
የአገልግሎት ጊዜያቸው ገና በመሆኑ ምክንያት መልቀቅ የማይችሉት አብራሪዎች ሥራቸውን ጥለው እየጠፉ እንደሆነ የሚናገሩት የመረጃ ምንጮች ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ብቻ አራት የዐማራና ሰባት የኦሮሞ ተወላጅ አብራሪዎች ሲጠፉ ተይዘው ታስረዋል ተብሏል፡፡ ከታሰሩት አብራሪዎች መካከል አንድ የዐማራ ተወላጅ አብራሪ የደረሰበት እንደማይታወቅና ከጎንደር የሔዱ ቤተሰቦቹ በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ሊያገኙት እንዳልቻሉ ነው የተነገረው፡፡
ሌላው ለውጥረቱ መንስኤ ነው የተባለው በከፍተኛ ጀነራሎቹና በታችኛው እርከን ላይ ባሉት መካከል ልዩነት መፈጠሩ ነው ያሉት ምንጮች ወታደራዊ እዝና ተዋረድ መተግበር ካቆመ እንደሰነባበተ ገልጸዋል፡፡ ለአየር ኃይል አባላት በየትውልድ ቦታቸው የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ ተፈቅዶላቸው የነበረውን አፈጻጸም ላይ ችግር መኖርም ሌላው የውጥረቱ መንስኤ ነው ብለዋል፡፡ የአየር ኃይል እማኞች እንደሚሉት በአየር ኃይል ግቢ ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት ከመቼውም ጊዜ የተለየ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
No comments:
Post a Comment