Wednesday, March 15, 2017

ሰበር ዜና …ለሥልጠና ወደ አድዋ የተወሰዱ የወልቃይት ዐማሮች በድብደባ ጉዳት ደረሰባቸው፤ – ሙሉቀን ተስፋው



የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን የጨረሱ የወልቃይት ወጣቶችን አሰልጥኜ ሥራ አስይዛችኋለሁ በማለት ነበር ሕወሓት ወደ አድዋ የወሰዳቸው፡፡ ከወልቃይትና ጠገዴ አካባቢዎች ተመልምለው የተወሰዱ ወጣቶች አድዋ ሲደርሱ ግን የጠበቁትን ሥልጠና አላገኙም፡፡
አብረዋቸው በሚማሩ የትግራይ ተማሪዎችና አስተማሪዎች ‹‹ስለምን ዐማራ ነን አላችሁ፤ ትግሬ የተጠላው በእናንተ ምክንያት ነው!›› የሚል ወከባና ጥያቄ ይደርስባቸዋል፡፡ ከዚያ ወጣቶቹ ‹‹ታዲያ ምን ልንል ነው፤ እኛ እኮ ዐማራ ነን›› የሚል የማያወላዳ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡
ትናንት መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሥልጠና የሔዱት ሁሉም ወጣቶች ያለምንም ረዳት በሰው አገር የተደበደቡ ሲሆን ሐጂ የተባለ ወጣት ከፍተኛ የአከርካሪ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል፡፡ በድብደባው ጉዳት የደረሰባቸው ዐማሮች እስካሁን ምንም ዓይነት ሕክምና ካለማግኘታቸውም በተጨማሪ ወደ ወልቃይት እንዳይመለሱ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ወልቃይት ከተመለሱ ለበለጠ አደጋ እንደሚጋለጡና እንደሚታሰሩም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment