Friday, March 31, 2017

የዳግማዊ አጤ ምኒልክን ጀግነት መዳፈር ማለት የመላው አፍሪካ፣ የመላው የጥቁር ሕዝብን ክብር እና ነጻነት መዳፈር ነው

     



 0  15  15
ከኢትዮጵያወርቅ (የሐረርወርቅ) ጋሻው
የጋርቤን፣ የሃሪየት ተብማንን፣ የማርቲን ሉተር ኪንግን፣ የማልከም ኤክሳን፣ የፍረድሪክ ዳግላስን፣ የማንዴላን፣ የኳሜ ኒኩርሟን፣ በአጤ ምኒልክ የጀግንነት ደም የተወጉትን የነፃነት መሪዎች እና ለአንድነት የታገሉትን እና  እየታገልን ያለንውን መዳፈር ነው።
ቁጥር አንድ
ማርች 29፤ 2017
አዩ እርሶ ሳያውቁት ከዚህ በታች ያለው ስዕል ሰለባ ነዎት።


ከዚህ ቀጥሎ ያለው ደግሞ በሚገባ እንደተቀመጠው ነጮች አደዋ ላይ ከተሸነፉ በኋላ የበርሊኑ ኮንፍራንስ በ1884 የታለመው አፍሪካን ለመቀራመት እንደተፈለገው በተግባር ባለመዋሉ አሜሪካንም ተባብራበት የነበረው እንዳሰቡት ሳይሆን ቀርቶ በጦርነት መሪነት እና ሕዝብን አስተባብሮ ባጭር ጊዜ ጦርነትን በቁጥጥራቸው ስር በማድረግ የታወቁት ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ጣሊያንን ስላንበረከኩት ማለትም ባጋጣሚ የተገኘ ድል ሳይሆን በልምድ እና በቆራጥነት በመሆኑ ለሌላው ጥቁር በአለም ውስጥ በተለይም በባርነት ይኖር የነበረውን ሁሉ ብድግ በማድረጉ ከአፍሪካ፣ አሜሪካን፣ ከሃይቲ፣ ካሪቢያን እስከ አሜሪካ አውሮፓውያን አንድ ድምጽ የሌለው መሳርያ ነደፉ። ከዚህም ድምጽ ከሌለው መሳርያ ዋናው ጥቁሩን (አፍሪካውያንን) ለይቶ አንገት ለማስደፋት በባርነትም የተያዘውን ባጠቃልይ አፍሪካዊ ነግሮ በነሱ አነጋገር አላሸነፈንም ሚኒልክ ጥቁር አይደልም በሚል የፈረንጅ ስእል እየሳሉ ጭምር የአፍሪካዊ (የጥቁር) አንጎል ከጦጣ የማይበልጥ ነው ሳይንስ አረጋግጥዋል በሚል በትምህርት ደረጃ የሳይንስ አንዱ መእራፍ በማድረግ ነድፈው ወድያው ከአደዋ ጦርንት ድል ማግስት ጥቁርን ሕዝብ ሳይኮሎጂካልይ ድምጽ በሌለው መሳርያ እያነበበ እና እያየ እራሱን እንደ ጦጣ አንጎል ባለቤት እንዲያይ ዘመቻ አድርገው ኖረዋል። በዚህ ድምጽ በሌለው የሳይኮሎጂ መሳርያ አይምሮው ከጦጣ የተሻለ አንጎል የለህም በተባለው እንደ እርሶ የተመረዘው በተግባር ሲተሮገም በሂደት ከታየው ማንም ሳይመራው እራሱን በእራሱ ዝቅ በማድረግ የተነገረውን ይዞ የራሱ ወገኖች በጦርነት ቦታ ተገኝተው የመዘገቡትን አላምንም ጣሊያን የነገረኝን ብቻ ነው በሚል ያውም ፋሽስት ጣሊያን እርሶ እንደተናገሩት በኤስቢኤስ ያልጻፈውን ሃቁን ገለባብጠው በማቅረብ ጭምር ማለት ነው።
“When you control a man’s thinking you do not have to worry about his actions. You do not have to tell him not to stand here or go yonder. He will find his ‘proper place’ and will stay in it. You do not need to send him to the back door. He will go without being told. In fact, if there is no back door, he will cut one for his special benefit. His education makes it necessary.” Carter Godwin Woodson.
እያደረገ ታሪኩን ሲያንቋሽሽ እና ለወጣቱም ትውልድ የፈረንጅ የበላይነት እንዲቀበል ለማድርግ ሃሰት ያስተምራል ማልት ነው።
“When you control a man’s thinking you do not have to worry about his actions. You do not have to tell him not to stand here or go yonder. He will find his ‘proper place’ and will stay in it. You do not need to send him to the back door. He will go without being told. In fact, if there is no back door, he will cut one for his special benefit. His education makes it necessary.” Carter Godwin Woodson.

