Tuesday, March 14, 2017

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ግለሰቦችን በቂም በቀል ለማጥቂያነትና አስፈጻሚዎች የአዋጁን መንፈስ ባለመረዳት ጉቦ ለመብያነት ጭምር እንዳዋሉት ተገለጠ።

   


አናንያ ሶሪ
“ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን ለመናድ ኦነግና ግንቦት ሰባት ከሚባሉት ድርጅቶች ግንኙነት ፈጥራችሁ ተንቀሳቅሳችኃል የሚል ነው። የአስቸኳይ ጊዜ
አዋጁ መርማሪ ቦርድ የሚባል ኮሚቴ ጎብኝቶን ነበር በአንድ ወቅት። የነበሩትን ችግሮች፤ አዋጁ ግለሰቦችን በቂም በቀል ለማጥቂያነትና አስፈጻሚዎች የአዋጁን መንፈስ ባለመረዳት ጉቦ ለመብያነት ጭምር እንዳዋሉት፤ በተለያዩ አስቂኝ ምክኒያቶች ሳይቀር የገቡ መኖራቸውን ገለጥናላቸው።” አናንያ ሶሪ።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ ለወራት እስር ላይ የቆየው ጋዜጠኛና የኢንተርኔት አምደኛ አናንያ ሶሪ  ተለቀቀ።በተመሳሳይ አብረውት የታሰሩት ጋዜጠኛና የኢንተርኔት አምደኛ ኤልያስ ገብሩና የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ አባል ዳንኤል ሽብሩ እስካሁን ያለመለቀቃቸው ታውቋል።

No comments:

Post a Comment