Friday, March 31, 2017

ብሄራዊ ቁጭትን እንደ ህዝባዊ ድጋፍ የሚቆጥረው የህወሓት ቡድን በአባይ ግድብ @እንቅዩጳዝዩን 444

   


ብሄራዊ ቁጭትን እንደ ህዝባዊ ድጋፍ የሚቆጥረው የህወሓት ቡድን በአባይ ግድብ
@እንቅዩጳዝዩን 444
ይጠናቀቅበታል ከተባለበት 5 ዓመት አንድ አመት ጨምሮ ገና ከግማሽ በታች ያልተሰራው የአባይ ግድብ ለሆድ አደር ቱባ ባለስልጣናት ና መጠርቂያ የሌለው የአርቲስት ተብየከመንግስት ካድሬወች ከርስ ከፍ ከማድረግ ውጭ ከፍ ብሏል ሲሉት ግድቡ እራሱን ዝቅ እያደረገ እያየን ነው። በተለያየ መንገድ ሰራተኛው እስከ ተማሪው ፣ከነጋዴው እስከ ገበሬው ድረስ አዋጣ እየተባለ እየተገደደ ከደሞዙ በሚቆረጥበት ሁኔታ ተሰብስቧል የሚሉት ቢሊየን ብሮች በትክክለኛው ቦታ ሲወሉ አይስተዋሉም። ብሄራዊ ቁጭት ያንገበገበው የኢትዩጲያ ህዝብ ያዋጣው ገንዘብ የታል መለቱ አይቀርም። አፋን አውጥቶ እንዳይናገር የአምባገነኑ ወያኔ የበቀል በትር አፋን ብትለጉመውም ቅሉ በተለያየ ቦታና ጊዜ ቢያንስ ለራሱ አንድ ጥያቄን መጠየቁን አላቆመም።”ይጨረሳል የተባለው 5 ዓመት አለፈው ፤በየጊዜው በሰበብ አስባቡ የሚመነተፈው ብር የት ገባ ? ” እያለ ከቻለ ለጓደኛው ካልቻለ ለራሱ ሹክ ይለዋል። ይሄ ጉዳይ የራሱ የህወሓት ቡድን ሹመምንት ጥያቄ መሆኑ አልቀረም ፥የተበላ ነገር ይረሳልና። ይህችን ጥያቄ ለመጠየቅ የምትከፈትን አንደበት ለመዝጋት ያሰበ ይመስላል ከሰሞኑ የግድቡ አጠቃላይ ሃይል የማመንጨት አቅም ለ6 ዓመታት አካባቢ 6ሺ ኪሎ ዋት የነበረውን 450 ኪ.ዋት ጨምረው ሃይል የማመንጨት አቅሙ አድጓል 6450 ኪ.ዋት አድርገነዋል እያሉ ያሉት ።በተጨመረችው የቁጥር ጨዋታ ለመገንባት ደግሞ ያው ጊዜና ተጨማሪ የገንዘብ መጠን ያስፈልጋል በማለት ጨዋታውን የስልጣን ወንበር ጊዜ መግዣ ያደረጉት። መቼ ይሄ ብቻ?ህወሓት ብሄራዊ ህዝባዊ ና ሀገራዊ ቁጭትን ለህዝባዊ ድጋፍ ለመጠቀም ሌላም ነገር ይዞ መጥቷል።
ከሰሞኑ ወደ ግድቡ አካባቢ የሚሰማ አዲስ ፊልም እየተሰራ ይገኛል።ለጉልበት ስራ ወደ በረሃ የሚወርዱ ወገኖች በተዋናይነት ተመልምለዋል። የወረዳና የመንደር ተጠሪ ካድሬወች ለማስመሰያ ድግሱ ተፍ ተፍ እያሉ ነው ። ነገሩ እንዲህ ነው። የነፃነት ሃይሎችን ከህዝብ ለማራቅ ና የጥፋት ሃይል አድርጎ በህዝብ ላይ ለመሳል የሚደረግ ሙከራ ነው ። በጉልበት ስራ ላይ በአካባቢው የሚገኙና በየማጎሪያ ቤቱ ታስረው ከሚገኙ ወገኖችን መሳሪያ ታጥቀው ከግድቡ ላይ ጥቃት ሊሰነዝሩ ሲሉ ያዝኲቸው ብሎ በሚቆጣጠሩት ሚዲያ ለማቅረብ ያሰበ ነው። ለዚህም ከENN ፣ከፋና ፣ከዋልታ የቴሌቪዥን ጣቢያወች የተመረጡ ልማታዊ ጋዜጠኞች ተገኝተወል። በተለይ ዋልታ ቲቪ የስርጭት ጂማሮ በመጋቢት 24 መክፈቻ አብይ ጉዳይ ይሆናል ተብሎ እንደታሰበ ታውቋል። ከግልገል በለስ እስር ቤት ተመርጠው የተወሰዱ እንዳሉም ለማረጋገጥ ተችሏል። ከወደ ጉባ አዲስ ህዝብን ማታለያ መንገድና ህዝባዊ ድጋፍ ማግኛ መንገድ ይዞ ለመታየት የሚፍጨረጨረው የህወሓት ቡድን በነፃነት ሃይሎች በደፈጣ ውጊያና በእቅድ ዘመቻ አይቀጡ ቅጣት እየቀመሰ ይገኛል። በአካባቢው የሚገኙ የነፃነት ሃይሎች ግን “አባይን ግድብ የሚነካው እርሱ ጠላታችን ነው” ይላሉ። ጨምረውም የወያኔ አምባገነን ቡድን ህዝባዊ ድጋፍ ለማግኘት የህዝቡን ብሄራዊ ቁጭት እየተጠቀመ በራሱ ሰወች በግድቡ ላይ ጥቃት ከፍቶ በነፃነት ሃይሎች እንደሚያሳብብ ከቀደመ ልምዱ እንረዳለን።ይሄን ማድረጉም አይቀርም ። በዚህም ነፃነት እንደውሃ የጠማው ህዝብ በንቃት እንዲከታተለው በአፅኖት ያሳስባሉ።



No comments:

Post a Comment