቀ ።


የወያኔ መንግስት እስረኞችን ለማሰቃየት በቃሊቲ እስር ቤት 4 የጨለማ ክፍል እንዳሰራ ታወቀ ።
የወያኔ መንግስት በእስር ቤት ያሉትን የፖለቲካ እስረኞች ለማሰቃየት በቃሊቲ እስርቤት ውስጥ 4 የጨለማ ክፍሎችን እንዳስገነቡ ምንጮቻችን ዘገቡ ።
ከዚህ በፊት በቃሊቲ እስርቤት ውስጥ ጨለማ ክፍል ስድስተኛ ተብሎ በሚጠራው ቦታ አንድ ብቻ የነበረ እና እሱን አፍርሰው በአሁኑ ሳአት 4 ክፍል በመገንባት በእስረኞቹ ላይ ከፍተኛ ስቃይ እና እንግልት ለማድረስ በቁርጠኝነት መነሳቱ የሚያሳይ ነው ።
አሁን በአዲስ መልክ የተገነባው የጨለማ ክፍል እያንዳዱ 36 ሰዉ እንደሚያዝ ለማወቅ ተችሎዋል ።
በተያያዘ ዜና በቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙ በፖለቲካ እስረኞች ላይ የሚደረገው ጫና እንደቀጠለ ሲሆን ከትላንት ጀምሮ ከእናት አባት እና ልጅ ውጭ የትኛውም ዘመድም ሆነ ወገን እንዳይጠይቃቸው እንደተከለከሉ ምንጮቻችን ከስፍራው ዘገቡ ።
መላው ማህበረሰብ በጨቁዋኙ በወያኔ መንግስት ላይ በአንድነት በመነሳት ጭቆናን እንዲታገሉ ጥሪ ቀርቦዋል ።

ሦስቱን መንግስታት በንጽጽር (ንጉሱ- ደርግ-ኢህአዴግ) – አሰፋ ጫቦ



Addis Admass ከአዘጋጁ፡- ለአቶ አሰፋ ጫቦ በቃለ-መጠይቅ መልክ በኢሜይል ከላክንላቸው በርካታ ጥያቄዎች ውስጥ ለአራቱ
የሰጡትን ምላሽ ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ ሰሞኑን ደግሞ፡- “ሦስቱን መንግስታት በንጽጽር እንዴት ይገልጹዋቸዋል?” በሚል
ለላክንላቸው ጥያቄ፣ አስፋፍተውና በመጣጥፍ መልክ ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ በአንድ ጊዜ ለማስተናገድ ብዙ በመሆኑ በሁለት
ክፍል እናቀርበዋለን፡፡ የመጀመርያው የመልሱን ክፍል እነሆ፡-
“ያለፍክባቸውን ሶስቱን መንግስታት በንጽጽር እንዴት ትገልፃለህ?”
የሚለው በጣም ከባድ ጥያቄ ይመስለኛል። ዘርዘር ባደርገው ጋዜጣው በቂ ቦታ አይኖረው ይሆናል ብዬ ፈራሁ። ሰብሰብ ያደርኩ እንደሁ ደግሞ ከመልስ ይልቅ ተጨማሪ ጥያቄዎች የሚጋብዝ ይሆናል ብዬ ፈራሁ።  እስኪ መጠነኛ፤ መሀል መንገድ ፈልጌ ለማትኮር እሞክራለሁ።
ለዚህም ሁለት አብይትና ገላጭም ናቸው ብዬ የምገምታቸው ነጥቦች ላይ አተኩራለሁ። የመጀመሪያው እነዚህን 3 መንግስታት፤ ማለትም የንጉሰ ነገስቱን፤ የኢትዮጵያ ሕዝባዊት ዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ (ኢሕድሪ (ደርግ) እና አሁን በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት እንደ ሥርዓተ-መንግሥት (System of Government) ምን ይመስላሉ የሚለውን ቀንጭቦ ማየት ይሆናል። ሁለተኛው እነዚህን መንግሥታት በቁልፍነት ሲያሽከረክሩና  አድራጊ ፈጣሪ የነበሩትን  ግለሰቦች፣ ማለትም፣ ኃይለሥላሴን፤ መንግስቱ ኃይለ ማርያምንና መለሰ ዜናዊን ለማየትና ለማሳየት መሞከር ይሆናል። እንደ አጋጣሚ ሆኖ ሶስቱንም በቅርብ የማወቅ፤ አብሮ የመስራት፤ ከዚያም ፈግጠው-ፈግጠው ተባብለን ተለያይተናል። በቅርብ ርቀት (የቅርበት-ርቀቱ መጠን ቢለያይም) ሰብእናቸውንም የማየትና የመታዘብ እድል ነበረኝ። ይህ የዐይን ምስክርነቴ ለምለው ተጨማሪ ምንጭም ሆኖ ያገለግላል የሚል እምነት አለኝ። በፈግጠው ፈግጠው ጉዳይ፣ እኔ ውድ ዋጋ ከፍያለሁ። እየከፍልኩም ነው። ”… ወትሮም መንገደኛ ፊትና ኋላ ነው” የሚሉት ሆኖ እንጅ እነሱም ከፍለዋል። እርግጥ የእጁን ያላገኘው መንግስቱም አለ።
ሕገመንግሥት
የማንኛውም አገር ሥርዓተ-መንግስቱ መግለጫ ሕገመንግስቱ ነው። ሕገመንግሥት ማለት አንድ አገር የሚገነባበት ጽኑ መሠረቱ፤ ጣራውን ተሸካሚ አስተማማኝ ግርግዳውና፤ ደመና ዞር ባለው ቁጥር፣ ብርድ፤ ፀሐይ ብቅ ባለች ቁጥር፣ ሙቀት የማያስገባ፣ የረጋና የተረጋጋ ጣሪያ ያለው ጽኑ አዳራሽ እንደ ማለት ነው። እዚያ ታላቅ አዳራሽ ውስጥ ነው ክፍሎቹ እንደ ቤተሰቡ ዕውነት የሚከፋፈሉትና የሚደላደሉት:: ሕገመንግስትን መሠረታዊ ህግ፤ የሕጎች ሁሉ ምንጭ (እናት) (Basic Law,Fundamental Law) ይሉታል። ነውም! ስለሆነም፤ በሕገመንግስቱ ብንጀምር የሚሻል ይመስለኛል።
በንጉሱ ሕገ መንግስት (1948 ዓ.ም) እንጀምር። ይህም “የተሻሻለው የ1948 ዓ.ም ሕገ መንግስት” ተብሎ የሚጠራው ነው። ይህ ሕገመንግስት አብዛኛው ህዝብ ከማያውቀው ታሪክ፣ ሌላም ታሪክ ከኋላው አለ። ንጉሱ፤ “ለምንወደዉና ለሚወደን ሕዝባችን በራሳችን ፈቃድ ተነሳስተን ሰጠነው” እንደሚሉት አይደለም። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውሳኔ የፈደራል አክት (The Federal Act 1952) የሚባል አለ። ይህም ኤርትራን ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን ለማገናኘት የተባበሩት መንግስታት ውሳኔ ነበር። በአለም አቀፍ የሕግና የፖለቲካ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ሕገ መንግስት አለ። ፌዴሬሽኑን ለመቀበል ይህንን የፌዴራል አከት መቀበል እንጅ አማራጭ አልነበረውም። ኢትዮጵያ ያኔ የነበራት የ1923 ዓ.ምቱ፤እጅግ ኋላቀር ሕገ-መንግስት ነበር። የፌዴሬሽኑ ርእሰ ብሔር ደግሞ ንጉሱ ሊሆኑ ነው። ስለዚህም ኤርትራን 25 ዓመት (1948-1923) ወደ ኋላ ከመውሰድ፣ ኢትዮጵያን 25 አመት ወደፊት መጎተት ይሻላል የሚል እርቅ ሃሳብ (Compromise) መሆኑ ይመስለኛል። ሌላው ቢቀር በወረቀት ላይ እንኳን ቢሆን ጎተት እናድርጋት እንደ ማለት ነው።
ቁልፉና ተፈላጊው ነገር ኤርትራን በዚህም ይሁን በዚያ ወደ እናት አገሯ መመለሱ ነበር፡፡ ብዙም ሳይሰነብት ኤርትራን ለዚህ ያበቃው ዘር መዘራት ተጀመረ። ይህ ያልተጣጣመም፤ ፈላጭ ቆራጭ ንጉስ ነገስትና ዘመናይ የሆነው የኤርትራ ሕግ አብሮ አለመሄድ፤ የፌዴሬሽኑ ማፍረስና መፍረስ መነሻ ምክንያቶች ሆኑ። እርግጥ አባባሽ የሆኑ ሌሎችም ምክንያቶች፣ ሰበቦች ሞልተዋል። ከመጀመሪያውም ቢሆን፣ ይሁን-ይሁን ተብሎ እንጅ ሁለንተናው ሲታይ የፌደራል መለኪያዎች አያሟላም ነበር የሚሉ የሕግም የፖለቲካም ምሁራን አሉ።
ከዚህ፤ 131 አንቀጽ ከነበረው ከ1948 ዓም ሕገመንግስት ውስጥ 35ቱ የንጉሰ ነገስቱን ዝርያና ውርስ፣ ስልጣን የሚናገር ነው። ከዚህ ውስጥ አንዱ አንቀጽ የያዘው፣ ዘውድ በሳባ በኩል ከአይሁዱ ነገሥታት ከዳዊትና ከሰለሞን ሳይቋረጥ የመጣ፣ ኃይለስላሴም የዚያ ዝርያ ስለሆኑ ከእርሳቸው ዝርያ ለዘለዓለም አይወጣም የሚል ነው። እንዲህ ሲያዩት የሚገርም ነው። እኔን ይገርመኛል። መጀመሪያ ለስላሴ ኦሮሞ ናቸውና እዚህ ስለ ንግስት ሳባ ከሚወራው ትንግርት ውስጥ (እውነትነት ቢኖረው እንኳን) የሚያገባቸው ነገር ያለ አይመስለኝም። ከሁሉም በላይ ግን ኃይለስላሴ፤ ይህንን እስከ ወዲያኛው ሊያደርስ የሚችል፤ የሚመኙትን ዘውድ የሚያጓጉዝ አልጋ ወራሽ አልነበራቸውም። አልጋ ወራሽ የተባሉት አንደበታቸው ተይዞ አውሮጳ ለሕክምና ከሔዱ አመታት አልፏል። ንጉሱ መጃጀታቸው ደግሞ የአደባባይ ሚስጥር ነበር። ለሁሉም ለሁሉም በ1966-67 የኃይለ ሥላሴም ሆነ የዝርያቸውም መጨረሻ እስከ ወዲያኛው ሳይሆን ከርቸሌ እንደነበረ ያየነው ወይም የሰማነው ነው።
ያም ሆኖ የዚህ ህገመንግስት ገላጫ ባህርዩ አንዱና ቁልፉ ኢትዮጵያን እንዴት እንደሚያስቀምጥ ነው። “ኢትዮጵያ ማለት ምድሪቱ፤ ባህሩ፤ ደሴቶቹና ከላይ የከበበው ሰማይ ጭምር ነው” ይልና ይህ የማይደፈርና የማይቆራረስ ነው ይላል። ስለዚህም  ኢትዮጵያ  ማን እንደሆነች፤ የት እንደምትገኝ፣ ምኑና ምኑ ተሰባስቦ፣ ወጥና አንድ ኢትዮጵያ እንደሚያሰኛት በማያጠራጥር፤ በማያሻማ ቋንቋ ተጽፎ ተቀመጧል። ይህም አይደፈርም አይገሰስም ይላል።
የደርግ ሕገመንግሥት፤ኢትዮጵያ የሶሺያሊስት አገር መሆኗን በማያሻማ ቋንቋ አስቀምጧል። ዛሬ ነፋሱን ተከትለንም ሶሺያሊስት፤ ካህኑ፤ አጥማቂው ጭምር የነበርነው ሁሉ “እኔኮ! ነገር ግን…!” ማለት ጀምረናል። እዚያ ውስጥ አልገባም። ከሐዲዎቹ ያላስተዋልነው ነገር ቢኖር አብዛኛው የምዕራብ አውሮጳ አገሮች በተለይም እስካንዲኔቪያ (Scandinevia) የሚባሉት ወይ ሶሺያሊስት ወይም የዚያ ጥምር መሆናቸውን ነው። ለምሳሌ የአሁኑ፤ የዛሬው፤ የፈረንሳይ መንግስት ሶሺያሊስት ነው። ይህ ደግሞ ወደ መቶ ዓመታት የሚጠጋ ታሪክ አለው።
የደርግ መንግስት፤ የኢትዮጵያ ማንነት ልክ የንጉሱ መንግስት ሕገመንግሥት ያለውን በተጠናከረ መልኩ ይደግመዋል። ኢትዮጵያ ነጻ የማትደፈርና የማትከፋፈል ነች ይላል። ሌላው የደርግን ሕገ መንግሥት ለየት የሚያደርገው፣ ይህ መንግስት የተመሠረተው ለነማን፤ በነማን እንደሆነ ይዘረዝራል። ይህም ዝርዝር “የሠርቶ አደሩ፤ የገበሬው፤ የምሁራን፤ የአብዮታዊው ሠራዊት፤ የእጅ ሠራተኞችና የተቀሩት የዲሞክራቲክ ኃይሎች መንግስት ነው !” ይላል። እዚህ ዝርዘር ውስጥ ያልገባ ቢኖር፤ “ሳይሰራ የሚባለው!” ነበር። ማለትም፤ ደርግ በዝባዥና አቆርቋዥ የሚላቸው መሆናቸው ነው። ደርግ ዛሬ ከመቃብሩ ቀና ብሎ ቢያይ “ምነው!?  ስምንተኛው ሽህ ገባ እንዴ!?” ሳይል የሚቀር አይመስለኝም፡፡
አሁን ደግሞ በሥራ ላይ ያለውን የኢህአዴግን ሕገመንግሥት ለማየት እንሞክር። ለመንደርደያ ያክል ይህንን ሕገመንግሥት ያረቀቀው፤ “ዶክተር” ፋሲል ናሆም መሆኑን መግለጹ ጥሩና አስፈላጊም ይመስለኛል። CONSTITUTION FOR A NATION OF NATIONS ,The Ethiopian Prospect የሚል መጽሐፍ ጽፏል። መጀመሪያ ነገር ይህ መጽሐፉ የኢትዮጵያ ሕገመንግሥት አይደለም። ለመንግሥቶች መንግሥት የወጣ ሕገመንግሥት ይለዋል። ትርጉሙ ግልጽ አይደለም። ለኔ ግልጽ አይደለም! ብቻ በዚህ ሕግ መንግስት፤ እንደ ፋሲል ናሆም አባባል፤ አቀራረብ ኢትዮጵያ የመጽሐፉም፤ የሕገመንግሥቱም ዋና ተዋናይና እምብርት አይደለችም እንደ ማለት ነው። ተለጣፊ መሆንዋ ነው። PROSPECTS  የሚለው ቃል ትርጉም ይኸውና፤ prospect,noun ,the possibility or likelihood of some future event occurring.” ምናልባት ሊሳካ ይችላል ማለት ነው። ምናልባት ሊሳካ የሚችለው ምኑ ይሆን? አልነገረንም! የሚጽፈው ስለ ኢትዮጵያ ስለሆነ ኢትዮጵያ፤ እንደ ኢትዮጵያነትዋ ላትሳካ ትችላለች ማለት ይሆን? ይህም የሚያስኬድ ትርጉም ይመስለኛል። ሌላው፤ወያኔ ይህንን የማይመስል ነገር ተግባራዊ ማድረጉ አይሳካለት ይሆናል ለማለት ይሆን? አሁን ምድሪቱ ላይ የምታየውን ዕውነት ልብ ያልን እንደሆነ፣ ይህኛውም ትርጉም የበለጠ የሚመስል ነው።
ፕሮፌሰር ቲዎዶር ቨስታል፤ TheodoreM.Vestal “ETHIOPIA:A Post-Cold War African State” በሚለው መጽሐፋቸው ስለ ፋሲል ኖሆም በሰፊው ጽፈዋል። በገጽ 95-96 ይገልጹታል። በገጽ 102 የግርጌ ማስታወሻም ላይ፣ ፋሲል በ1966 የኃይለ ሥላሴን ሕገመንግሥት፤ በኋላም ትንሽ ቆየት ብሎ የደርግን ህገ መንግስት አርቃቂ መሆኑና አሁን ደግሞ ለሶስተኛ ጊዜ የዚህኛው አርቃቂ መሆኑንም ያመለክታሉ። ሌሎች ምሁራን መፈልፈል እንዲቻል የሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅንም ያቋቋመው ፋሲል ናሆም ነው።
የፋሲልን መጽሐፍ አንድ ቀን አበራየዋለሁ፤ ወይም “ገላልጦ ለማየት” እሞክራለሁ የሚል ሐሳብ ስለአለኝ እመለስበታለሁ። የፋሲል መጽሐፉ ሽፋን ሁለት የአኩሱም ሐውልቶችና በመካከሉ አሮጌ የብራና ጽሁፍ የሚመስል ተሸንቅሯል። ወደ ጥንታዊቱ ዘመነ አኩሱም እንመልሳችኋለን ነው መልእክቱ? መቼም ትርጉም አለው! ከሌሎች ነጥቦች ጋር ሲገናዘብ፣ ለዚህም ትርጉም ቦታ አለው።
የዛሬን የኢትዮጵያን ማንነትና ምንነት ለመረዳት፣ የኢህአዴግን  ሕገመንግሥት አንቀጽ 2 ማንበብ ይበጃል። ኢትዮጵያ ማለት የፌዴሬሽኖቹ አባላት ጥርቅም ነው ይልና ዳር ድንበሯ ግን በስምምነት ይወሰናል ይላል። ስለ ምድሩ ስለ ሰማዩ፤ ስለ አየሩ፣ ስለ ባሕሩ የሚያወሳው ነገር የለውም። እርግጥ ስለ ባህሩ የሚያነሳው ነገር የለዉም። ቀይ ባህርን ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥነት ያገኘችው ስለሆነ፣ የኢትዮጵያ አካል አይደለችም፣ አልነበረችምም ብሎ መለስ ዜናዊ ለተባበሩት መንግስታት ደብዳቤ ጽፏልና፣ ስለ ባህር ንብረት ሊነሳ አይችልም። ዳር ድንበሯ የተከበረ፤ የማይደፈር፤ የማይቆራረስ ነው አይልም። አንዴ ኤርትራ ተቆርሶ ሔዷልና፣ ከአሁን በኋላ አይቆራረስም ማለቱ ትርጉም የለውም ብለውም ሊሆን ይችላል። በህግ Precedent ይሉታል። አስቀድሞ የተወሰነውን፣ ይህኛውም ይከተላል እንደ ማለት ነው።
በዚህ ላይ አሁን ሲነገር እንደምሰማው፤ (ተጠናቆ እንደሁ አላውቅምና) ለሱዳንም መሬት ይሰጥና ከዚያ በኋላ ይመስለኛል የምዕራቡ ድንበራችን የሚወሰነው። በምስራቅ በኩል ያለው ድንበራችን ጉዳይ በእጃችን ያለ አይመስለኝም። ሶማሌ መፈረካከሷ ብቻ ሳይሆን ሞቃዲሾን ያማከለው የሱማሌ መንግስት የሚሉት፣ እንኳንስ ድንበር ሊካለል፣ ለራሱም ቢሆን ከመንግስት ይልቅ የመንግስት ቅዠት ነው የሚመስለው።
ብቻ ብዙ ማለት ሲቻል ላሳጥረው። በኢህአዴግ ሕገመንግሥት አንቀጽ ሁለት መሠረት፤ ኢትዮጵያ የታወቀ፣ የጸና፣ የማይሸራረፍ፣ የማይቦጨቅ ዳር ድንበር የላትም፡፡
መሪዎቹ
አሁን ደግሞ በሥልጣን ላይ ያለ መንግስት፣ አድራጊ ፈጣሪ የነበሩ መሪዎች፤ ማለትም ኃይለ ሥላሴን፤ መንግስቱ ኃይለማርያምንና መለስ ዜናዊን በጨረፍታ ለማየት እንሞክር።
በኔ አስተያየት፤ አስተያየት ብቻ ሳሆን ከተግባራቸው በመነሳት እነዚህ ሶስት ግለስቦች ከጠበቅነውና ከምንጠብቀው በላይ የሚጋሩት የጋራ ባሕርይ ያላቸው ይመስለኛል። ከእነዚህ የጋራ ባሕርያት ውስጥ  ሰውን የመረዳትና የመመዘን ብቻ ሳይሆን ሰንጥቆ ውስጡን የማየት፤ሰውን ፈጽሞ አለማመን፤ የሰውን ጠንካራና ደካማ ጎኑን ማወቅ፤ ጠንካራ ጎን አለው ብለው የገመቱትን ቢቻል ማራቅ፣ ካልሆነም ማጥፋት፤ በጣም የከረረ ራስ ወዳድነት፤ ርህራሔ (Empathy,Smpathy) የሚባለውን ነገር ጨርሶ አለማወቅ፤ ከዚህም የተነሳ ከወዳጅ ዘመድ፣ ጓደኛ ጀምሮ ይበልጠኛል ብሎ ያመኑትን ሰው ለማጥፋት ወደ ኋላ አለማለት፤ ለድርጊታቸው ተቀባይነት ያለው በአገር ፍቅር የተቀባባ ምክንያት መስጠትና ከራሳቸው በስተቀር ምንንም ማንንም አለመውደድና ያቀረቡ መምሰል እንጅ ሰው አለማቅረብ —– ገላጮቹ ናቸው። ዋና መመሪያቸው፤ “ጠርጥር ገንፎም ውስጥ አለ ስንጥር!” የሚል አይነት ይመስላል።
የሰውን ልጅ ስነአዕምሮ አጥኝዎች (Psychologists) ይህንን ከአዕምሮ ህመም እንደ አንዱና ለማከምና ለማዳን የማይቻል መሆኑን ይገልጻሉ። ለማከምና ለማዳን የማይቻለው፣ የዚህ አይነት ህመም ያለባቸው ሰዎች በጣም ጠልቀው የሚያዩ ስለሆነ፣ ሐኪሙ ለሚጠይቀው ጥያቄ “የሚፈልገው መልስ ይህ ነው!” ብለው አውቀው፣ ወስነው ስለሚመልሱ፤ በሩን መዝጋት ስለሚችሉ፣ ውስጥ ገብቶ አይቶ መድኅኒትም ሆነ ምክር መስጠት አይቻልም ነው የሚሉት።
ይህን የአዕምሮ ህመም አይነት Sociopath  ይሉታል። በአማርኛ ለመተርጎም ይከብደኛል። ምናልባትም ዕቡይ ማለት ይቻል ይሆናል። ይህንን ለመረዳት M.E Thomas  የምትባል የሕግ ፕሮፌሰር Confessions of a Sociopath: A Life Spent Hiding in Plain Sight: በሚል የጻፈችው ዝነኛ መጽሐፍ አለ። የመጽሐፉ ተጨማሪ ርዕስ፡- A Life Spent Hiding in Plain Sight የሚል መሆኑን ልብ ይሏል! አብረውን ናቸው ግን አንለያቸውም፤ አናውቃቸውምም ለማለት ነው። እንደሌላው በሽታ በአደባባይ የሚገለጥበት መንገድ የለውም ለማለት ነው። ራስዋ የዚህ ሕመምተኛ መሆንዋን አምና፣ በምርጥ የአዕምሮ ሕመም ሐኪሞች (Psychiatrists) ተመርምራ የጻፈችው ነበር።  እኔም ይሕንን መጽሐፍ ካነበብኩ በኋላ አንድ በዚህ ሙያ  25 አመት የሰራና ልምድ ያለው፣በሚያስተምርበት ተመዝግቤ አንድ የሳይኮሎጂ ትምህርት ወሰድኩ። ከዚያ በፊት ዩኒቨርስቲ እንደ መግቢያ የወሰድኩት የሳይኮሎጅይ ትምህርትና በንባብም ያዳበርኩት ተጨምሮ ነው እዚህ ከሙያዬ ውጭ ይህን አስተያየት እንድሰነዝር የገፋፋኝ። አንድ ቀን ክፍል ውስጥ ይህንኑ ፕሮፌሰር፤ “ታዲያ ስለ Sociopath ምን ይሻላል?” አልኩት። “መሆኑን ከለየህ፣ ከቻልክ ከአጠገቡ ሮጠህም ቢሆን አምልጥ!” ያለኝን አስታወስኩና ሳቅሁኝ። ሩጬ አላመለጥኩምና!
ባለሙያዎቹ ይህ የአዕምሮ ሕመም፤ ሁለት ምንጭ አለው ይላሉ። አንዱ በተፈጥሮ (Genetic) ሲሆን ሁለተኛው ከአስተዳደግ ነው ይሉናል። Nature and Narture ይህንን አሁን ባለው ማስረጃ ኃይለ ሥላሴን እንመለከት። የ19ኛው ክፍለ ዘመን ሰው ነበሩ። ይህም ማለት ወጣቱ ምንሊክ ነበሩ ማለት ነው። የገዙት፤ የነዱት ደግሞ በ20ኛው ክፍለ ዘመን ነበር። ይህም ማለት ዘመኑ የርሳቸው ዘመን አልነበረም (anamoly) ለማለት ነው። ቢሆንም ፊደልም ቢሆን ከፈረንጅ ጋር ቆጥረዋል። ሰዉ ማመስገን የማይሆንላቸው ተፈሪ መኮንን፤ “ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ“ በሚለው መጽሐፋቸው፤ የሚያመሰግኑት ይህንኑ ፈረንጅና አንድ ከኦርቶዶክስ የኮተለክ አስተማሪያቸውን ብቻ ነበር። ተፈሪ መኮንን፤ እናት፣ አባት፣ ወንድም፣ እህት የሌላቸው፣ በመጥፎ ሞግዚት ያደጉ ነበሩ። የዘውዴ ረታን፤ “ተፈሪ መኮንን” እና የፈታውራሪ ተክለሐዋሪያትን፤ “ሜሟር” ማንበብ ነው። አባት የላቸውም ያልኩት በሕይወት ሳይሆን ከስራቸው የተነሳ፣ ራስ መኮንን የሚያሳድጉ አባት አልነበሩም ለማለት ነው። ይህ እንግዲህ የኃይለ ሥላሴን ድብቅና ሽምቅ ፍቅር አልባ ነፍስ የቋጠረ ይመስለኛል። ጸጋዬ ገብረመድኅን፤ “በክልስ አባ ልበ እግረኛ” ግጥሙ፤ “..ከራሱ በስተቀር ሌላ ያለው የማይመስለው..” የሚለው አይነት መሆኑ ነው።
ከሌላ እናት የሚወለዱ አንድ ወንድማቸው፤ ደጃዝማች ይልማ፤ ቢኖሩም እሳቸውንም ቢሆን በመጽሐፋቸው ውስጥ ይከሳሉ። ይቀናቀነኝ ነበር! ይላሉ።
(ይቀጥላል)

