Monday, March 20, 2017

በወያኔ እስር ቤት የሚገኙት የፖለቲካ እስረኞቹ አቶ በቀለ ገርባ አቶ ደጀኔ ጣፋ የረሃብ አድማ ጀመሩ።



በወያኔ እስር ቤት የሚገኙት የፖለቲካ እስረኞቹ አቶ በቀለ ገርባ አቶ ደጀኔ ጣፋ የረሃብ አድማ ጀመሩ።
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና የፓርቲው ፀሐፊ አቶ ደጀኔ ጣፋ ቤተሰቦች እስረኛ ቤተሰቦቻቸው በማርሚያ ቤቱ ውስጥ ለእስረኛ የሚሰጥ መብት ለእነሱ ስለተነፈጋቸው ማረሚያ ቤቱ መብታቸውን እሲያከብርና ውሳኔ እስኪሰጣቸው ምግብ እንደማይቀበሉ እንደነገሯቸው ተናገሩ።
በቀለ ገርባበቂልንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የእስረኛ ቤተሰቦች ታሳሪ ቤተሰቦቻቸውን አግኝተው ምግብ ማቀበል እንዳልቻሉና ሲያገኟቸውም ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ከፍተኛ ችግር ስላለባቸው ችግራቸው እስኪፈታ ምግብ እንደማይቀበሏቸው እንደነገሯቸው ለአሜሪካ ድምጽ ገለጹ።የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ ልጅ ወ/ት ቦንቱ በቀለና የፓርቲው ዋና ፀሐፊ አቶ ደጀኔ ጣፋ ባለቤት ወ/ሮ አሰለፈች ሙላት ዛሬ ወስደውት የነበረውን ስንቅ ይዘውት ወደቤት እንደተመለሱ ሲናገሩ የሕግ ጠበቃቸው ደግሞ ደንበኞቻቸውን ማግኘት እንዳልቻሉ ተናግረዋል። VOA

No comments:

Post a Comment