Thursday, March 30, 2017

ዜና ወልቃይት ….በወልቃይት የታሰሩ ወጣቶች ካልተፉ በአዲረመጥ ሌላ ተጋድሎ ሊጀመር ይችላል፤ – ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋው



ሳተናው
By ሳተናውMarch 30, 2017 06:46 

ከአንድ ወር በፊት የአዲረመጥ ልጆች ለኳስ ጨዋታ ወደ ማይጋባ ሒደው ነበር፤ ሆኖም ሰፋሪዎች በትግራይ ፖሊሶች ታግዘው የአዲረመጥ ልጆችን ይደበድባሉ፡፡ ዛሬ ደግሞ ባለፈው የወልቃይት ልጆችን ሲያሰቃዩ የነበሩ ሰፋሪዎች ለስብሰባ ወደ አዲረመጥ መጡ፡፡
ለስብሰባ የመጡት ሰፋሪዎች ‹‹ዐማሮች ሊደበደቡን ነው›› የሚል ክስ በማሰማታቸው በሦስት መኪና የትግራይ ታጣቂዎች ወደ ወልቃይት ጉዞ ጀምረዋል፡፡ ከዚህም በላይ በማይጋባ ከተደበደቡት ልጆች መካከል የተወሰኑትን ወጣቶች የታሰሩ ሲሆን ከታሰሩት ልጆች መካከል ፎቷቸው ከዚህ ሥር የተቀመጠው ሰሎሞን አታላይና አበራ አለነ ይገኙበታል፡፡ የታሰሩ ልጆች ካልተፈቱ ነገሮች ሊቀየሩ ይችላሉ ተብሏል፡፡ በአዲረመጥ ሌላ ሕዝባዊ ተጋድሎ ሊቀጣጠል ይችላል፡፡

No comments:

Post a Comment