ቆሻሻ መጣል ክልክል ነው! ዲ/ን ዳንኤል ክብረት


የሰዎችን አስተሳሰብ ሊለውጡ የሚችሉ ንግግሮችን በማድረግ የሚታወቀው ዓምደኛው ዴቪድ ጄ. ፖላይ ‹የቆሻሻ መኪና ሕግ (The Law of the Garbage Truck)  የተሰኘ ተወዳጅና ተደናቂ መጽሐፍ አለው፡፡ ይህንን መጽሐፉን ለመጻፍ መነሻ የሆነው ኒውዮርክ ውስጥ አንድ ቀን በታክሲ ሲጓዝ ያጋጠመው አደጋ ነበር፡፡ እርሱ የሚሄድበትን ታክሲ ከጎኑ የመጣ ሌላ መኪና ሊገጨው ለጥቂት ተረፈ፡፡ ስሕተቱ ከጎን የነበረው መኪና ሾፌር ነበር፡፡ ነገር ግን አደጋ አድራሹ ሾፌር በስሕተቱ ከመፀፀት ይልቅ መስኮቱን ከፍቶ የታክሲውን ሾፌር መሳደብና ማበሻቀጥ ጀመረ፡፡ የታክሲው ሾፌር ግን ፈገግ ብሎ እጁን ለሰላምታ በማውለብለብና ‹መልካም ቀን ይሁንልህ› በሚል የምኞት ቃል አለፈው፡፡
ጄ. ፖላይ ነገሩ ስላስገረመው የታክሲው ሾፌር ጠየቀው፡፡ ‹ጥፋተኛው ያኛው ሾፌር ነው፡፡ ይባስ ብሎም መስኮቱን ከፍቶ ሲሰድብህ ነበር፡፡ አንተ ግን መልካም እንደተደረገልህ ሁሉ ፈገግ አልክለት፤ እንዲያውም እጅህን አውጥተህ ሰላምታ ሰጠኸው፡፡ መልካም ምኞትህንም ገለጥክለት፡፡ ግን ለምን?› ሲል ጠየቀው፡፡ የታክሲውም ሾፌር አሁንም ፈገግ ብሎ ‹ብዙ ሰዎች የቆሻሻ መኪኖች ናቸው፡፡ ቆሻሻውን ተሸክመውም የሚያራግፉበት ቦታ ይፈልጋሉ፡፡ የያዙት ቆሻሻ ስድብ፣ ንዴት፣ ጭንቀት፣ ብልግና፣ ጭቅጭቅ፣ ንዝንዝ፣ ቁጣ፣ ርግማን፣ ተንኮልና ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ልክ የቆሻሻ መኪና ከየቤቱ ቆሻሻውን እስኪሞላ ድረስ እንደሚሰበስበው ሁሉ እነዚህም ከቤታቸው፣ ከትዳር አጋራቸው፣ ከጓደኞቻቸው፣ ከሥራ ቦታቸው፣ ከንግድ ድርጅታቸው፣ ከብሶታቸው፣ ከኪሣራቸው፣ ከደረሰባቸው ችግርና ካጋጠማቸው ፈተና ቆሻሻቸውን ይሰበስቡታል፡፡
አንተ ግን የቆሻሻ መጣያቸው አትሁን፡፡ የቆሻሻ መኪናው ሲሞላ የመጣያ ቦታ ይፈልጋል፡፡ ከዚያ ደግሞ ተመልሶ እንደገና ሌላ ቆሻሻ ይሰበስባል፡፡ እነዚህም ከየቦታው ቆሻሻ ጠባያቸውን ይሰበስቡና አንተ ላይ ሊያራግፉብህ ይመጣሉ፡፡ ያን ጊዜ ዝም ብለህ አትቀበላቸው፡፡ የቆሻሻ መኪና ከየቦታው የሰበሰበውን ቆሻሻ ሲያነሣ፣ ቆሻሻ የነበረበትን ቦታ ያቃልለዋል፡፡ ነገር ግን ወስዶ ሌላ ቦታ በማከማቸት የተከማቸበትን ቦታ ያቆሽሸዋል፣ ያሸተዋል፣ ያበላሸዋል፡፡ እነዚህም እንዲሁ ናቸው፡፡ ከየቦታው የሰበሰቡትን ቆሻሻ ጠባይ አንተ ላይ ያራግፉና አንተን ሲያናድዱህ፣ ሲያበሽቁህ፣ ሲያስፀፅቱህ ይውላሉ፡፡ ቀንህን ያበላሹብሃል፡፡ ያደረጉህ ነገር፣ የሠሩህ ሥራና፣ የወረወሩብህ ስድብ አአምሮህ ውስጥ እየተብላላ ቀኑን ሙሉ ጠባይህን አበላሽቶት ይውላል፡፡
ለምን ትፈቅድላቸዋለህ? ፈገግ ብለህ፣ ምንም እንዳልተፈጠረ ቆጥረህ፣ ነገሩን አሳልፈህ፣ ለክፋታቸው በጎነት፣ ለስድባቸው መልካም ምኞት፣ ለርግማናቸው ምርቃት፣ ለቁጣቸው ፈገግታ፣ ለትዕቢታቸው ትኅትና መልስላቸውና ቆሻሻቸውን ይዘው እንዲመለሱ አድርጋቸው፡፡ በጭራሽ አንተ ላይ ማራገፍ የለባቸውም፡፡ ለዚህ ነው እኔም በፈገግታ፣ በሰላምታና በመልካም ምኞት የሸኘሁት፡፡ ከቻልኩ በርሱ ላይ ያለውን ቆሻሻ አቀልለታለሁ፡፡ ስላልሰደብኩት፣ ስላላንጓጠጥኩትና ስላልተጨቃጨቅኩት ቀኑን ሙሉ ፈገግታዬን፣ ሰላምታዬንና መልካም ምኞቴን በማሰብ ሲደሰት ይውላል፡፡ ካልተቻለ ደግሞ እኔ ላይ ቆሻሻውን ከማራገፍ ስለተከላከልኩት አትራፊው እኔ ነኝ› ሲል አብራራለት፡፡
ይህንን የሰማው ጄ. ፖላይ ነገሩን ሲያምሰለስለው ከርሞ፤ ‹የቆሻሻ መኪና ሕግ› የተሰኘውን ተወዳጅ መጽሐፉን አዘጋጀ፡፡ ፖላይ በዚህ መጽሐፉ ውስጥ ‹የቆሻሻ መኪና በአንተ ላይ ቆሻሻውን እንዳያራግፍ ከፈለግክ እነዚህን ሕጎች ተግብራቸው› ይላል፡፡ የመጀመሪያው ሕግ ባለጌ፣ ሐሳብ አልባና ቁጡ የሆኑ ሰዎች በአንተ ላይ ቆሻሻቸውን እንዳይጥሉ ምንጊዜም ተከላከል› የሚል ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰዎች ሲያግጥሙህ ከቻልክ ጆሮህን ካልቻልክም ልብህን አትስጣቸው፡፡ ‹ወፎች በጭንቅላታችን ላይ እንዳይበሩ ማድረግ አንችልም፡፡ በጭንቅላታችን ላይ ጎጆ እንዳይሠሩ ማድረግ ግን እንችላለን› የሚል አባባል አለ፡፡ ሰዎች እንዳይሳደቡ፣ እንዳይቆጡ፣ ነገር እንዳያመነጩና እንዳይነታረኩ ማድረግ አንችልም፡፡ ጭንቅላታቸው እነርሱ ላይ ስለሆነ፡፡ ነገር ግን ከእነርሱ አንደበት የሚወጣው ክፉ ቃል በጆሯችን በኩል ወደ ልባችን ገብቶ፣ ጎጆ እንዳይሠራ ማድረግ  ይቻላል፡፡ ስናስበው፣ ስናወጣ ስናወርደው፣ ከንፈራችንን ስንነክስለት፣ ጠረጲዛ በቡጢ ስንመታና ምነው እንዲህ ባልኩት ኖሮ፣ እንዲህም ባደረግኩት ኖሮ ስንል እንዳንውል ማድረግ ይቻላል፡፡ እንዴት? ፊት ባለመስጠት፣ ጆሮና ዓይን በመንሣት፣ የልብን በር በመዝጋት፣ ከቁብ ባለመቁጠር፣ ለመርሳት በመሞከር፣ በጭንቅላታችን ላይ እንደሚበሩት ወፎች በመቁጠር፡፡ በመናቅና በማቃለል፡፡
ሁለተኛው ሕግ ደግሞ፤ ‹ያለፉ ክፉ ነገሮችን ማስታወስና ቀጣዩን የሕይወት ጉዞህን መፍራት አቁም› ይላል፡፡ ያለፉ ክፉ ትውስታዎችን በአንዳች ነገር ዝጋቸው፡፡ በንስሐ፣ በይቅርታ፣ በካሣ፣ በዕርቅ፡፡ እርሳቸው፡፡ ካልቻልክ ደግሞ በሚጎዱህ መጠን ልክ አታስታውሳቸው፡፡ መርሳት የሚባለው ጸጋ የተሰጠን አንድም ክፉ ነገሮችን ለመርሳት እንድንችል ነው፡፡ ቆሻሻውን አጽዳ፡፡ ሰዎች በአንድ ወቅት ክፉ አድርገውብህ ይሆናል፡፡ እነዚያ ሰዎች በአንተ ላይ ቆሻሻውን አከማቹት ማለት ነው፡፡ አንተም ለዘመናት የቆሻሻቸው ማራገፊያ ሆነህ፣ ይዘኸው እየተጓዝክ ነው፡፡ አራግፈው፡፡ ቆሻሻ ምንም ቢራገፍ በቆሻሻ መኪናው ላይ የሚተርፍ ቅሬት መኖሩ አይጠረጠርም፡፡ አንተም ባለፉት ዘመናት ሰዎች ላይ ቆሻሻ ስታራግፍ አንተ ላይ የቀሩ ትርፍራፊዎች አይጠፉም፡፡ ተሸክመኻቸው አትዙር፤ አራግፋቸው፡፡ ያለፉ ቆሻሻዎችን አለማጽዳት ነገን እንድንፈራው ያደርገናል፡፡ ያለፉ ቆሻሻዎችን በሚገባ ካጸዳናቸው ነጻነት፣ ንጽሕናና ብሩኀ ተስፋን እናገኛለን፡፡ ብዙ ሰዎች የትናንት እሥረኞች ናቸው፡፡ እርሾው መልካም ካልሆነ ሊጡ፣ ብሎም እንጀራው እንደሚበላሸው ሁሉ ትናንትህ ካልጸዳ ነገህ ይበላሻል፡፡
ሦስተኛው ሕግ ደግሞ ›ልትቆጣጠረው በምትችለው ነገር ላይ አተኩር እንጂ ልትቆጣጠራቸው በማትችል ክፉ ነገሮች ላይ ጊዜ አታጥፋ› የሚል ነው፡፡ ሰዎች በሚናገሩት፣ በሚያደርጉት፣ በሚሠነዝሩትና በሚፈጥሩት ነገር ላይ ልብህ አይቁም፡፡  በታክሲ ውስጥ ስትሄድ አንድ ጋጠ ወጥ ሰው ቢገጥምህና የማይሆን ቃል ቢናገርህ ለእርሱ ቦታ አትስጠው፡፡ አንዱ ፌርማታ ላይ ይወርዳል፡፡ ከዚያ በኋላ አታገኘውም፡፡ አንተን ግን ቀኑን ሙሉ ሲበጠብጥህ ይውላል፡፡ ‹ቁንጫ የጠረጉት ለት ባለጌ የመከሩት ለት ይብሰዋል› እንዲሉ ምክር ለሁሉ አይሰጥም፣ መልስ ለሁሉ አይመለስም፤ ክርክር ከሁሉም ጋር አይደረግም፡፡ ዕንቁዎችህን የምትሰጣቸውን ሰዎች ለይ፡፡ ዕንቁላሎችህን የምታስታቅፋቸውን ዶሮዎች ምረጥ፡፡ የዚያን ሰው ተግባር፣ ንግግር፣ ጠባይ፣ ባህልና ልምድ ልትቆጣጠረው አትችልም፡፡ ልጅህ ነው? ጓደኛህ ነው? የትዳር አጋርሽ ነው? የሥራ ባልደረባህ ነው? ጎረቤትህ ነው? በጉዳዩ ላይ ብትበረታበት ለውጥ ለማምጣት ትችላለህ? ከሆነ መልካም፡፡ ካልቻልክ ግን ለምን ዕንቁዎችህን በእሪያዎች ፊት ትጥላለህ? ‹እገሌ እንዲህ ይልሃል›፣ ‹እዚህ ቦታ ስላንተ እንዲህ ሲወራ ሰማሁ› የሚሉትን አትስማ፡፡ አትቆጣጠራቸውም፡፡ ራስህን ተቆጣጠር፣ ራስህን ግራና የራስህን መንገድ ቀይስ፡፡
አራተኛው ሕግ ‹ባገኘህበት ቦታ ሁሉ ጋጠ ወጥነትን ቀንስ፣ ሥልጣኔን ጨምር፣ ጉልቤዎችን ከነ ቆሻሻ መኪናቸው አስቁማቸው› ይላል፡፡ ሰዎች በአንተ ላይ ጋጠወጦችና ያልሠለጠኑ እንዲሆኑ አትፍቀድላቸው፡፡ መርሕህን፣ ጠባይህንና መሥመርህን ግልጽ አድርግላቸው፡፡ ጋጠወጥነትንና አለመሠልጠንን በቸልታና በዝምታ ከተቀበልካቸው እንደ ልባቸው ይፈነጩብሃል፡፡ ከመጀመሪያው እንዲህ ላሉ ሰዎች ቦታ አይኑርህ፤ ካጋጠሙህም ሐሳብህን ግለጥላቸው፡፡ ካልተመቸሃቸው ወይም ካልተመቹህ ግንኙነትህን አቋርጥ፡፡ ‹ለባለጌ ከሳቁለት፣ ለውሻ ከሮጡለት› አደጋው ከባድ ነው፡፡ ሥልጣን ወይም ጉልበት ስላላቸው ብቻ በአንተ ላይ ቆሻሻ ለመድፋት እንደሚችሉ የሚያስቡ ባለ ሥልጣናት፣ አለቆች፣ ጉልበተኞችና ደፋሮች ይኖራሉ፡፡ ከቻልክ በሕግ ካልቻልክ ግን በርህን በመዝጋት መኪናውን አስቁመው፡፡ የሚፈልጉትን አታድርግላቸው፣ በመንገዳቸው አትሂድ፣ በዕቅዳቸው አትመራ፣ ጠባያቸውን አትጋራ፣ እንዳመጣጣቸው አትመልስ፡፡ ምንጊዜም አንተ ራስህን ብቻ ሁን፡፡ የወረወሩትን አታስበው፣ የጠየቁህንም ሁሉ አትመልስ፡፡ ችግሩን የመፍቻ ሌላ መንገድ አስብ፡፡ የሠለጠነ፣ ሕጋዊ የሆነና፣ ችግሩን የሚፈታ መንገድ ፈልግ፡፡ ጋጠወጥነትን በጋጠወጥነት፣ ስድብን በስድብ፣ ነገርን በነገር፣ ክፋትንም በክፋት አትመልስ፡፡ ያ ከሆነ በመንገዳቸው እየተጓዝክ፣ የቆሻሻቸውም ማራገፊያ እየሆንክ ነው፡፡ ሁለታችሁም ጋ አንድ ዓይነት ሽታ ካለ፣ ሁለታችሁም ጋ አንድ ዓይነት ቆሻሻ አለ ማለት ነው፡፡
አምስተኛው ሕግ ደግሞ ‹በቤተሰቦችህ፣ በልጆችህ፣ በጓደኞችህና በሥራ ባልደረቦችህ ላይ ቆሻሻ ባለመድፋት ጠባይህን እየገራኸው ሂድ› ይላል፡፡ ከቻልክ ከአንተ ቆሻሻ እንዳይወጣ አድርግ፡፡ ካልቻልክስ? ቆሻሻው ማንንም ሳይጎዳ የሚወገድበትን መንገድ ፈልግ፡፡ በተናደደክ ጊዜ ከሰዎች ጋር መከራከርን ተው፡፡ ተደስተህም ሆነ ተናደህ ውሳኔ አትወስን፡፡ ከስሜትህ ሳትበርድ ሰዎችን አታናግር፡፡ ከሰዎች ጋር ለመነጋገሪያ መልካሙ ጊዜ ስሜት በርዶ፣ አእምሮ ቦታውን ሲይዝ ነው፡፡ የተናደድክበትን ሰው ወዲያው አታግኘው፡፡ ውለህ አድረህ፣ ነገሩን አውጥተህና አውርደህ፣ ከተለያየ አቅጣጫም ነገሩን መዝነህ ከዚያ በኋላ አናግረው፡፡ ስድብ ሰውን አይለውጥም፤ ቁጣም አእምሮን አይቀይርም፤ ጭቅጭቅ እንደሚያንጠባጥብ የቤት ጣሪያ ይሆናል፤ ሐሜትም ዞሮ ለራስ ነው፡፡ ለውጥ ማምጣት፣ ችግር መፍታትና ሰዎችን ማረም ከፈለግክ ሌሎች መንገዶችን ሞክር፡፡
‹ከመርገም ውስጥ በረከትን ፈልግ› ይላል ስድስተኛው ሕግ፡፡ ከኪሣራህ፣ ከሕመምህ፣ ከጉዳትህና ከችግርህ ውስጥ ደስታን ለማብቀል ሞክር፡፡ አካልህን ሲያሥሩህ፣ ኅሊናህን ነጻ አድርግ፤ ሰውነትህን ሲያምህ፣ አእምሮህን ጤነኛ አድርገው፤ ገንዘብህን ስትከስር ጤናህንና ሥነ ልቡናህን  አትርፍ፤ ወዳጆችህን ስታጣ፣ ትዝታቸውን አስቀር፤ አካልህ ሲጎዳ መንፈስህን ሙሉ አድርግ፤ ያጣህውን ትተህ ያለህን ቁጠር፡፡ ማንም ጥርስህን እንጂ ፈገግታህን ማርገፍ አይችልም፡፡ ማንም ዋንጫህን እንጂ አሸናፊነትህን ሊወስድብህ አይችልም፡፡
‹የቆሻሻ መኪና የማይደርስበት ክልል መሥርት› የሚለው ደግሞ ሰባተኛው ሕግ ነው፡፡ በቤተሰብህ፣ በጓደኞችህ፣ በዘመዶችህ፣ በሥራ አካባቢህና በመንደርህ ይህንን ክልል መሥርት፡፡ ሌሎችን በማሳመን፣ በማስረዳት፣ ሐሳብህን በመግለጥና ነገሩ እንዲገባቸው በማድረግ ‹የቆሻሻ መኪና በዚህ ማለፍ ክልክል ነው› የሚል መርሕ እንዲኖራቸው ማድረግ ትችላለህ፡፡ የምትውልበት፣ የምትሠራበትና የምትኖርበት አካባቢ ከቆሻሻ መኪኖች ነጻ ከሆነ ማንም ወደ አንተ ቆሻሻ ለመድፋት አይመጣም፡፡ በቢሮህ ግድግዳ ላይ ‹ቆሻሻ መድፋት ክልክል ነው› የሚል ለጥፍ፡፡ ሰዎች ይገርማቸውና ይጠይቁሃል፡፡ ‹እዚህ ቢሮ የቆሻሻ መኪና ምን ሊያድርግ ይመጣል? የጽዳት ሠራተኞችስ እንዴት እዚህ ቦታ ቆሻሻ ይደፋሉ? › ይሉሃል፡፡ ንገራቸው፡፡ ቆሻሻው ምን እንደሆነና የቆሻሻ መኪኖች እነማን እንደሆኑ፡፡ ይቀየሩ ይሆናል፡፡ ከጓደኞችህም ጋር ተነጋገሩና ተስማሙበት፡፡ ማንም ቆሻሻውን በራሱም ላይ ሆነ በሌሎች ላይ ላይጭን ተስማሙ፡፡
የመጨረሻው ሕግ ደግሞ ‹በየቀኑ ለመደስት ሞክር፣ የምትወደውን ለመሥራትና የምትሠራውን ለመውደድ ተጣጣር፣ ተግባርህም ሁሉ ለውጥ የሚያመጣ ይሁን› ይላል፡፡ በየቀኑ መደሰት ማለት በየቀኑ መጠጣት፣ አዲስ ልብስ መልበስ፣ ሲኒማ መመልከትና ቀልድ ሲቀልዱ መዋል አይደለም፡፡ አዲስ ነገር ለመሥራትና ትርጉም ያለው ውሎ ለመዋል ወስኖ መነሣት ነው፡፡ መሥሪያ ቤትህ ዕቅድ ይኖረው ይሆናል፡፡ አንተስ አለህ? ወደ ቢሮ የምትሄደው ያስቀመጥከውን ለመሥራት ነው ወይስ የተቀመጠልህን ለመሥራት? ስንት ፋይል ልታይ፣ ስንት ውሳኔ ልትወስን፣ ስንት ምርት ልታመርት፣ ስንት ችግር ልትፈታ፣ ስንት ትርፍ ልታመጣ፣ ስንት ሰው ልታክም፣ ለራስህ ምን አቅደሃል? አካባቢህን ጽዱ፣ ውብ፣ ሥራብኝ ሥራብኝ የሚል አድርገኸዋል? ሥራ ቦታህ ላይ ከቀኑ ውስጥ ሩቡን ትውልበታልህ፤ ያ ማለት ከሕይወትህ ሩቡን ታሳልፍበታለህ፤ የሥራ ቦታህን ስታበላሸው ሩቡን ኑሮህን ታበላሸዋለህ፡፡ ያም ብቻ አይደለም፡፡ ሥራህን በወደድከው መጠን ጠዋት ወደ ሥራህ እንደ ጽጌሬዳ ይስብሃል፡፡ ማታም ወደ ቤትህም በደስታ ይሸኝሃል፡፡
ከቻልክ የምትወደውን ሥራ ሥራ፡፡ ካልቻልክ የምትሠራውን ሥራ ውደድ፡፡ ለመጥላት ምክንያት ከምትፈልግ ለመውደድ ምክንያት ፈልግ፡፡ የምትጠላውን ሥራ እየሠራህ ምንም በጎ ለውጥ ልታመጣ አትችልምና፡፡ ደንበኞችህ ቆሻሻ ተጭነው ይመጡ ይሆናል፡፡ አንተ ግን እንዲያራግፉብህ አትፍቀድላቸው፡፡ ንዴታቸውን አብርደህ፣ ቁጣቸውን አሳስቀህ፣ ችግራቸውን ፈትተህ፤ ያንንም ሁሉ ካልቻልክ ኀዘናቸውን ተካፍለህ መልሳቸው፡፡ ቢሮህን የቆሻሻ ማከማቻ አታድርገው፡፡ ስብሰባ የደስታ ምንጭ፣ የዕውቀት መገብያና፣ የችግር መካፈያ እንጂ የቆሻሻ መጣያ እንዳይሆን ሥራ፡፡ ደስታ ከለውጥ ይገኛል፡፡ የምትጋተረው ከችግሮች ጋር እንጂ ከሰዎች ጋር አይሁን፡፡ ለውጥ እያመጣህ በሄድክ ቁጥር ለራስህ ደስታን እየሸመትክ ትሄዳለህ፡፡
ይህንን ለማድረግ የቆረጡ ሰዎች ይህንን መፈክር ይዘዋል፡፡
ቁም! እዚህ ቦታ ቆሻሻ መጣል ክልክል ነው፡፡
አዎ! በሚያሳዝን ሁኔታ!
የአባተን እንደዚህ ከጨረስኩልህ ተስፋዬ ይፍሩስ እንዴት ሆነ ነው? የቤተሰቦቹን ዕጦት፣ የቤተሰቦቹን ኪሳራ እናስላው … አንድ አናፂ አባት፤ ሁለት ልጆቹን በድህነት አስተምሮ ተስፋዬ ይፍሩ መሀንዲስ እዚህ ጎፋ ተመደበ፤ አመፅ ተነሳ፡፡ የአመፁ አስተባባሪ እሱ ነው፡፡
“ተስፋዬ?”
አዎ ታላቅየው፣ አባተን ያስተማረው ማለት ነው። ሲያምፁ እሱ ለጥበቃ የተመደበበት ቦታ አሁን ልክ በድሉ ህንፃ የተባለው ቦታ ነው፡፡ እነ መንግስቱ ኃ/ማ፣ ደርጎች ደረሱ፤ አመፁ ላይ፡፡ አመፁን ሊያከሽፉና ተስፋዬ ይፍሩን የአመፁን አስተባባሪ፣ እጅ ከፍንጅ ሊይዙት ሲሉ ራሱን ገደለ!!
ያ ትውልድ እሺ፤ እንዴት ነው በካህሳይ ድላይ የሚመዘነው? እዚች አገር የማዝነው እነ ገረመው የሚባሉ 14000 ብር (የፊውዳል ልጅ ነው፣ የባላባት ልጅ ነው) አባትዬው ሁሉን ነገር ሲወረሱ፣ ያንን ገንዘብ ከሳጥን ውስጥ ወስዶ፤ ለኢህአፓ ለከተማው አስረክቦ አሲምባ የመጣው ልጅ ጭንቅላቱን ሲመታ፣ በአንድ እጁ በሁለት እግሩ ማህል ገብቼ ላድነው ስል የሁለታችንም ግንባር እኩል በሆነበት ላይ አንዷ ጥይት የእሱን ግንባር መትታው፣ የሱ ግማሽ ግንባር እግሩ ላይ ሲወድቅ፤ እኔ ወይ ሰቦቃ፣ ወይ ለማ ወይ ደርቤ የፈለከውን በለኝ፤ ከዛ በላይ እኔ ተርፌ፣ ያ ደም እኔ ላይ ፈሶ፣ በደምቡ መሰረት ስኖር፤ ትልቅ ነገር ነው – ያ ደም እሜዳ ፈስሶ እንዴት ይሆናል? ላለየው ሰው ለማስረዳት ይከብዳል፡፡ ካልኖርከው በስተቀር አባተ ይፍሩን ለማን ትነግራለህ? ተስፋዬ ይፍሩን ለማን ትነግራለህ? ድላይና ካህሳይ (አማኑኤል በሚል ስም ነው የማውቀው እኔ) ሁለቱ የጭንቅላታቸው አቅም ከመዋደድ ያላለፈ ነው እሺ! አገር ህዝብ፤ Ideologyን አልደረሱበትም – ገና መዋደድ ላይ ናቸው፡፡ ስለዚህ ተዋደውም ከሆነ፣ መፋቀሩም ተሰርቶ ከሆነ፤ ባይዋደዱ አይገርመኝም፡፡ ግን እዛ ጋ በአንተ ግጥም ያልተዘመረለት ብለህ ፅፈሃል- እኔ መኃይም በመሆኔ፣ምሁር ባለመሆኔ ያልጻፍኩትን፣ ስለ እነ አባተ ይፍሩ ብታውቅ ያልተዘመረለትን ምን ልትል ነው? የተዘመረላቸውስ እነ ጃራ አሉ! አሪፍ ልጆች ናቸው!
“ያ፤ ተራራ የተሰየመለት ጀግና ነው ያልከኝ? ነው እንዴ?”
ደረጄ ሞሲሳ ነው ዕውነተኛ ስሙ፡፡ የላብ ስኩል (የበዕደማሪያም) ልጅ ነው፡፡ የበረሀ ስሙ ጃራ ነው! ሮባ ልጁን በስሙ ጃራ ብሎ ነው የሰየመው – ዛሬ!
“የሮባ ልጅ?”
የሮባ ልጅ ጥፋት ቢያጠፋኮ ይሄን ስም አነሳብሃለሁ ነው ያለው፡፡ ይበዛብሃል! ይሄ የተዘመረለት ጃራ ነው፡፡ ያልተዘመረላቸው አባተና

እንጀራው 30 በመቶ ጤፍ፣ 70 በመቶ ጀሶና ሰጋቱራ ተቀላቅሎ ይጋገራል::በሁሉም ክፍለ ከተሞች ድርጊቱ እንደሚፈፀም ለማወቅ ተችሏል


– ወንጀሉ ላለፉት 5 ዓመታት በከተማዋ በድብቅ ሲፈፀም ቆይቷል
– እንጀራው 30 በመቶ ጤፍ፣ 70 በመቶ ጀሶና ሰጋቱራ ተቀላቅሎ ይጋገራል
– ሀኪሞች፤ ጀሶና ሰጋቱራ በጉበትና ኩላሊት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል አሉ
– በሁሉም ክፍለ ከተሞች ድርጊቱ እንደሚፈፀም ለማወቅ ተችሏል
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች ጥቂት የጤፍ ዱቄትን ከጀሶ፣ ከሰጋቱራና ከደረቀ እንጀራ ዱቄት ጋር በመቀላቀል እየጋገሩ፣ ለገበያ የሚያቀርቡ ሰዎች ከየአካባቢው በቁጥጥር ሥር እየዋሉ ነው፡፡ እስከ አሁን በአቃቂ ቃሊቲ፣ በልደታ፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በሰበታ ከተማ ውስጥ በተመሳሳይ ድርጊት ላይ የተሰማሩ ህገወጦች መያዛቸው ታውቋል፡፡ በትላንትናው ዕለት በልደታ ክ/ከተማ በተመሳሳይ ድርጊት ላይ የተሰማሩ 5 ተጠርጣሪዎችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡
ህገወጦቹ 30 በመቶ የጤፍ ዱቄት፣ ቀሪውን 70 በመቶ ደግሞ ጀሶ፣ ሰጋቱራና የደረቅ እንጀራ ዱቄት በመቀላቀል እየጋገሩ ለሆቴሎች፣ ለሱፐር ማርኬቶች፣ ለሱቆችና ለምግብ ቤቶች በስፋት ሲያከፋፍሉ ቆይተዋል፡፡ ድርጊቱ በከተማዋ በሁሉም ክፍለ ከተሞች እየተፈፀመ እንደሚገኝና የተፈጨውን ሰጋቱራና የጀሶ ዱቄት ግብአቶች የሚያቀርቡ ግለሰቦች በስፋት እንደሚገኙ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል አንዳንዶቹ ተናግረዋል፡፡
መነሻውን አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ያደረገው ይኸው ህገወጦችን በቁጥጥር ሥር የማዋል ሂደት፤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ላፍቶና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞችም ቀጥሎ ሰንብቷል፡፡ ሰሞኑን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እየተባለ በሚጠራው የፖሊስ ካምፕ አካባቢ በሚገኘው የቅዱስ ጳውሎስ ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ በተመሳሳይ ሁኔታ 13 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ንብረትነቱ የቤተክርስቲያኑ በሆነውና አንድ ግለሰብ በኪራይ በወሰደው በዚህ ቤት ውስጥ በሰባት በርሜል የተቦካና ለጋገራ የተዘጋጀ ሊጥና በከረጢት ተሞልተው የተቀመጡ ጀሶዎች ተይዘዋል፡፡ ቀደም ሲል በዚሁ ክፍለ ከተማ አየር ጤና፣ ታቦት ማደሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተመሳሳይ መንገድ ጀሶና ሰጋቱራውን ከጤፍ ጋር እየተቀላቀሉ በመጋገር ለገበያ ሲያቀርቡ የነበሩ 8 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም የክፍለ ከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር አወል ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ውስጥ የተከናወነ የዚሁ ጤፍን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር ቀላቅሎ በመጋገር ለገበያ የማቅረብ ወንጀል መርማሪ የሆኑት ዋና ሳጅን ጎሽሜ አገኘሁ እንደገለፁልን፤ የድርጊቱ ፈፃሚዎች በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ አምስት ግለሰቦች ናቸው፡፡ ከእነዚህ ተጠርጣሪ ወንጀለኞች መካከል ሶስቱ በቁጥጥር ሥር ሲውሉ ሁለቱ እስከ አሁንም አልተያዙም፡፡ ተጠርጣሪዎቹ መንግስት በሰጣቸው ሼድ (መጠለያ) ውስጥ ጤፍን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር እየቀላቀሉ በመጋገር፣ ለሽያጭ የማቅረብ ሥራን ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ከአንድ ግለሰብ ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ መሰረት፤ የመሥሪያ ቦታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ ለመጋገር የተዘጋጀ 17 በርሜል ሊጥ፣ ከ20 ኩንታል በላይ የተፈጨና ለመቦካት የተዘጋጀ ዱቄት፣ በርካታ የሰጋቱራና የጀሶ ክምር መገኘቱን መርማሪው ገልፀዋል፡፡ በወቅቱ በጋገራውና በሊጥ ማቡካቱ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 12 ሰራተኞችና 3 የድርጅቱ ባለቤቶች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ የወንጀል ፈፃሚ ናችሁ ተብለው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት 15 ሰዎች መካከል 12ቱ ሰራተኞች ድርጊቱን የፈፀሙት ታዘው ነው በሚል ከእስር የተለቀቁ ሲሆን ሶስቱ የድርጅት ባለቤቶች ግን በእስር ቆይተው፣ የ50 ሺህ ብር ዋስ ጠርተው ወጥተዋል፡፡ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች አሁንም በፖሊስ አለመያዛቸው ታውቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ወቅት ድርጊቱ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እየተፈፀመ እንደሚገኝና ምንም አዲስ ነገር ወይም ወንጀል አለመሥራታቸውን ሲነገሩ ተሰምተዋል፡፡ ለምርት ግብአትነት የሚጠቀሙበትን የጀሶና የሰጋቱራ ዱቄት በአይሱዙ እያመጡ የሚያከፋፍሏቸው ሰዎች እንዳሉም ተጠርጣሪዎቹ ገልፀዋል፡፡ ከእስር የተለቀቁት አስራ ሁለቱ እንጀራ ጋጋሪዎች በወር 3000 ብር ደመወዝ እየተከፈላቸው ሲሰሩ እንደቆዩም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የወንጀል ክስ ያቀረበው የሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን፤ ሶስቱ ተጠርጣሪዎች ባዕድ ነገርን ከጤፍ ጋር ቀላቅለው በመሸጥ በሚል ወንጀል ክስ አቅርቦ ሐምሌ 15 ቀን 2008 ዓ.ም ለፍ/ቤት ምስክሮቹን አሰምቷል፡፡ ፍ/ቤቱ የተባለው ባዕድ ነገር በጤና ላይ የሚያስከትለው ጉዳት መጠን ተመርምሮ ማስረጃው እንዲቀርብለት፣ በማዘዝ ለሐምሌ 26 (የፊታችን ማክሰኞ) ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በትናንትናው ዕለት ደግሞ በልደታ ክፍለከተማ ልዩ ስሙ አፍሪካ ህብረት አካባቢ የጤፍ ዱቄትን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር ቀላቅለው እንጀራ እየጋገሩ የሚሸጡ ግለሰቦችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ተጠርጣሪዎች ምንም ዓይነት ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው፣ ለአምስት ሆነው በተከራዩት ቤት ውስጥ የጀሶና የሰጋቱራ እንጀራ እየጋገሩ ለሽያጭ ያቀርቡ ነበር ተብሏል፡፡ ፖሊስ በትናንትናው ዕለት በተጠርጣሪዎቹ ቤት፣ ለጋገራ የተዘጋጀ አራት በርሜል ሊጥ እንዲሁም ሶስት ኩንታል ከሰጋቱራና ጀሶ ጋር የተደባለቀ የእንጀራ እህል ይዟል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታም ባለፈው ሳምንት በሰበታ ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ቦታው ዋቶ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ነዋሪ በሆነ አንድ ግለሰብ የጤፍ ዱቄት ከጄሶና ሰጋቱራ ጋር እየተቀላቀለ ተጋግሮ ለሽያጭ ሲቀርብ በፖሊስ መያዙ ታውቋል፡፡ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር በዋለበት ወቅት በርካታ በርሜል ለጋገረ የተዘጋጀ ሊጥና ከሰጋቱራና ጀሶ ጋር የተቀላቀለ ዱቄት በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡
ከጀሶ፣ ሰጋቱራና የሻገተ ደረቅ እንጀራ ጋር እየተቀላቀለ የሚጋገረውና ለምግብነት እየዋለ የሚገኘው ‹እንጀራ››፤ በጤና ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት አስመልከቶ አስተያየታቸውን እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስቱ ዶክተር አብርሃም ተስፋዬ፤ ሁኔታው እጅግ አስደንጋጭና ሰብአዊነት የጎደለው ድርጊት መሆኑን ገልፀው፤ የከፋ የጤና ችግር ማስከተሉ አይቀሬ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹እንጀራው ለምግብነት ቢውል ይህን ዓይነት የጤና ችግር ያስከትላል ለማለት የንጥረነገሮቹን ምንነት ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ በጥቅሉ ግን በጀሶ ውስጥ የሚገኘው ንጥረ ነገር፣ ነገሮችን የማኮማተር፣ የማጨማደድ ባህርይ አለው፡፡ በዚህ ሳቢያም ሰውነታችን ሊጨማደድና፣ የመጠን ለውጥ ሊያመጣ ይችላል፡፡ ንጥረ ነገሩ፣ በኩላሊት፣ ጉበትና በጨጓራ ላይ የሚያስከትለው የጤና ችግር በቀላሉ የሚገልፅ አይደለም ብለዋል፡፡
የቶም ከፍተኛ ክሊኒክ ባለቤት የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቱ ዶ/ር አሚር መርዋን በበኩላቸው፤ ባዕድ ነገሮችን ወደ ሰውነታችን ውስጥ በሚገቡበት ወቅት እንደየ ንጥነገራቸው፣ ይዘታቸውና መጠናቸው የተለያዩ የጤና ችግሮችን ማስከተላቸው አይቀሬ መሆኑን ገልፀው ለባዕድ ነገሮቹ ተጋላጭነታችን እየጨመረ በሄደ መጠን የጉዳታችንም ልክ በዛው መጠን እየጨመረ እንደሚሄድ ተናግረዋል፡፡
‹‹ጀሶና ሰጋቱራ በአንጀት ውስጥ ገብተው መፈጨት የማይችሉ ከመሆኑም በላይ በጀሶ ውስጥ የሚገኘው ኬሚካል፣ የአንጀት ግድግዳን አልፎ ወደ ደም መሄድ ከቻለ፣ በውስጣዊ የሰውነታችን ክፍሎች ላይ ከባድ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ለዚህ ደግሞ የመጀመሪያው ተጋላጭ ጉበታችን ነው፡፡ ጉበት በተፈጥሮው ጎጂና መርዛማ ነገሮች በደም አካማኝነት አልፈው ወደ ኩላሊትና ሳንባ እየሄዱ ጉዳት እንዲያስከትሉ የማድረግ ተግባር ያለው በመሆኑ፣ እነዚህ ኬሚካሎችን በሚያገኝበት ጊዜ ራሱን መስዋእት አድርጎ፣ ይዘቱን እንዲቀይሩ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህ ሣቢያም ጉበታችን ለጉዳት ይጋለጣል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከጉበት አቅም በላይ ከሆነ ወደ ኩላሊት በመሄድ የኩላሊት ጠጠርና መሰል ችግሮች እንዲከሰቱ ያደርጋል፡፡ በእንጀራው ውስጥ የሚጨመር የሻገተ እንጀራ ደግሞ አፍላቶክሲን በተባለው ንጥረ ነገር አማካኝነት ጉበት ላይ ጉዳት ያደርሳል፡፡ ይህ ደግሞ የገቡት ካንሰርን ሊያስከትልም ይችላል›› ብለዋል ዶ/ር አሚር፡፡

ደቡብ ጎንደር ዞን እብናት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ መዘርፋ ታውቋል ።


ደቡብ ጎንደር ዞን እብናት ወረዳ ዛሬ ምሽት ማለትም በሐምሌ 22 /2008 ዓ.ም ለሐምሌ 23/2008 ዓ.ም አጥቢያ የፖሊስ ጣቢያ መጋዘን መዘርፋ ታውቋል ።ማንነታቸው ባልታወቁ ሰውች የተዘረፈው መካዝኑ የተለያዩ የጦር መሳሪያወችንናየፖሊስ አልባሳትን እንዲሁም የፖሊስ መገልገያ ቁሳቁሶችን የያዘ እንደነበር ታውቋል ።ዛሬ እስከ እኩለ ቀን ድረስ በወረዳው ፖሊስ አዛዥ ንጉሴ የሚመራ ቡድን የመሳሪያ ቆጠራ እያደረገ ሲሆን 12 ክላሽንኮፍ መሳሪያ አለመኖራቸው ተረጋግጧል።
ይህ የመሳሪያ ዘረፍ በሰሜን ጎንደር የተጀመረው የማንነት ጥያቄ በተነሳው አመፅ ጎንደር ውጥረት ውስጥ ባለችበትና ነገ ማለትም ሐምሌ 24/2008 ዓ.ም በሚካሄደው ህዝባዊ አመፅ ድራር ላይ መሆኑ የወረዳው ና የዞኑ አመራሮችን ድንጋጤ ውስጥ ከቷል ።አንጋጋሪነቱም ጨምሯል ፤እስካሁን በድርጊቱ የተጠረጠሩ ሰወችን ለማደን የአመራሮቹ አይን በምሽቱ የጥበቃ ዘብ ያደረው የፖሊስ አባል ላይ አፍጥጠዋል ።

በጎንደር የሚካሄደውን ሰልፍ ለማደናቀፍ ሕወሓት እየተሯሯጠ ነው። ሕወሓት ተሸብሮ ሕዝብን ለማሸበር አየተንደፋደፈ ነው።


በጎንደር የሚካሄደውን ሰልፍ ለማደናቀፍ ሕወሓት እየተሯሯጠ ነው። ሕወሓት ተሸብሮ ሕዝብን ለማሸበር አየተንደፋደፈ ነው።
በጎንደር ተሰማርቶ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ ባጠቃላይ ነገ የሚካሄደዉን የጎንደርን ሰልፍ ተነተርሶ የተሰጣቸዉን ሰላማዊ ሰልፍ የማክሸፍ ሴራ ያለማቀበላቸዉን የሚጠቁሙ መረጃዎች ደርሰዉናል።
በወልቃይት የዐማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴዎች ላይ የሚደርሰውን አፈናና ግድያ እንዲቆም የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በጎንደር ከተማ እሁድ ሐምሌ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. መላው አማራ ታሪካዊ ሰልፍ ያደርጋል ፡፡ በጎንደር የሚካሄደውን ሰልፍ ለማደናቀፍ ሕወሓት እየተሯሯጠ ነው።ሕወሓት ተሸብሮ ሕዝብን ለማሸበር አየተንደፋደፈ ነው። ነገ እሁድ ሃምሌ 24 2008 በጎንደር ከተማ የሚደረገው ሕዝባዊ ተቃውሞ እንዳይደረግ የሕወሓት ኣገዛዝ በከፍተኛ ደረጃ እየሰራ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል። ምንጮቹ እንዳሉት በዚህ ሳምንት ሕዝቡን በስብሰባ ለማታለል ቢሞክሩም በፍጹም ሊበገርላቸው ስላልቻለ ያለው እድል የሕወሓት ሰራዊትና የኣማራ ክልል ፖሊስን በጋራ በጎንደር ከተማ ማስፈርና ወደ ከተማዋ የሚያስገቡ መንገዶችን መዝጋት ነው።
Minilik Salsawi's photo.
በዚህም መሰረት በክልሉ የፖሊስ ከፍተኛ ባለስልጣናት የተመራ ኣንድ የግብረ ሃይል ቡድን በስሩ 8 ቲሞችን በማዋቀር ከባህር ዳር ተነስቶ ጎንደር የገባ ሲሆን ይህ የኣማራ ክልል የፖሊስ ቡድንን ከጀርባው ሆኖ ለመንቀሳቀስ ከኣይከል ሳርባ ወታደራዊ ካምፕ የሕወሓት ሰራዊቶች ጎንደር ከተማ የገቡ ሲሆን በጎንደር ዙሪያ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ ፍተሻ የሚካሄድ ሲሆን ከከሰኣት በኋላ ጀምሮ በተለያየ ምክንያት ወደ ጎንደር የሚገቡ መኪኖች እንዳይገቡ እንዲደረግ ለሕወሓት ሰራዊቶች ትእዛዝ ተሰጥቷል።ይህ የሚያሳየው የሕወሓት ኣገዛዝ ከፍተኛ ሽብር ውስጥ እንደገባና ህዝብን እያሸበረ እንደሆነ ነው። በጎንደር ይካሄዳል የተባለው ሰልፍ ለኣምባገነኖች ታላቅ ሽብር መፍጠሩ በየሚዲያዎቻቸው እየለፈፉ የሚገኙት ፕሮፓጋንዳ በቂ ማረጋገጫ ነው።እሁድ ሐምሌ 24 ቀን 2008 በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ መላው አማራ ታሪካዊ ሰልፍ ያደርጋል::

