
አብረዋቸው በሚማሩ የትግራይ ተማሪዎችና አስተማሪዎች ‹‹ስለምን ዐማራ ነን አላችሁ፤ ትግሬ የተጠላው በእናንተ ምክንያት ነው!›› የሚል ወከባና ጥያቄ ይደርስባቸዋል፡፡ ከዚያ ወጣቶቹ ‹‹ታዲያ ምን ልንል ነው፤ እኛ እኮ ዐማራ ነን›› የሚል የማያወላዳ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡
ትናንት መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሥልጠና የሔዱት ሁሉም ወጣቶች ያለምንም ረዳት በሰው አገር የተደበደቡ ሲሆን ሐጂ የተባለ ወጣት ከፍተኛ የአከርካሪ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል፡፡ በድብደባው ጉዳት የደረሰባቸው ዐማሮች እስካሁን ምንም ዓይነት ሕክምና ካለማግኘታቸውም በተጨማሪ ወደ ወልቃይት እንዳይመለሱ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ወልቃይት ከተመለሱ ለበለጠ አደጋ እንደሚጋለጡና እንደሚታሰሩም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
No comments:
Post a Comment