Tuesday, March 14, 2017

ሰበር ዜና….በሰሜን ጎንደር የወያኔ ጦር ሽንፈት ገጠመው፤ 13 ወታደሮች ተገድለዋል – ሙሉቀን ተስፋው



የጀግናው አርበኛ ጎቤ ጦር በሰሜን ጎንደር ዞን ዛሬ መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም. ረፋድ 3.30 ተኩል ጀምሮ ከወያኔ ትግሬ መከላከያ ጋር ባደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ ድል ቀንቶታል፡፡ እስከ እኩለ ቀን ድረስ በቆየው ጠንካራ ውጊያ የጀግናው አርበኛ ጎቤ ጦር 13 የወያኔ መከላከያ ሠራዊት አባላትን የገደለ ሲሆን አንድ የወያኔን ጦር ደግሞ አቁስሎ ማርኳል፡፡
በአርበኛ ጎቤ እግር ተተክቶ ጦሩን ሲመራ የነበረው አርበኛ ሻንቆ ‹‹የመሪያችን ሞት በሚገባ ተበቅለናል፤ ተጋድሎአችን እስከ ያለምንም ጥርጥር ያሸንፋል›› ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ የዐማራው ጦር የተማረከውን ወታደር ጨምሮ የ14 ወታደሮችን ሙሉ ትጥቅ የማረከ ሲሆን ከባለፈው ወር ወዲህ የተገኘ ታላቅ ወታደራዊ ድል እንደሆነ ተገልጧል፡፡
የዐማራ አርበኞችን ለማጥቃት የመጣው ጦር መሣሪያውን በዱር እየጣለ ወደ አቅራቢያ ከተማ የሸሸ ሲሆን የአካባቢው ገበሬዎች በዱር የወዳደቀ ብዙ መሣሪያ እየያዙ እንደሄዱም ለማወቅ ተችሏል፡፡
(ማሳሰቢያ፤ በአርበኞቹ ጥያቄ መሠረት ጦርነቱ የተካሔደበትን ቦታ ከመግለጽ ተቆጥበናል)
የዐማራ ተጋድሎ ያሸንፋል//

No comments:

Post a Comment