የህወሃት አድሏዊና አምባገነናዊ አገዛዝ “በቃኝ”በማለት ህዝባዊ ተቃውሞ እየተቀጣጠለ ነው


የተቃውሞ ጎራውም ቢሆን ከዚህ ከፋፋይ የጥፋት ድግስ ያለመትረፉን ብዙዎቹ ተቃዋሚዎች የወቅቱን የኢትዮጵያ ሁኔታ በሚመለከት ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በሚሰጡት ትንታኔና በሚያቀርቡት መፍትሄ በአብዛኛው መሰረታዊ ጉዳዮች ሳይለያዩ በጋራ አገራዊ አጀንዳ ላይ ተባብረው በመስራት ህወኃት የሰበረውን የግንኙነት ድልድይ ለመገንባትና አገርና ህዝብን ለመታደግ በቃላቸው ለመገኘት ባለመቻል ደጋግመው መክሸፋቸው በግልጽ ይታያል፡፡
ይሁን እንጂ ከዓመት በላይ የዘለቀው የሃመር ወጣቶች የፍትህና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ፣ ዓመት ሊደፍን የተቃረበው ኦሮሚያ -አቀፍ ህዝባዊ እምብተኝነትና የመብትና የዲሞክራሲ ጥያቄ ፣ በኮንሶ የተነሳው የማንነት ጥያቄ፣ በአሁኑ ወቅት ከወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በጎንደር ተነስቶ በአማራ ክልል በፍጥነት እየተዛመተ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ፣ እንዲሁም በመላው አገሪቱ በሁሉም ክልል የሚታየው የህወኃት አድሎኣዊና አምባገነናዊ አገዛዝ ‹በቃኝ› በማለት በተናጠልና በተበጣጠሰ መልክ ፣ ግን በቆራጥነት፣ ያለማቋረጥና ማፈግፈግ እየተቀጣጠለ ነው ፡፡
ይህ አገር-አቀፍ የእምቢተኝነት ህዝባዊ እንቅስቃሴ ፣ እንዲሁም ከያቅጣጫው ከህዝቡ የሚሰማው የትግል አጋርነት ጥሪና በአንድ የጋራ ጥያቄ ዙሪያ የመሰባሰብ መንፈስ፣ ህዝቡ ከፓርቲዎች ቀድሞ ሄዷል የሚያስብል ነው፡፡ ለተቃዋሚ ጎራውም ትግሉን የማስተባበርና በአንድ አገር-አድን አጀንዳ ስር ለማሰለፍ አብሮ የመስራትን ወቅታዊነትና አስፈላጊነት እንዲሁም ከመቼውም ጊዜ በላይ ተግባራዊ ምላሽ እንደሚጠይቅ ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል ፡፡ በእጅጉ የሚያበረታታ ነው፡፡
በተቃራኒው ህወኃት/ኢህአዴግ በአምባገነናዊ ተግባሩ ገፍቶበት የዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብት በጠብመንጃ ኃይል ለማፈን፣በዚህ የከፋ ወቅት ዜጎችን መኖሪያ አፍርሶ በኅልውናቸውና ሰብአዊ ክብራቸው ላይ መቀለዱንና… የተያያዘውን የግፍ መንገድ አጠናክሮ ለመቀጠል እየተንገታገተ ይገኛል፡፡ ሌሎች የቀድሞ ሕወኃታዊያንን ጨምሮ አምባገነናዊ አገዛዙ በሞት አፋፍ ላይ መሆኑን ገልጸው ለህገመንግስታዊ የምርጫ ስርዓት ምስረታ መወትወት ጀምረዋል፤ ይህም የተጨባጭ ሁኔታና በህወኃት ውስጥ ያለውን መከፋፈል አመላካች ነው፡፡ በአጭሩ የአገራችንን ተጨባጭ ሁኔታ በጤናማ አዕምሮ ለሚመዝን ኢትዮጵያዊ ዜጋ የመንግስት ደጋፊም ሆነ ተቃዋሚ ያለው አምባገነናዊ አገዛዝ በያዘው የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ፣ ወታደራዊ ኃይልና የአፈና ስልት ሊቀጥል የማይችል፣ ያለው የጥቂቶች ዘረኛ ቡድን ዕድገቱን ጨርሶ በጣረ-ሞት ላይ እንደሚገኝና ለውጡ አይቀሬ መሆኑን መረዳት አይቸገርም ፡፡ በዚህ ረገድ ከህዝባችን ፊት ሁለት ግልጽ አማራጮች ቀርበዋል፡፡
የመጀመሪያው ሁላችንን አሸናፊና ተጠቃሚ ከሚያደርግ ዘላቂ ሰላማዊ መፍትሄ የሚያደርስ ሲሆን ሁለተኛው ያለውን አስተዳደር በአፈናና በኃይል ወደከፋ አምባገነናዊ ወታደራዊ አገዛዝ የሚያሸጋግር ወይም ባይወደድም በጠመንጃ ያለውን አምባገነናዊ አገዛዝ የሚያስወግድ አሉታዊ የኃይል አማራጭ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን ይህን በህዝቡ መካከከል የተሰራጨውና ህዝቡን የከፋፈለውን ህወኃት ሰራሽ የልዩነት ግንብ ለማፈራረስ፣ መርዙን ለማርከስ አደጋ የተደቀነበትን የአገርና ህዝብ አንድነትና ኅብረት ያስተሳሰሩ ታሪካዊና ባህላዊ ጠቃሚ እሴቶች ማስቀጠል የግድ ይለናል፡፡ ለዚህ ደግሞ ሁሉን አሳታፊ ውይይት በማድረግ ብሄራዊ መግባባት መፍጠር ዕርቅ ማውረድና በአካታችና አሳታፊ የሽግግር ወቅት የተሰበረውን የአንድነት ድልድይ ገንብቶ ዘላቂ ሰላምና ፍትሃዊ ልማት የምንገነባበት የሁላችን ለሁላችን በእኩል የሚያገለግል፣ በቀደመው መቃብር ከሚገነባ በኃይል ላይ የተመሰረተ የሥልጣን ሽግግር በተለየ ፣ ወደ አዲስቱን ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የመገንባት ሂደት የሚያደርሰን የሽግግር ወቅት /መንግስት መመስረት ብቸኛው ዘላቂ መፍትሄ ነው፡፡
የድርጅታችን ምርጫ የመጀመሪያው ሰላማዊው መንገድ / አማራጭ በመሆኑ ለመንግስትና ደጋፊዎቹ፣ በአገር ቤትና በውጪ አገር ለሚገኙ የተደራጁና ያልተደራጁ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ የሚከተለውን ጥሪ ያስተላልፋል ፡፡ ገዢው ፓርቲና መንግስት፡- ኢትዮጵያዊያን በአገሪቱ የከፋፍለህ ግዛው ፖሊሲ ውጤት የሆነውና በስፋት የተሰራጨው የዘርና የጥላቻ ፖለቲካ እንዲያበቃ፣ በታሪክና መንግስት ምስረታ ሂደት የተፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ እንዲበጅላቸው…. በአገራዊ ጉዳዮች የጋራ መግባባት ለመፍጠር…. የሚያስችል አገራዊ የሰላምና ዕርቅ ጉባኤ እንዲካሄድ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም ‹‹ ማን ከማን ተጣላና ነው፣ ይህ የተቃዋሚዎች አቋራጭ የሥልጣን ጥያቄ ነው….›› በማለት በእብሪት ሲታሾፉ መቆየታችሁ ይታወቃል፡፡
አሁን ላይ ግን ሌላው ቀርቶ በህወኃት/ኢህአዴግ ውስጥና መካከል የተፈጠረው ልዩነት በለመዳችሁበት መንገድ ሊትሸፍኑትና ሊታለባብሱት ከሚችሉት በላይ መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ በመሆኑም እየተጠየቀ የቆየው አገራዊ የሰላምና እርቅ ጉባኤ የናንተም ጥያቄ ከሆነበት ደረጃ መድረሱን ተቀብላችሁ ከእብሪታችሁ ተላቃችሁ ጥሪውን እንድትቀበሉ፤ የመካከለኛውና ዝቅተኛው አመራርና ካድሬ፣ እንዲሁም ደጋፊዎች ጥሪያችን ከፓርቲና ጊዚያዊ ጥቅም በላይ የአገርና ህዝብ ህልውናና ቀጣይ ግንኙነት የሚወስን ስለሆነ ራሳችሁን ከህዝብ ጎን አሰልፋችሁ ታሪካዊ ገድል እንድትፈጽሙ ፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፡- ከዚህ በፊት በአገርቤት የሚገኙ ብዙዎች በጋራ ሆነን – ‹‹ አንድም አገራዊ ፣ አካባቢያዊ/ክልላዊ ወይም የብሄረሰብ የፖለቲካ ድርጅት ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ ለዚህች አገር ውስብስብ ችግሮች በተናጠል ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጣ አይችልም ››ከሚል ድምዳሜ በመድረስ በጋራ አገራዊ ጉዳዮች በኅብረት መስራት አስፈላጊና ወቅታዊ መሆኑን በተደጋጋሚ ሰንገልጽ ፣ እንዲሁም በአገር-ቤትና በውጪ አገር ስለብሄራዊ መግባባትና ዕርቅ ስንሰብክ መቆየታችን ይታወቃል፡፡
ለዚህም በጋራ ለመስራት በተደጋጋሚ ሙከራ አድርገን ከተጠናወተን ‹‹ መጀመር እንጂ ከዳር ማድረስ የማያስችል ደዌ›› ሊንፈወስ ባለመቻላችን በተደጋጋሚ ከሽፈናል፡፡ ስለዚህ ሁላችንም ከእስከዛሬው ተሞክሮ ቀስመን፣ ያለንበትን ወቅታዊ አደጋ ተረድተን፣ ባለፈው መቃብር ላይ አዲሱን ከመገንባት አስተሳሰብና ልምዳችን ተፋተን፣ ከተናጠል ሩጫና የጎንዮሽ ፍትጊያ ወጥተን፣ የትግል ስልትና ሌሎች ልዩነቶችን እንዲሁም የፓርቲ ፕሮግራምና የሥልጣን ጥያቄን ወደኋላ አቆይተን ፣ ከመርዶ ነጋሪነትና መግለጫ ማውጣት ተሻግረን፣ከቢሮ ወጥተን ህዝባችን ውስጥ በተግባር በመድረስ በ ‹‹አገራዊ የሰላምና ዕርቅ ጉባኤ›› ጥያቄ ዙሪያ ተሰባስበን ህዝቡን በጋራ ለማስተባበርና ለማታገል አመራር በመስጠት በገዢው ፓርቲ ላይ የምናሳርፈውን ተጽዕኖ እንድናጠናክር፤ በአገር ውስጥና በውጪ አገራት የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በተለይም በዚህች በተፈጥሮ የታደለች ግን ደሃ አገር፣ በህዝብ ሃብት ቀለም የቆጠርን ‹ምሁራንና ልህቃን› ፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ባህላዊ መሪዎች . . . የህዝቡ የትግል ተነሳሽነትና ዝግጁነት እንዲሁም አገራችን ያለችበትን ተጨባጭ ሁኔታና የተጠየቅነውን የማስተባበር ኃላፊነትና ተግባር በማገናዘብ – የተደራጀን በየተደራጀንበት የሲቪልና ሙያ ማኅበራት ፣ ያልተደራጀንም በየተሰማራንበት የሙያና የሥራ ዘርፍ፣ አገራችን ከገባችበት አዘቅት ለማውጣት፣ ከተደቀነባት አደጋ ለመታደግ ብቸኛው መፍትሄ የብሄራዊ መግባባትና እርቅ መንገድ መሆኑን ህዝቡን በማስተማር ፣ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች- ገዢውም ተቃዋሚውም ወደ አገራዊ መግባባትና ዕርቅ መድረክ እንዲመጡ – አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ፣ አገር የምትጠይቀውን ዋጋ ለመክፈል እንድትወስኑ፣ በተግባር እንድታሳዩ፤ አገራዊ ጥሪያችንን ስናስተላልፍ ይህ ጥሪ የሚጠይቀው ተግባር የነገ ሳይሆን የዛሬ መሆኑን በአጽንኦት እናሳስባለን ፡፡ ለዚህ አማራጭ ተፈጻሚነት ድርጅታችን የሚቆጥበው አንዳችም እንደሌለና የቱንም መስዋዕትነት ለመክፈል ስላለው ዝግጁነት የገባውን ቃልኪዳን ደግመን እናረጋግጣለን፡፡ በሁሉም ልጆቿ ፣ ለሁሉም ልጆቿ የምትመች አዲስቱ ኢትዮጵያ ትገነባለች//
የኦሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት/ኦሕዲኅ/ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ፤ ሃምሌ 22/ 2008 ፤ አዲስ አበባ

አጋጣሚውን መጠቀም ብልህነትና ማስተዋል ነው ! ከአዲስ አበባ ወጣቶች የተላከ መልእክት


አገር ሰላም's photo.
አሁን የደረስንበት ሰዓት በኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ ያለውን እውነተኛ ስሜት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው ህዝባዊ እንቢተኝነቱ ከጫፍ ጫፍ በሚባል መልኩ እየተቀጣጠለ ይገኛል። በውስጥም በውጭ ይህንን እንቅስቃሴ ለድል ለማብቃት ትግሉን የጋራ ማድረግና በጥበብ መምራት ግድ ይላል። ከአፋኞቻችን ውልደት ጀምሮ በብሔር በክልል በፖለቲካዊ ቡድን እየተቧደንን በሰላማዊ መንገድም ሆነ በአመጽ በተናጠልና ህዝቡን ባላማከለበት መንገድ ስናካሂደው ቆይተናል ውጤቱ ግን ዋናዎቻችንን መገበርና የአፋኙን ሥርዓት እድሜ ማራዘም ነው።
“የብዙ ኪሎ ሜትር ጉዞ በአንድ እርምጃ ይጀመራል” ጉዞውን ለማስካት ደግሞ የጉዞ አቅጣጫውን መያዝ ግድ ይላል። ነፃነታችንን ለማስመለስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ በአስቸኳይ ታዋቂ ፖለቲከኞችን ምሁራንን የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን የሚዲያ ሰዎችን በህብረተሰቡ ተደማጭ የሆኑ ታዋቂ ሰዎችን ያካተተ ቡድን ተመስርቶ ትግሉ ሊመራ ግድ ይላል መከፋፈል ይቁም የአብዛኛው የትግል እንንቅስቃሴ ነፃነታችንን ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቻችንን ማስከበርና ተከባብረን በሰላም የምንኖርባት ሉዓላዊነቷ የተከበረ ሀገር እንድትኖረን ነው።
የአባቶቻችንን ክብር እንዉረስ ተዋርደናልና ክብራችንን እናስመልስ ! ሀገር እያለን ባይተዋር ሆነናልና እንተባበር ! ይህንን ከጫፍ ጫፍ ያለ ህዝባዊ እንቢተኝነት ተባብረንና ተከባብረን እንምራው ልዩነቶች ካሉ ከድል በኋላ በሰለጠነ መንገድ በአግባብ በጠረንጴዛ ዙሪያ ተወያይተን እንፍታ እርስ በእርስ ተጋጭተን ሀገራችንን አደጋ ላይ እንዳንጥል በማስተዋል እንራመድ።
ከአዲስ አበባ ወጣቶች የተላከ መልእክት