Professor Tekeste Negash,
History is a weapon man think about it. Stop thinking in a white man’s mind, but yours.
I suggest you to go outside the White man’s book and educate yourself with Dr. Woodson advise bay reading “The Mis-Education of the Negro” by Carter Godwin Woodson And “What They Never Told You in History Class, Vol.1: Indus Khamit-Kush .

በቁጥር ሁለት እንገናኛለን እንደገና።
ይሄ ግልባጭ ለሚደርሰው ለኢትዮጵያ ሕዝብ እነሆ።
ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ከCarter Godwin Woodson ጋር የሚቀመጥ ነው።
ታሪክ ያውም በነቃ ዘመን በአንድ መስመር የሚሄድ ሳይሆን በብዙ አቅጣጫ ያለውን ሃቅ ማንበብ እና መርምሮ አጥንቶ ማወቅን ይጠይቃል። ነጮች ያስተማሩን በእየዩንቨስቲው የኖረ ሃሰት ታሪክ ነው። እነሱን የከፍ የሚያደርግ ሚመለከት ብቻ እንጂ የእኛን ታሪክ አይደለም ያቀረቡልን በእርግጥ ባሪያናችሁ እያሉ አስተምረዋል። በአሜሪካን የአለም ወይም ወርልድ ሂስትርይ ፕሮግራምን ስንመለከት 80 % ውሸት ነው። በሚቀጥለው ከእነመረጃው ምን ማለት እንደፈለኩኝ በራሴ የደረሰብኝን : ውሸት አልቀበልም በማ ክፍል ውስጥ አቀርባለሁ።
ባሪያን ነፃ ለማውጣት የሚደረገው ትግል ቀላል ነው። ከባዱ ባርያውን ባርያ መሆኑን ማሳመኑ ነው።
ከየሐረርወርቅ ጋሻው።

