Friday, March 31, 2017

ሙርሌዎች ዛሬም የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው በመግባት ሦስት ህጻናትን ይዘው ሄዱ



(ዘ-ሐበሻ) የሙርሌ ጎሳ አባላት ዛሬም የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው ጋምቤላ በመግባት ጥቃት ፈጽመው በዚያውም ሦስት ህጻናትን ይዘው መሰወራቸው ተሰማ::
የዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች ከስፍራው ባደረሱን መረጃ መሰረት ፒንዩዶ በተሰኘው የስደተኛ መጠለያ በመሄድ ነው እነዚሁ ሙርሌዎች ህጻናቱን ይዘው የሄዱት::
ከአስራምስት ቀን በፊት የደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል ባደረሱት ጥቃት 18 ሰዎች መግደላቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም:: እንዲሁም 22 ህጻናትን አፍነው መውሰዳቸው አይዘነጋም::
ከደቡብ ሱዳን ተነስተው የሚመጡት እነዚሁ የሙርሌ ታጣቂዎች በተመሳሳይ ባለፈው ፌብሩዋሪመጨረሻ ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽመው 13 መግደላቸውን 20 ህጻናትን አፍነው መውሰዳቸውንም ይታወሳል::
መንግስት የለም ወይ?


 0  60  60

No comments:

Post a Comment