Friday, July 29, 2016

ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ ከጎጃም ሕዝብ የተላከ


የወያኔ መንግስት በአንተ በውዱ ወገናችን ላይ ከጥቂት ሳምንታት ወዲህ እየፈፀመ ያለውን የማን አለብኝነትና የእብሪት ተግባር በቁጭትና በእልህ እየተከታተልንና ከአንተ ወገናችን ጎን በመቆም ያለንን አጋርነት እየገለፅን ቢሆንም፣ ይህንን የእናት ጡት ነካሽ የሆነውን የዘረኛና የፋሽስት መንግስት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጠራርጎ ለማስወገድ ተግባራዊ ስራዎችን ተባብረን መስራት ስለሚጠበቅብንና የመይሳው ካሳና ልጆች ሲጠቁ የበላይ ዘለቀ ልጆች አርፈው አይተኙምና የሚከተሉትን ነጥቦች በማንሳት የትግል አጋርነት መልዕክታችን ይድረሳችሁ እንላለን።
1. የብአዴን አመራር አባላት (እንደ አለምነው መኮንንና ብናልፍ አንዷለም) ሌሎችም ከአማራው ይልቅ ለሆዳቸው አድረው ከወያኔ ጋር በተሰለፉ የአማራው ካድሬዎች ላይ ሁሉ የማያዳግም ርምጃ መውሰድ፤
2. የስርዓቱ ተጠቃሚ በሆኑ በወያኔ/ብሕአዲን የንግድ ተቋማትና ጥቅማ ጥቅሞች ላይ እንዲሁም ከአንዱ አካባቢ ወደሌላው አካባቢ በሚንቀሳቀሱ የስርዓቱ የንግድና የግል ተሽከርካሪዎች ላይ ርምጃ መውሰድ፤
3. ታፍነው የተወሰዱ የወልቃይት ጠገዴ የማንነት አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ካልተለቀቁ፣ በምትኩ የወያኔ ገዥ አባላትንና ቤተሰባቸውን አፍኖ በመውሰድ መደራደሪያ ማድረግ፤
4. ከአሁን በኋላ ለሚሰነዘርብን ማንኛውም ጥቃት ሁሉ አፀፋዊ ምላሻችን እጥፍ ድርብ መሆን ይኖርበታል፤ እነሱም የያዙት እንደኛው ነፍስ ነውና ለሚሰነዝሩት ጥቃት ማንኛውም ዜጋ በተጠንቀቅ በመቆም አይቀጡ ቅጣት ልንቀጣችው ይገባል። ጀግንነትን ተወልዶ ያደገው ከእኛው ዘንድ መሆኑን ቢያውቁትም የበለጠ ማንነታችንን ልናስተምራቸው ይገባል።
5. እነሱ ያላከበሩትን ሕግ ሌላው ዜጋ እንዲያከብረው ደጋግመው የሚጠይቁትን፣ ድርድርና ሽምግልና እያሉ ጊዜ ለመውሰድና ትግሉን ለማኮላሸት የሚጠቀሙበት ስልት ስለሆነ ካለፈው ተምረን በዚህ ሳንታለል ጊዜያችንን በስር-ነቀል ለውጥ እንጂ በጥገናዊ ለውጦች እንዳንታለል።
6. የወያኔ መንግስት መሳሪያችንን ለማስፈታት እያሴረ በመሆኑ፣ ይህን ለማስፈፀም የሚንቀሳቀስ ሰራዊት ከመጣ ውረድ እንደውረድ ተባብለን በምናውቀው ተራራ ዋሻና ቀዳዳ መፋለም ይኖርብናል። በቁማችን ከሞትን ቆይተናል፤ የወልቃይት ጠገዴና የጠለምት ሕዝብ 36 ዓመት ተገድሏል፣ ታስሯል፣ ተሰዷል በአካል ያለውም መሬቱን ተነጥቋል፤ የተቀረው ሕዝብም መንገድ ከፍቶ ላሳለፋቸው ውለታ 25 ዓመታት በሙሉ የሰቆቃ በትራቸውን አሳርፈውበታል። ጣሊያንም ከዚህ የበለጠ በወገናችን ላይ አልፈፀመም።
7. ማንነቱን እንዲረሳ ወደ ትግራይ በግዳጅ የተካለሉ አካባቢዎችን ሆን ተብሎ ወደ ትግርኛ ስያሜ እየተቀሩ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሕዝቡ በነዚህ ስሞች በምንም ዓይነት እንዳይጠቀም ተገቢው ቅስቀሳ መካሄድ አለበት።
8. ለወሎ ወገናችን፣ ግዛትህ ተቆርሶ እንደ ጎንደር ተወስዶ፣ ክብርህ ተዋርዶ፣ ማንነትህ ተንቆ እንደ ስልቻ እየታሰርህና እየተፈታህ ባለህበት በዚህ ፈታኝ ወቅት ከጎንህ አለንና ተነስተህ ከጎንደር ወገናችን ተሰልፈህ የተነጠቅኸውን መሬት ለማስመለስ ተነስ። ሁሌም የማታሳፍረን የሸዋ ወገናችን ለጥሪያችን በተንቀቅ ተዘጋጅተህ ጠብቀን።
9. የአማራ የመከላከያ ሰራዊት ሆይ፣ መሳሪያህን በአማራ ሕዝብ ላይ በማንሳት ይቅርታ የማይደረግለት ስህተት እንዳትፈፅም፤ የመሳሪያህን አፈሙዝ በወያኔና በግብረ በላው ብሕአዲን ላይ እንድታዞር ጥሪ አቅርበንልሃል።
10. ዋናው ግባችን የወያኔ/ኢሕአዲግ ፋሺስታዊ መንግስትን መገርሰስ በመሆኑ፣ ለማይቀረው ድል አብረን እንሰለፍ። እስከ መጨረሻው የደም ጠብታ ከጎንህ ነንና ትግላችን በድል ሳይጠናቀቅ አርፈን እንደማንተኛ ልናረጋግጥልህ እንወዳለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤


በሰመረ አለሙ
በምንኖርበት በምእራቡ አለም ዜጎች ከምርጫ በፊት መሪዎቻቸዉን ይገመግማሉ፤ያለፈ ታሪካቸዉን፤ልምዳቸዉን፤ማህበራዊ ተሳትፎዋቸዉን በተለይም ሀገር ወዳድነታቸዉን ከግምት ከተዉ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች አንጻር ለቦታዉ ብቁ መሆናቸዉነ መርምረዉ መዝነዉ ይመርጣሉ። በዚህ ሁኔታ የተመረጠ መሪ መልካም ስነምግባር ይኖረዋል; ለአላማዉ የጸና ይሆናል;አድልዎን ይጠየፋል፤መልካም አስተዳደርን ያሰፍናል፤ ለአገር ዘላቂ ጥቅም ለማስገኘት በርትቶ ይሰራል ፤ሃላፊነቱንም በብቃት ይወጣል። የዚህ ጽሁፍ አንባበዎችም ይህ አሰራር ከማይተገበርበት ከምስራቁ፤ ከአረቡ አለምና ከአፍሪቃ ሀገሮች ኮብልለን ይህን በሚያራምዱ በምእራብ አገሮች ተጠልለን በምንፈልገዉ ምርጫ የምንፈልገዉን ተወዳዳሪ እየመረጥን ያለንበት ሀገር የሰጠንን መብት እያጣጣምን እንደምንኖር በእርግጠኝነት መናገር ከማስቻሉም በላይ ይህ አሰራር ወደ አገራችን የሚደርስበትን ሁኔታም በአይነ ህሊና እያየን እንገኛለን እንጥራለንም።
ታዲያ የጽሁፌ መንደርደሪያ ይሄ ሁኖ ዛሬ በፖለቲካዉ ምህዳር ከሀገር ቤት ዉጭ ድርጅት መስርተዉ ጦር ሰብቀዉ የተነሱትን የድርጅት፤የፖለቲካ፤እና የጦር መሪ የሆኑትን ዶር ብርሀኑን ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ ዜጎች በልባቸዉ ያለዉን ወደ ዉጭ እንዲያወጡ ለመጋበዝ በይዘቱ ልዩ ሊሆን ይችላል ብዬ ያሰብኩትን ጽሁፌን ለአንባቢ አቅርቢያለሁ። በእርግጥ ይህ ሙከራ አዲስ አይደለም ቀደም ባለዉ ጊዜ ዶ/ር በየነ ጴጥሮስን ግርማ ካሳ በተባ ብእሩ ሲጎበኛቸዉ አሰፋ ጫቦም ተደርቦ ዶክተሩን ከዉስጥ ወደ ዉጭና ከዉጭ ወደ ዉስጥ እንድናይ ረድቶናል ክፋቱ አቶ አሰፋ ጫቦም ከዚሁ ፍላጻ አላመለጠም።
የጽሁፉ ዋና አላማ በመሪነት ስም የሚመጡትን ግለሰቦች ለመተናኮል ሳይሆን ለመሪነት ከመብቃታቸዉ በፊት በሚገባ ይገምገሙ ለማለት ነዉ። እንደ ልማድ ሁኖ በህይወት የሌሉትን ብቻ ከማብጠልጠል በህይወት ስላሉ የድርጅት መሪዎች ስብእና፤ብቃት፤ችሎታ ተመሪዉ ህዝብ በቂ ዘገባ ያስፈልገዋል ብዬ አምናለሁ። ገብሩ አስራት፤ሌንጮ ለታ፤አረጋዊ በርሄ፤አንዳርጋቸዉ ጽጌ፤ብርሀኑ ነጋ፤ሰየ አብረሀ፤ኢያሱ አለማየሁ፤አሰፋ ጫቦ፤ኤርምያስ ዋቅጂራ የመሳሰሉ ግለሰቦች ድርጅት መስርተዋል ወይም ደግሞ በተመሰረተ ድርጂት ዋና ተዋናይ ነበሩ ድርጅታቸዉም ዉስጥ ከፍተኛ ተሳትፎም አድርገዋል አንዳንዶቹም ድርጅታቸዉ በለስ ቢቀናዉ ኢትዮጵያን ይረከቡ ነበር። ከእነዚህ መሀልም ዛሬ ፍዳችንን የሚያበላንን የህወአትን መሰረት የጣሉ ወይም ደግሞ ቀደም ባለዉ ስርአት ተዋናይ የነበሩ መሆናቸዉን ከ30 እስከ 85 የእድሜ ቅንፍ ዉስጥ ያለን በሚገባ እናዉቃለን። በእንጻሩም እነዚህ ግለሰቦች ዛሬ መሰረቱን የጣሉለትን የህወአትን መንግስት በእነሱ ፊታዉራሪነት እንድንጥለዉ ያሳስቡናል። የዚህ ጽሁፍ መክፈቻ ዶ/ር ብርሀኑ ቢሆኑም ሌሎችንም እንዲሁ ቀሪዉ ኢትዮጵያዊ እንዲጎበኛቸዉ እያሳሰበኩ ዘገባዬን በሚከተለዉ መልኩ አቀርባለሁ።
ከ60ዎቹ (የምን እንቅስቃሴ ብየ እንደምጠራዉ ቸግሮኝ ነዉ) ባሉት እንቅስቃሴዎች ሁሉ የዶ/ር ብርሀኑ ስም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያልተጠቀሰበት እሳቸዉም በተለያየ ክብደት እጃቸዉን ያላስገቡበት እንቅስቃሴ ይኖራል ብሎ መገመት አስቸጋሪ ነዉ። ቀደም ባለዉ ጊዜ በኢህአፓ ቀጥሎ በቀስተ ዳመና ቀጥሎ በቅንጂት ቀጥሎ በጂ7 ጎልተዉ የታዩ ተዋናይ ናቸዉ። እዚህ ላይ የዶ/ር ብርሀኑ ስም መነሳት ያስፈለገበት ዋናዉ ምክንያት አንድን ድርጅት መርተዉ ኢትዮጵያን ነጻ አዉጥተዉ መሪ ለመሆን በእንቀስቃሴ ላይ በመሆናቸዉ ተመሪዉ ህዝብ ስለኝህ ሰዉ አንስቶ መጠየቅ ፤መተቸት ፤ መመርመር፤ሀሳብ መስጠት እንዲችል ለመጋበዝ ነዉ።
ዶር ብርሀኑም የምእራቡን አለም ዲሞክራሲ በሚገባ በማወቃቸዉ ተመሪዉ ህዝብ መሪዉን ለመተቸት ሀሳብ ለመስጠት ሙሉ መብት እንዳለዉ በሚገባ እንደሚረዱም እገምታለሁ። እዚህ ላይ እያንዳንዳችን ወደ ስራ ስንቀጠር ስለ ግል ህይወታችን፤ ችሎታችን፤ለስራዉ ብቁ መሆናችንን ቀጣሪዎቻችን እንደሚገመግሙን ማለት ነዉ። አንድ ቁማርተኛ በክፉ ሱስ የተጠመደ፤ የቤተሰብን ዋጋ ክብር የማይሰጥ ወይም ሌላ አስነዋሪና አስከፊ ጸባዮችና ልምዶች ያሉበት ይህ ጸባዩ በተለያየ መልኩ ስራዉ ላይ ስለሚንጸባረቅ እንዲህ ያለ ግለሰብ ለትልቅ ስራ ቢታጭ ከልማቱ ይልቅ ጥፋቱ ስለሚያመዝን መሪዉን የሚመረጥ ዜጋ ያለፈ ታሪኩን የመመርመር ግዴታ ይኖርበታል ተብሎ ስለሚታመን ነዉ። (ለፍርድ የምትቸኩሉ አንባቢዎቼ እሳቸዉን ማለቴ አይደለም ምሳሌዉን ነዉ)።
ከላይ ለመግለጽ እንደሞከረኩት በያለንበት በምእራቡ አለም እንደምናዉቀዉ አንድ መሪ ለመሪነት ሲቀርብ ዜጎች የመምራት ብቃቱን በአስጨናቂ ጥያቄ ይገመግማሉ። ይህ መሪ ለኢኮኖሚ እድገት፤ የስራ አጥነትን ችግር ለማቃለል ፤ለልማት፤ ለማህበራዊ ፍትህ ምን መልስ አለዉ የሚለዉን ለመገምገም ሲሆን ከዚህ አለፍ ብሎም ድፍረቱና ሀገር አደጋ ላይ በወደቀችበት ጊዜ የጦር አዝማች ሁኖ ጦሩን ለድል ማብቃቱንም አብረዉ ይመለከታሉ። ይህንና ይህን የመሳሰለዉ ጥያቄ ለመሪዉ ቀርቦ መሪዉም ብቃቱን በሚሰጠዉ መልስ ባሳለፈባቸዉ ስራዎቹ ለህብረተሰቡ ባደረገዉ አስተዋጽኦ ተለክቶ መራጩ ህዝብ ድምጹን ይሰጠዋል።
እዚህ ላይ ከነገሬ ሳልወጣ ከጥንት ክፍለ ሀገራችን (ኤርትራ) ጋረ በተደረገዉ ጦርነት የጦሩ የበላይ አዛዥ መለስ ዘራዊ ጦሩን ለዉጊያ ልኮ ምንም ሳይረበሺ የተልእኮ ትምህርቱን ፈተና ለመቀበል በእርጋታ ያጠና እንደነበር የጊዜዉ አንጋቾቹ በሗላም ተወርዉረዉ የተጣሉት እነ አለምሰገድ በለቀቁት ጽሁፍ ላይ አንበበናል። በተመሳሳይ ሁኔታ ስታሊንግራድ መያዟ ነዉ ምን እናድርግ ብለዉ ለስታሊን ቴሌግራም ሲያደርጉለት እዛዉ በቆምክበት ምድር ለሀገርህ ሀዉልትህ ሁነህ ሙት እኔም ከአንተዉ ጋር አብሬ እሞታለሁ ብሎ ነበር ለጄነራሉ የመለሰለት። የሁለቱንም ዉጤት አንዱን ከታሪክ አንዱን በአይን ምስክርነት ታዝበናል። ለዚህ ነዉ ለመሪነት የሚመጡ ግለሰቦች የመሪነት ችሎታቸዉ ወደ ወምበሩ ከመድረሳቸዉ በፊት ይገምገም የሚባለዉ። ይህ ብቻ አይደለም በፖላንድ አምድ የስታሊን ልጅ እንደ ማንኛዉም ራሺያዊ ዜጋ በዛ ቀዉጢ ሰአት በመቶ አለቃ ማእረግነት ሀገሩን ለመከላከል የዜግነት ግዴታዉን ሲወጣ በጠላት እጅ ወድቆ ወታደራዊ ምዝገባ ሲካሄድ የስታሊን ልጅ መሆኑን ባለስፈላጊ ሁኔታ ከምረኮኞቹ አንዱ በመናገሩ ጀርመኖች እጃቸዉ የገባዉን አዱኛ በመደራደሪያነት በታሰሩት ጄነራሎች ሊለዉጡ ለስታሊን ከመደወል አልፈዉ ልጁንም በስልክ አገናኝተዉት ነበር። በቀዉጢ ሰአት የማዋጋትና የመምራት ብቃት ያለዉ ስታሊን ግን ደዋይ ጀርመኑ ጀነራል ላይ ስቆ ልጁን ግን ብትሞትም ለሀገርህ ነዉ የሞትከዉ ስምህ ግን አብሮህ አይሞትም ብሎ ነበር የመለሰለት። በዚህ ድርድር እንዳልሆነላቸዉ የተረዱት ጀርመኖች ግን የዚህን መሪ ልጂ ገደሉት ስታሊንም እምባዉን ወደ ዉስጥ ዉጦ ሀገሩን ከጀርመን ወራሪ አዳነ በስታሊንግራድ ዉጊያ የተገኘ ጀርመናዊም ሀገሩን በድጋሚ ሳያይ ቀረ። ይህን ምሳሌ ወደ ሀገራችን ገልብጠን ስናየዉ በዉን የህወአት መሪዎች ከዚህ የተቀራረበ ገድል ለኢትዮጵያ አይደለም ለትግራይ ይሰራሉ? ከተግባራቸዉ አንጻር ግን አይመስልም። ለዚህ ነዉ ለሀገር ዘላቂ ጥቅም የሚሰሩ ሀገር የሚወዱ መሪዎች ይመረጡ የሚባለዉ መሪነት የመድረክ ተዋናይነት ስላልሆነ።
ለጊዜዉ ከሞላ ጎደል የራዲዮ የድህረ ገጽ የቴሌቨዥን አገልግሎት የሚሰጠዉ ኢሳት የተባለዉ የሚዲያ ተቋም ሲሆን ዶር ብርሀኑም እዛ መድረክ ላይ ሲወጡ ጠያቂ እንጂ ተጠያቂ አይመስሉም። ሲሳይ አጌናና ሌሎች ኢሳቶች እንደ አቶ ተክሌ የሻዉ ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ሐይሌን አይነቱንና ዶር ብርሀኑን የሚያዩበት አይን አንድ አይደለም ምንም እንኳን ሁሉም ኢትዮጵያዉያን ቢሆኑም። አርካይቭ ዉስጥ ስላለ የአባባሉን ተአማኒነት ጎልጉሎ ማየት ይቻላል። በእርግጥ ኢሳት ሙሉ በሙሉ በዶር ብርሀኑ ድርጅት ቁጥጥር ስር ቢሆንም ገንዘቡን የሚያዋጡት ግን የድርጅታቸዉ አባሎች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች ኢትዮጵያዉያንም በመሆናቸዉ ሚዛኑን የጠበቀ የሚዲያ አገልገሎት ሊሰጥ በተገባዉ ነበር።
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ተጽፎ ካልተሰጣቸዉ በስተቀር ብዙ ጊዜ ንግግራቸዉ ለተች አጋልጦ ይሰጣቸዋል። አንባቢ እንደሚያስታዉሰዉ ከህወአት መጻፎች ዉጭ ለመጀመሪያ ጊዜ የተቆረጠች ኢትዮጵያን ያየነዉ በዶ/ር ብርሀኑ መጽሀፍ ነዉ ። አለፍ ሲሉ በስብሰባ ላይ በረከት ሰሞን ወዳጄ ነዉ፤ መለስ ዜናዊ የቅርቤ ሰዉ ነዉ ሲሉ ለአቶ ሰየ አብረሀና ወንድማቸዉ ደግሞ በጣም የሳሳ ልብ ያላቸዉ ከመሆኑም በላይ በጽሁፋቸዉም ላይ ደጋግመዉ የእነዚህን ሰዎች ስም ያነሱ ነበር። ሰየ አብረሀ ግን አዉቀዋለሁ ከማለት የዘለለ ነገር አለማለቱንና በረከት ሰምኦንም ባልተወለደ አንጀቱ በመጽሀፉ ላይ በክብረ ነክ አገላለጽ በሳቸዉ ላይ ከማላገጥ በስተቀር ብድራቸዉን ሳይከፍላቸዉ ቀርቷል።
የአማራን ጨቋኝ አባርሬ የትግሬን ጨቋኝ ላነግስ አልፈልግም ያሉት ዶር ብርሀኑ በድምሩ 40 ሚሊዮን ህዝብ ከማስቀየማቸዉም በላይ ማንን ይዘዉ ኢትዮጵያዊ ድርጅት እንደሚመሩም ለማወቅ አዳጋች ሁኗል። እዚህ ላይ አንባቢ እንደሚገነዘበዉ የኦሮሞ ብሄረተኞች የኦሮሞ ህዝብ በእጃችን ነዉ በሚሉበት ጊዜ ከአፋር፤ ጋሙጎፋ፤ባሌ፤ሱማሌ ጋር የቅርብ ግንኙነት የሌላቸዉ ዶር ብርሀኑ ማንን ይዘዉ የኢትዮጵያ መሪ ሊሆኑ እንደሚችሉ ለመረዳት አስቸጋሪ ነዉ። እንግዲህ እነዚህ የተገለጡት ብሄረሰቦች ሲቀነሱ ለዶ/ር ብርሀኑ የሚቀሯቸዉ አነድ 4 ሚሊዮን ህዝብ ቢሆን ነዉ እነሱም ሙሉ በሙሉ እሳቸዉን ይደግፋሉ ብዬ አልገምተም ምክንያቱም እሳቸዉ ያነጣጠሩበት ነገድ በኢትዮጵያ አንድነት ከማንም በላይ ተጠቃሚ እነደሆነ በሚገባ ስለሚታወቅ ነዉ። እንደ እዉነቱ ከሆነ አማራ ገዛ በሚሉበት ዘመን ተመችቷቸዉ የኖሩት ዶር ብርሀኑ በትግሬዉም ዘመን ከላይ በፎቶግራፉ እንደሚመለከተዉ ደስታ በደስታ ሁነዉ ለስልጣን ቀርበዉ በምከርም በምንም ሟቹ መለስ ዘራዊን ያገለገሉ ነበሩ። አንባቢ ከዛ ፈቶ ጀርባ ያለዉን ምስጢር መፍታት ግዴታዉ ነዉ እኔ ግን አባባሌን ይደግፋል ብዬ ለጥፌዋለሁ።
እንግዲህ ለኢሳት ስራ ማስኬጃ ግብጽ ይሄን ያህል ረዳ ሻቢያ ይህን ያህል ረዳ የሚለዉን የጂ7ን የዉስጥ አሰራር ትተን በዚህ ዶር ብርሀኑ አዛዥና ናዛዥ በሆኑበት ኢሳት ከአንድነት ይልቅ ልዩነት፤ ከጥንቱ ከሚያኮራ ታሪካችን ይልቅ አዲስ ታሪክ ፍለጋ የምንኳትንበት፤ ኢትዮጵያዊነትን የሚያቀነቅኑ እንደ ጠላት የሚታዩበት፤ ኢትዮጵያዉያን አይደለንም የሚሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች ትልቅ መድረክ ተሰጧቸዉ በትልቅ ክብር ኢትዮጵያንና አንድነቷን የሚያራክሱበት፤ የሚያዋርዱበት መድረክ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዶር ብርሀኑ/ነአምን ዘለቀ እንደሚመራ አንባቢ በሚገባ ይረዳዋል ብዬ እገምታለሁ። በዚህ ኢሳት በተባለዉ መድረክ በስህተት ኢትዮጵያዊ መንፈስ ያላቸዉ ወገኖች ሲጋበዙ ጥያቄዉ የፖሊስ ምርመራ አይነት ሲሆን ወከባዉና ክብረ ነክ አቀራረቡ መሀከለኛ እድሜን ላለፈ ኢትዮጵያዊ የሚመች አይሆንም። ሆኖም ዶር ብርሀኑ ይህንን እያዩ እርምት ሊወስዱ ባለመሞከራቸዉ እኝህ ሰዉ ወዴት እየሄዱ ነዉ ምንስ አስበዉ ነዉ ብሉ መጠየቅ ግድ ይላል።
ኢሳትና በቀጣይነት ከረንት አፌየርስ የተባለዉ የፓልቶክ (የኮምፒተር) መወያያ መድረክ የዶር ብርሀኑ ድርጂት አቀንቃኞች፤ሻቢያኖች በስድብ ሰናይፐር የሰለጠኑ አባሎቻቸዉን በማሰማራት ኢትዮጵያዊነትን የሚያንሸራሸሩ ወገኖችን ባልተወለደ አንጀት የሚያዋርዱበት መድረክ ሁኖ ሳለ ዶር ብርሀኑ ጊዜ ሲኖራቸዉ እየገቡ የሚስቁበት መድረክ ነዉ ብዬም እገምታለሁ። በዚህ መጠነ ሰፊ ዘለፋ በዚህ ኢትዮጵያዊ ባልሆነ የዉይይት ስልት ዘለፋዉ በእጅጉ የበዛባቸዉ የቀድሞ የቅንጂት አንጋፋዎች ስድቡን አስቁሙሉን ብለዉ በእንባ ቀረሺ ልመና ቢማጠኑም ሰሚ ጠፍቶ ክፍሉ እራሱ በራሱ መክኖ ዛሬ ተሳዳቢዎችም አደብ ገዝተዉ በስራቸዉ አፍረዉ ጥግ ጥግ ይዘዉ ቁመዋል። መቼም ጽናጽል ከጽናጽል ዉጭ ምንም ሊሆን አይችልምና፡፤
እንግዲህ ከዚህ በላይ ያለቸዉን በዚህ መልኩ ካስቀመጥኩ በሗላ ፓርቲያቸዉ በለስ ቀንቶት የወደፊት የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስተር ዶ/ር ብርሀኑ አዲሱ እምነታቸዉ ኢትዮጵያን ከሻቢያ ጋር በመሆን ነጻ እናወጣለን የሚል መሆኑ ከማንም የተሰወረ ካለመሆኑም በላይ አንጋቾቻዉም ደረታቸዉን ሰጥተዉ በአጽንኦት ያለ እፍረት ይህንን ሀሳባቸዉን ያጠናክራሉ። ብዙ ወገኖች አረ ይህን ነገር ቆም ብለን እናስብበት እኛም ያገባናል በሻቢያና በህወአት መሀከል ልዩነት የለም ቢባሉም በከረንት አፌየርስና ኢሳትን በመሳሰሉት የዶር ብርሀኑን እምነት በሚያራግቡ የሚዲያ ተቋማት ሀሳብ ለመስጠት ሲሞከር በረቀቀ የዘለፋ ስልታቸዉ አንተ ወያኔ ነህ በሚል ማስደንገጫ ኢትዮጵያዉያኑን ጥግ ሊያስይዙ ይሞክራሉ። እንደዉም በኢሳትም ሆነ በነዚህ የፓልቶክ መወያያዎች ሻቢያኖቹ የጎላ ቦታ ተሰጥቷቸዉ የአንድነት ሐይሉን ያንገላታሉ።
በኢትዮጵያዉያኑ አካባቢ እየተለመደ የመጣዉ በዳይን ከወዳጂ በተሻለ መልኩ የመንከባከብ ባህል ማዳበር ነዉ። ዶ/ር ብርሀኑ ፤አንዳርጋቸዉ ጽጌ፤ ኤርምያሰ ዋቅጂራ ፤ ተስፋዬ ገ/አብ ፤ሰየ አብረሃ፤አረጋዊ በርሄ፤ገብሩ አስራት…….ከህወአት ጋር በጣም የቀረበ ትሰስር ያላቸዉና አንጋፋዎቹም ምስረታዉ ላይ የመሰረት ድንጋይ የተከሉ መሆናቸዉ እየታወቀ ዛሬም አዋቂ እንደጠፋ ሁሉ ወደ ኢትዮጵያን መንደር ብቅ ብለዉ ነገርን ያሳክራሉ ትግሉም ኢትዮጵያዊ መልክ እንዳይዝ በረቀቀ ልምዳቸዉ ያወነባብዳሉ ። የመጣዉን መንግስትም በአማካሪነት ያገለገሉ በቃችሁ ሳይባሉ ቀርተዉ ዛሬም ነገር ያደፈርሳሉ። ለዚህ ነዉ መሪዎችን የፖለቲካ ሰዎችን ከማምለካችን በፊት የቀድሞ ህይወታቸዉን በትኖ ማወቅ ያስፈለገበት ምክንያት ። ዉሳኔያቸዉ የቤተሰብ ዉሳኔ ሳይሆን ህዝባዊ ነዉ የሚያደርሱት ጥፋት የብዙ ሚሊዮን ህዝቦችን ህይወት ይነካል። በጫት እና በመጠጥ የነበዘ መለሰ ዜናዊ እና ለመሪነት ብቃት የሌላቸዉ የህወአት መሪዎች ወደብን ያህል ነገር አሳልፈዉ ሲሰጡ ምን እንደሆነ እንኳን በቅጡ አልመረመሩትም ዛሬ የኢትዮጵያ ገበሬና ነጋዴ አርሶና ነግዶ ጥረቱን ለጂቡቲ ይሰጣል። ኢትዮጵያን የሚያክል ትልቅ አገር ዛሬ ለጂቡት ማጎብደድ ግዴታ ሁኖበታል አንዴ ዉሀ ላቅርብ አንዴ ለም መሬት ዉሰዱ እየተባሉ ይስተናገዳሉ። እንግዲህ ለዚህ ነዉ መሪዎቻችንን ማንነታቸዉን መርምረን መረዳት የሚያስፈልገን። ህወአት በስብሰባዉ አፈጮሌ ቀጣፊ ባይመረጥ ኑሮ ዛሬ ቢያንስ አሰብ እና 70000 ኢትዮጵያዊ የተቀጠፋባቸዉ መሬቶች ለኢትዮጵያ ሁነዉ ይቀሩ ነበር። ዶ/ር ብርሀኑንም ከዚህ ማእዘን ማየት እንደፈለግሁ አንባቢ ይረዳልኝ።
እንግዲህ ከላይ የተመለከተዉን ብዙ የሚናገረዉን የዶር ብርሀኑን ፎቶ አንባቢ ዉስጣዊ ሰሜታቸዉንና ይፋ ባልሆነ በስልጣን ተዋረድ ከታምራት ላይኔ በላይ ለመለስ ዘራዊ ቀረቤታም እንደላቸዉ ታሳብቃለች ብዬ እገምታለሁ። የዩኒቨርስቲ መምህራኖችም የሕወአት ስራ አገር ማጥፋት መሆኑን ተረድተዉ ስራ ሲያቆሙም ዶር ብርሀኑ ክፍተቱን ሞልተዉ መስራታቸዉ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነዉ ለዚህ ነዉ የመሪዎች ያለፈ ታሪካቸዉ በሚገባ መገምገም ያስፈለገበት።
ዛሬ ኢትዮጵያ በሻቢያ አማካይነት ነጻ ትሆናለች በሚል በከፍተኛ ፖለቲካዊ ክንድ ጠምዝዝ ቅስቀሳ ወገኖች ወደ ኤርትራ እየሄዱ ደብዛቸዉ ጠፍቶብናል። ቀደም ባለዉ ጊዜ ጋዜጠኛ ደምስ ከብዙ በጥቂቱ ሁኔታዉ ተጋልጦ እርምት እንዲወሰድበት ቢጠይቅ የእሩምታ ተኩሰ ከየአቅጣጫዉ ተከፍቶበት መድረክም ተከልክሎ ሳይወድ በግድ የወያኔን እምነት አራማጂ ለሆነዉ ለብርሀኑ ዳምጤ ቀርቦ ተከታይ ሀሳቡን ማሰማቱን የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚከታተል ወገኔ አስደምጦኛል ኢሳት በሩን ክፍት ቢያደርግለት ስንት ጉድ እንሰማ ነበር።
ወይ ዉርደት 100 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢተዮጵያ ሀገርነቷ ባልተረጋገጠዉ ክፍለ ሀገራችን መጫወቻ ትሁን? ዉርደት ከዚህ በላይ የታለ? ደጃዝማች አፈወርቅ፤ጸሐፊ ትእዛዝ አክሊሉ ሐብተወልድ/አብዲሳ አጋ/ገበየሁ ባልቻ/በላይ ዘለቀ /በላይ ቃለ አብ፤ኡመር ሰመታን፤ዘርአይ ደረስ ይህን ሳታዩ ሞታችሁ እድለኞች ናችሁ። የኢትዮጵያ ወታደር በሱማሌ ሲገደል ከረንት አፌርስ ና ኢሳት ርችት ይተኩሱ ነበር አይ ዜጋ አይ ትምህርት። በዉን ተራ ወታደሩ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግሬ ነዉ?፡በዉን ተራ ወታደሩ ወያኔን ሊጠብቅ ነዉ የተቀጠረዉ? እናንተ ምንም ሳታጡ ባንዳ ሁናችሗል እሱ ግን የሚበላዉ አጥቶ ባንዳ ቢሆን ምኑ ይገርማል?
ዶ/ር ብርሀኑ ከኤርትራዉ አስተደደር ያላቸዉ ግንኙነት የበታችና የበላይ ካልሆነና የወዳጂ መንግስት ከሆነ እንደሳቸዉ ቀደም ባለዉ ጊዜ በሀይል ከኤርትራ በመወንጨፍ ኢትዮጵያን ነጻ እናወጣለን ብለዉ ኤርትራ የተጠለሉ ብዙ ወገኖቻችን በእስር በእንግልት ላይ የሚገኙ መሆናቸዉን አምነስቲ ኢንተርኛሽናልና ወጣ ገባ የሚሉ ወገኖች ነግረዉናል። ከነዚህም መሀል ስመ ጥሩዉ ኮለኔል ታደሰና ወጣቱ የቢቢሲ ጋዜጠኛ ዮሴፍ ይገኙበታል። እንግዲህ ፕሮፌሰር ብርሀኑና ነአምን ዘለቀ የኤርትራ መንግስት ወዳጃቸዉ ከሆነ የኤርትራ መንግስተ በፍቃዳቸዉ ወደ ሀገሩ የገቡትን ዜጎቻችን አስፈትተዉ ነጻነታቸዉን ወደሚያገኙበት ሀገር እንዲያሰናብቱልን በኢትዮጵያዉያን ስም ጥያቄዬን አቀርባለሁ።
ቀደም ባለዉ ጊዜ አቶ ሌንጮ ይመስለኛል የጠላት አገር ወደሚለዉ ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ታስሮበት ሰተት ብሎ ገብቶ አስለቅቆ እንደተመለሰ አንድ ጽሁፍ ላይ ተጽፎ አይቻለሁ። እንግዲህ ሌንጮ ከጠላት መንግስት ይህን ካደረገ ለዶር ብርሀኑ ከወዳጂ መንግስት በችግር ላይ የወደቁ ወገኖቻችንን ማስለቀቅ ይከብዳቸዋል ብዬ አልገምትም። ፖለቲካ ተለዋዋጭ ነዉ አቶ አንዳርጋቸዉ የህወአት ባትሪ አብሪ ነበሩ ነገር ተለዉጦ ዛሬ በሚያስሩበት እስር ቤት ታስረዋል፡ ነገር ግን ባለንበት አገር አቶ አንዳርጋቸዉ ይፈቱ በማለት የምንችለዉን ሁሉ ያለእረፍት በማድረግ ላይ ነን። ይህ ስህተት ካልሆነ እርሶም በዛ የታሰሩብንን ወገኖች የማስፋታት የዜግነትና የመሪነት ግዴታ ይኖርቦታል ብዬ እገምታለሁ። እዚህ ላይ ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትላንት ኮለኔል ታደሰና መሰሎቹ ላይ የደረሰዉ በእርሶም ላይ የማይደርስበት ሁኔታ አይኖርም ብዬ እገምታለሁ። ዛሬ ለነሱ የተጨነቅን ሰዎች ለደረሰቦት ችግር ልንደርስ የምንችለዉ እርሶ ለኮለኔል ታደሰና በኤርትራ በእንግልት ላይ ለሚኖሩ ወገኖቻችነን በሚያደረጉት አስተዋጽኦ ልክ መሆኑን በአጽንኦት ማስገንዘብ እንወዳለን። ወደ ኤርትራ ምቾታቸዉን ትተዉ የሄዱ ወገኖች በሙሉ በሀገር ፍቅር ስሜት ተንገብግበዉ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ለማድረግ በመሆኑ ዛሬ እኛ ባለንበት ሀገር ባንታሰርም ልባችን ከነሱ ጋር መታሰሩን ሊያዉቁልን ይገባል ብዬ እገምታለሁ። በዚያ በእንግልት የሚገኙ ወገኖቾን እያዩ እንዳላዩ አልፈዉ ኢትዮጵያን ነጻ አወጣለሁ የሚል አባባል ዉሀ ስለማይቋጥር ካሁን በሗላ ወደ መድረክ ሲቀርቡልን ይዣቸዉ መጣሁ የሚለዉን መልካም ዜና እንጂ ሌላዉን መስማት እንደማንፈልግ እንዲረዱልን እንጠይቃለን።
ለዚህ ጥያቄዎ የኤርትራ መንግስት መልስ ሊሰጥ የማይችል ከሆነ ዉሳኔዎን እንደገና በጥንቃቄ ይመርምሩ እላለሁ። ነገር ባላሰብኩት መንገድ ሂዶ ልዩ ትርጉም ከተሰጠዉ ይቅርታ ከማለት ሌላ ምን ይበላል ቢያንስ ሰዉ አልሞተም ሀሳብ ተንሻፍፎ ሊሆን ይችላል ይሰተካከላል። ለአስተያየት በዚህ ድረሱኝ semere.alemu@yahoo.com
በቸር ይግጠመን
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

Thursday, July 28, 2016

አንድ ህዝብ አንድ ሀገር! (አብርሃ ደስታ)


ሰው ነፃነት ይፈልጋል። ነፃነት ላለመፈለግ ራሱ ነፃነት ይጠይቃል። ስለዚህ ነፃነቱን የሚቃወም አይኖርም። ምክንያቱም ነፃነትን በራስ መቃወም በራሱ ነፃነት ነው። ሰው ነፃ ለመሆንም ላለመሆንም ነፃ መሆን አለበት። ሰው ነፃ ላለመሆን የመወሰን ነፃነት አለው። ዋናው ጉዳይ ዉሳኔው የራስ መሆን አለበት፤ የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሊኖረው አይገባም።
ነፃነት የሰው ነው፤ የራሳችን ሃብት ነው። በሌሎች ጣልቃ ገብነት ሊገደብ ግን ይችላል። ስለዚህ ነፃነታትችን ከፈለግን መጠበቅ ይኖርብናል። ነፃነታችንን ለመጠበቅ ፈፃሚ ተቋም ያስፈልጋል። ፈፃሚ ተቋም ወይ ስርዓት የሚኖረው መንግስት ሲኖር ነው። መንግስት የሚኖረው ሀገር ሲኖር ነው። ሀገር የሚኖረው ህዝብ ሲኖር ነው።
የምንፈልገው ነፃ ህዝብ ነው። ነፃ ህዝብ የሚኖረው ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሲኖር ነው። ዴሞክራሲያዊ መንግስት የሚኖረው የዴሞክራሲ ግንዛቤ ያለው ህዝብ ሲኖር ነው። ግንዛቤ ያለው ህዝብ መብቱ ያውቃል፤ መንግስት አገልጋይ እንጂ ጌታ አለመሆኑ ይረዳል።
ባጠቃላይ ህዝብ የስልጣን ባለቤት ሲሆን ዴሞክራሲያዊ መንግስት ይኖራል። እናም ነፃነቱን ያረጋግጣል። ህዝብ የስልጣን ባለቤት የሚሆነው መንግስትን መቆጣጠር ሲችል ነው። መንግስትን መቆጣጠር ስልጣን መስጠትንና መንጠቅን ይጨምራል።
ህዝብ መንግስትን መቆጣጠር የሚያስችል ዓቅም የሚፈጥረው አንድነት ሲኖረው ነው። ሰለማዊ ህዝብ በጎሳ፣ በቋንቋ፣ በሀይማኖት፣ በአከባቢ ወዘተ ሳይከፋፈል በአንድነት ሲቆም መንግስትን ይቆጣጠራል። በአንድነት መቆም ማለት የግድ አንድ ዓይነት የፖለቲካ ኣቋም መያዝ አይደለም። የራሱ የመሰለውን አመለካከት ይኖረዋል። የሚወሰነውም በአብዛሃ (አብላጫ) ድምፅ ነው። ምክንያቱም ሁሉም ሰው ነፃ ነው።
ስለዚህ ነፃ ህዝብ እንዲኖረን ነፃ መንግስት ያስፈልጋል። ነፃ መንግስት እንዲኖረን የህዝቦች አንድነት ያስፈልገናል። የህዝቦች አንድነት እንዲኖር የሀገር አንድነት መኖር አለበት። ምክንያቱም የሀገር አንድነት ከሌለ የህዝብ አንድነት አይኖርም። የህዝብ አንድነት ከሌለ የህዝብ ስልጣን አይኖርም። የህዝብ ስልጣን ከሌለ ዴሞክራሲ አይኖርም። ዴሞክራሲ ከሌለ ነፃነት አይኖርም። ነፃነት ከሌለ እኩልነት አይኖርም። እኩልነት ከሌለ ፍትሕ አይኖርም። ፍትሕ ከሌለ የህዝቦች አንድነት አይኖርም። የህዝቦች አንድነት ከሌለ የእርስበርስ ችግር ይኖራል። የእርስበርስ ችግር ሀገርን ያፈርሳል። ሀገር ከፈረሰ ምንም አይኖርም።
ስለዚህ ነፃነት ከፈለግን ሀገር ያስፈልገናል። ሀገር ከፈለግን አንድ ህዝብ (የሚተባበር ህዝብ) ያስፈልገናል። አንድ ህዝብ ከፈለግን ነፃነት ያለው መሆን አለበት። ነፃነት የሌለው ህዝብ ወይ ሀገር አይቆምም። ስለዚህ ሀገር እንዲቆም ነፃነት ያስፈልጋል። ነፃነት እንዲከበር አንድ ሀገር፣ አንድ ህዝብ አስፈላጊ ነው።
ጨቋኝ ገዢዎች ግን የህዝቦችን አንድነት አይፈልጉም። ምክንያቱም ህዝብ አንድ ከሆነ፣ ከተባበረ ከስልጣን ያስወግዳቸዋል። ለዚህም ነው ብዙ ግዜ “የከፋፍለህ ግዛ” ስትራተጂ የሚጠቀሙ። ስለዚህ ነፃነት ፈላጊዎች እንዲያሸንፉና የህዝብና የሀገር አንድነት እንዲጠብቁ የህዝቦችን አንድነት አደጋ ላይ የሚጥል ተግባር አንስራ። መከፋፈል ለገዢዎች ይጠቅማል።
አዎ! አንድ ህዝብ አንድ ሀገር ለነፃነት።
It is so!!!

የሕወሓት የሃሰት ክስ ቀጥሏል:: ኦሮሚያን ለመገንጠል በሚንቀሳቀስ አዲስ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ የተጠረጠሩ ተከሰሱ


የኢትዮጵያን አንድነት የማፈራረስና ኦሮሚያን ከፌዴሬሽኑ የመገንጠል ዓላማ ይዞ በህቡዕ ሲንቀሳቀስ እንደነበር በተገለጸው የኦሮሞ አንድነት ግንባር (ዩኤልኤፍኦ) በሚል ስያሜ አዲስ በተቋቋመ ድርጅት፣ የሽብር ወንጀል ለመፈጸም አባል በመሆን ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል የተባሉ 17 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ማክሰኞ ሐምሌ 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በተጠርጣሪዎቹ ላይ ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው፣ አዲስ የተቋቋመው የኦሮሞ አንድነት ግንባር ድርጅት በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ዓላማና ተልዕኮ ለማጠናከር መሆኑን ገልጿል፡፡
ተከሳሾቹ ከአዲስ አበባ፣ ከኦሮሚያ፣ ከድሬዳዋ፣ ከምሥራቅና ምዕራብ ሐረርጌ በመውጣጣት ከአዲስ አበባና ከኦሮሚያ የተቀናጀ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ተነስቶ የነበረውን አመፅ እንዲቀጣጠል፣ በተለይ በምሥራቅ ሐረርጌ በጋራ ሙለታና በበዳኖ ቡድን እያደራጁ በመላክ የመንግሥትን ታጣቂዎች ትጥቅ እንዲያስፈቱና በየትምህርት ቤቱ የተሰቀለውን የኢፌዴሪ ሰንደቅ ዓላማ በማውረድ፣ የኦነግን ባንዲራ እንዲውለበለብ ያስተባብሩ እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
ተከሳሾቹ የኦነግን የፖለቲካ ፕሮግራምና ዓላማ ሳይቀይሩና ባንዲራውም ከኮከቡ በስተቀር አንድ ሆኖ፣ የኦሮሞ አንድነት ግንባር በሚል ስያሜ እስከ መጨረሻው የኢትዮጵያን መንግሥት በትጥቅ ትግል ታግለው ለመጣል፣ መቀመጫውን እንግሊዝ አገር ካደረገው የኦነግ ከፍተኛ አመራር ጋር መስማማታቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ይገልጻል፡፡
የኦነግ ከፍተኛ አመራር መሆኑ የተገለጸው አብደላ መሐመድ መኖሪያው አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ መሆኑ በክስ ከተገለጸው አንደኛ ተከሳሽ አሚን ዩዬ ሙሐመድ (ነገዎ ቢሎ) ጋር በስልክ ተነጋግረው በተስማሙት መሠረት፣ 1,100 የአሜሪካን ዶላር ልኮለት ለሽብር ተግባር ማስፈጸሚያና አባላትን ለመመልመል መስማማታቸውንና ተግባራዊ ማድረጋቸውንም ክሱ ያብራራል፡፡
የኦነግ አመራሮች የኦሮሞ አንድነት ግንባርን በአዲስ መልክ ማደራጀት በዋናነት የፈለጉት፣ በጫካና በከተማ ሽብር በመፍጠር ኅብረተሰቡ የኢትዮጵያ መንግሥትን ጠልቶ ከሥልጣኑ እንዲወገድ ለማድረግ መሆኑንም ክሱ ይጠቁማል፡፡
ኦሮሚያን ከፌዴሬሽኑ የመገንጠል ዓላማ የነበረውን የኦነግን ተልዕኮ ለማስፈጸም በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ በማሳደርና ኅብረተሰቡን በማስፈራራት፣ የአገሪቱን መሠረታዊ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማኅበራዊ ተቋማትን ለማናጋትና ለማፈራረስ የኦሮሞ አንድነት ግንባር ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ ሲንቀሳቀስ እንደነበርም በክሱ ተገልጿል፡፡ ተከሳሾቹ በአሜሪካ፣ በእንግሊዝ፣ በሳዑዲ ዓረቢያና በሌሎችም አገሮች ከሚገኙ የኦነግ አመራሮች ተልዕኮ በመቀበል፣ በኤርትራና በሶማሊያ ወታደራዊ ሥልጠና በመውሰድ ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ፣ ሐረርና ሌሎች አካባቢዎች በመሄድ በህቡዕ ተደራጅቶ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሰው የኦሮሞ አንድነት ግንባር ውስጥ አባል መሆናቸውንም ክሱ ያስረዳል፡፡
ሁሉም ተከሳሾች የኦነግን ዓላማና ተግባር በተጠናከረ ሁኔታ ለማስቀጠል የኦሮሞ አንድነት ግንባር በሚል ስያሜ በተቋቋመው የሽብር ቡድን ውስጥ አባል በመሆን በአዲስ አበባ የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም. በዲአፍሪክ ሆቴል የሽብር ቡድኑ በጠራው ስብሰባ ላይ መሳተፋቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ በስብሰባውም ላይ እንደተስማሙት በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው አመፅ እንዲቀጥል በየአካባቢያቸው የማስተባበር ሥራ እንዲሠሩ ሎጂስቲክስ፣ ስንቅና የጦር መሣሪያ እንደተዘጋጀ ሁሉም ወደ ጫካ በመግባት መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመለወጥ መታገል እንዳለባቸው መስማማታቸውን ክሱ ያብራራል፡፡ የተከሳሾቹን የቅድመ ክስ መቃወሚያ ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለሐምሌ 27 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

እኛ ያልተሳተፍንበት እኛ ያላቁላላነው ድግስ ሁሉ የጸረ ትግሬ ደናቁርት ነው።(ሕወሓቶች) By ምንሊክ ሳልሳዊ


እኛ ያልተሳተፍንበት እኛ ያላቁላላነው ድግስ ሁሉ የጸረ ትግሬ ደናቁርት ነው።(ሕወሓቶች)
ምንሊክ ሳልሳዊ ሁሉንም ነገር እነሱ ካልተጠሩ ወደ ጥላቻ ይመነዝሩታል .የሕወሓት ኣባላት እና ደጋፊዎቻቸው ስለ ሕዝብ ኣንድነት ስለሕዝብ ነጻነት እና ስለ ሕዝብ ፍቅር ሲሰበክ ያማቸዋል፤ ይብልጡኑ ደግሞ የፈጠራ ታሪካቸውና የጎሳ ፖለቲካቸውን የሚያደፈርስ ሕዝብን የሚያነቃ ሰው ከመጣ ኣለቀለት ይወርዱበታል፥ የሕዝቦች ኣንድነትና ፍቅር ለወያኔ ስልጣን አደጋ ነው። ስለ ኣንድነት ስለ ፍቅር ስለ ነጻነት ስለ ጋራ እድገት ከዘመርክ አንተ የቀድሞ ስርዓቶች ናፋቂና አሽባሪ ጸረ ሕዝብ ነህ በሕወሓቶችና ደጋፊዎቻቸው መንደር፡ማንኛውንም ነገር እነሱ ካልተሳተፉበት መላው ኢትዮጵያ ቢያጨበጭብ መላው ሕዝብ ሆ ቢል ወደ ዘረኝነት ኣጠጋግተው ያጦዙታል።እነሱ ካልተጠሩ ወደ ጥላቻ ይመነዝሩታል
ከምርጫ ዘጠና ሰባት በኋላ እማ ብሶባቸው ስለ ሕዝብ በደል የጮኸ ሁሉ ጸረ ትግሬ እና ኣሸባሪ ይባላል።ይህን የሚሉት ሕወሓቶች ብቻ እንዳይመስሉህ ሕወሓትን እንቃወማለን የሚሉ የስርዓቱ እድም ማስረዘሚያዎችም ጭምር ናቸው ።ኣንዳንደ የትግራይ ተወላጆችም ዝም ኣላሉም ይህ የሕወሓትና የተጠቃሚዎቹ የዘረኝነት መርዝ ለሃገር በተለይ ለትግራይ ኣደጋ እንደሆነ እየተናገሩ ነው።
በማናቸውም ጉዳዮች ላይ የትግራይ ተወላጆችን ኣሊያም የትግራይ ስም ብሎም የሕወሓት ስም ካልተነሳና የኣገዛዙ ታምቡር ካልጮኸ በጉዳዮች ዙሪያ ስድቡ ዘለፋው የዘረኝነት መርዙ ወዘተ ጋጋታው ከሕወሓት መንደር ለጉድ ነው፥ፕ\ር ፍቅሬ ቶሎሳ ኣማራና ኦሮሞ ከኣንድ ምንጭ ተቀዱ ስላለ ተብሎ የዘረኝነት ከበሮ እየተደለቀ ያለው በሕወሓት ኣባላት ደጋፊዎች እና በጽንፈኛ ኦሮሞዎች መሆኑ ምን ያህል ሕወሓቶችና ፍጥረቶቻቸው በበታችነትና በድንጋጤ እየደነበሩ እንደሚኖሩ ያሳያል።ልብ ያለው ልብ ብሎ ከታዘበ እውነታውን ሳይረፍድ ሊያውቅ ግድ ይላል፤ሕዝቦች በጋራ እንዳይነሩ እርስ በርሳቸው እየተባሉ እንዲያልቁ የተረፉት ደግሞ በሕወሓት ጉያ እንዲወሸቁ ሕወሓት እየሰራ ያለው የክፋት ድርጊት ጦሱ ነገ ከባድ መሆኑ ሊያውቀው ይገባል፤ምልክቶችም እየታዩ ነው። ይህንን መጥፎ የጎሳ ፖለቲካ ኣካል የሆነውን የሕወሓት የዘረኝነት ኣባዜ ተረባርበት በማለዳው ልንቀጨው ይገባል። #

የረኀብ አድማ ከመቱ 9ኛ ቀናቸውን ያስቆጠሩት 9 የፖለቲካ እስረኞች ራሳቸውን ስተው በግሉኮስ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ።


የረኀብ አድማ ከመቱ 9ኛ ቀናቸውን ያስቆጠሩት 9 የፖለቲካ እስረኞች ራሳቸውን ስተው በግሉኮስ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው  ገለጹ።
ከኃምሌ 13 ጀምሮ ከቤተሰቦቻቸው የሚሄድላቸውን ምግብ ያልተቀበሉ ሲሆን፣ በትላንትናው ዕለት እና ከትላንት በስቲያ ሰውነታችው ደክሞ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ እንዳሉ ለመረዳት ተችሏል።
1.በቀለ ገርባ 2.ብርሀኑ ተክለያሬድ 3.ዮናታን ተስፋዬ 4.ደጀኔ ጣፋ 5.ፍቅረማርያም አስማማው 6.ማስረሻ ሰጠኝ 7.ጉርሜሳ አያኖ 8.አዲሱ ቡላላ 9.አበበ ኡርጌሳ
ከላይ የተዘረዘሩት የፖለቲካ እስረኞች 5 ነጥብ ያለው መግለጫ አውጥተው የምግብ ማቆም አድማ መጀመራቸው ይታወሳል።
1. በሽብርተኛነት ተከሰው በእስር ቤት ያሉ እስረኞች ላይ የሚፈጸመው አሰቃቂ ምርመራ እንዲቆም
2.ፍርድ ቤቶች ነጻ ካለመሆናቸው የተነሳ ፍርድ ያጓትታሉ፣ በክልል መታየት የሚገባቸውን ጉዳዮች ያለሕግ በመንጠቅ ወደፌደራል ፍርድቤቶች መውሰድ ፌዴሬሽኑን የማፍረስ ተግባር ስለሆነ በአስቸኳይ እንዲቆም።
3.በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ ለእስር ተዳርገው የሚገኙ ዜዜጎች ላይ የሚፈጸመው ግፍ እና አድልዎ ይቁም
4.በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች ተሰማርቶ እየገደለ ሰቆቃ እየፈጸመ የሚገኘው የፌደራል ሠራዊት እንዲወጣ እና በዜጎች ላይ የሚፈጸመ አፈና፣ እስራት፣ ግድያ እንዲቆም
5. ሕገወጥ በሚል ሰበብ በዚህ ክረምት የዜጎችን ቤት የማፍረስ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም
ይህን እየጠየቅን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የሚገኝ ሕዝባችን ስለሰብአዊ መብት መከበር እና ስለፍትሕ ከጎናችን እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን::
 ኢሳት
Nafkot Eskinder's photo.