ከዚህ በታች ባለፈው የጻፍኩልዎ ሲሆን የፊደል ስህተቶች ስላገኘሁበት አርሜው እንደገና ከዚህ በታች አስቀምጬዋለሁ።
(http://ethiopatriots.com/pdf/Yedres-Le-Pro-Tekesete-20170320.pdf)
ይድረስ ለፕሮፈሰር ተከስተ ነጋሽ : የታሪክ አላዋቂነትዎን ያርሙት።
ከዳላስ ቴክሳስ።
ባለፈው በኤስቢኤስ በአውስትራልያው የአማርኛ የሬድዮ ስርጭት ላይ ፡ በእርሶ እና የኢትዮጵያን ታሪክ አዋቂ ይሁኑ አይሁኑ ሳይገልጹ እርሶ እና ባለቤትዎ ስማቸውን ጠቅሰው ያው ፎቶግራፋቸው እንደሚያሳየው የውጪ ሰው ናቸው ማለትም ነጭ ፡ ስለ ኢትዮጵያ ሴቶች ጻፍን ብለው ሲናገሩ ፡መጀመርያ ባለቤትዎን እንክዋን በሚገባ ቦታ አልሰጥዋቸውም መጽሃፉን አብረን ጻፍን ከማለት ሌላ ሴትን ማክበር ከቤት ይጀምራል። ዋናው መልክቴ ስለእርሶ ስለባለቤትዎ ሳይሆን ፡ መቼም ለሴቶች መብት ታጋይም በመሆኔ ጠቀስኳቸው እንጂ ጉዳዬ ጀግናዋ ንቁዋ እና ብቸኛዋን ንግስት እሌኒን ማለት ከአዳል እና ከአማራ የተወለዱትን አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት የተዛነፈ ያልተሟላ በደንብም የማያቁትን አስመልክቶ መሴ ማርሾን ዡል ከአጤ ላሊበላ ጀምሮ ስለ አጤ ዘረያቆብ፡ አጤ በእደ ማርያም ፡ አጤ እስክንድር ፡ አጤ አምደ ጽዮን ፡ አጤ ናኦድ ፡ አጤ አጤ ልብነ ድንግል ፡ አጤ ገላውዲዮስ ፡ አጤ ሚናንስ ፡ አጤ ሰርጸ ድንግል ፡አጤ ኢያሱ ቀዳማዊ ፡ ታሪክ ዜና እና መዋዕልን ያጠቃልላል። ከእነዚህ 16 መስሃፍት ውስጥ ስለ አጤ ዘረያቆብ ፡ አጤ በእደ ማርያም ፡ አጤ ናኦድ እና ልጃቸው አጤ ልብነድንገል መለስ ብለው ቢያነቡ ወይም ቢያጠኑ ትልቅ የታሪክ ችሎታዎን ያስተካክልሎዎታል ብዬ በሚገባ አምናለሁ። እንደሚታወቀው አንድ ሰው ስለ እራሱ ታሪክ ወይም ስለ አለም ታሪክ ለማወቅ የታሪክ ፒኤችዲ አያስፈልገውም። ያለውን የታሪክ መጸሃፍ ሁሉ ስራዬ ፡ ጉዳዬ ብሎ ማንበብ እና መመራመር እና ፈረንጅ የጻፈውን እራሱን ከፍ እያደረገ ፡ ጥቁርን ዝቅ እያደረገ አሜን ብሎ መቀበልም እንዳይሆን ፡ ጥናቃቄን የራስን ታሪክ በሚገባ አውቆ ቀድሞ በመጠንቀቅ ጭምር ማለት ነው።
ፕሮፌሰር ተከስተ እርሶ ስለ ንግስት እሌኒ የተናገሩት ፡ ይዘገንንናል የልጅን ሚስት ለአባት።
“ንግስት እሊኔ ከአዲያ እና ከንባታ ይወለዳሉ። የአጼ ዘርያቆብ ባለቤት ነበሩ የሚል ነው።
ከዚህ በታች ያለው በትክክሉ የንግስት እሌኒ ታሪክ ነው። ለዚህም ከላይ እንዳስቀመጥኩት የመሴ ፕርሾን ዡልን መጽሃፍ ያንብቡ። ከዚህ ውጪ በመሄድ ምንም አዲስ ታሪክ ሊፈጠር አይቻለም ሃቁ የኢትዮጵያን ታሪክ ምንያህል በሚገባ ያውቁታል ነው።
ፕሮፌሰር ተከስተ ፡
ንግስት እሌኔ አይደሉም ሐድያ እና ከምባታዋ ንግስት ጽዮን ሞገሳ ናቸው። ንግስት እሌኒ የአጼ ዘረያቆብ ባለቤት አይደሉም ታሪክ እንደሚያስራዳው በተለያየ መጸሃፍ ተጽፎ ይገኛል። ለርሶ የማዝልዎ የበድጋሚ የፐሴ ፕርሾ ዡልን መጽሃፍ ነው። የአጤ ዘረያቆብ ባለቤት ንግስት ጽዮን ሞገሳ ይባላሉ ብሄራቸውም ከንባታ እና ሕዲያ ነው።
ንግስት እሌኒ የአጤ በእደ ማርያም ባለቤት ናቸው። ማለት የአጤ ዘረያቆብ ልጅ ባለቤት።
ንግስት እሌኒ በእርግጥ ልጆች አልወለዱም ። ስላልወለዱ አጤ በእደ ማርያም ንግስት ሮማነ ወርቅንም አግብተው ወልደዋል ። ንግስት ሮማንወርቅ የአጤ እስክንድ በእደ ማርያም እናት መሆናቸው ነው።
በተጨማሪ ፓንክረስት ስለንግስት እሌኒ የጻፉትንም የቅርብ ጊዜን መጽሃፍ ያንቡ እና እራስዎን ያርሙ ።
በተረፈ ስለ አጤ ምኒልክ ትልቅ ውሸት ስላስቀመጡ ይሄም ከመጽሃፍዎ መታተም ጋር የተያያዘ አዲስ ዘመቻ ጣልያን ሊቀለብስ የማይችለውን ታሪክ መቀልበስ እራሱ ጽፎ ከተሰራጨው ጭምር በሚገባ በእየአሃጉር ተቀምጦ ስላለ በተለይ ፈረንሳይ ፡ እንግሊዝ ፡ ጀርመን ፡ ፓርቱጋል ፡ ስፔን ለኢትዮጵያ ብለው ሳይሆን ለራሳቸው ታሪክን በመበወዝ ስለማይቀበሉ የአጤ ምኒልክ የጥቁር ሕዝብ አኩሪ ታሪክ
ለዘለዓለም ይኖራል። የራስ መንገሻ ዮሐንሳን የሃይለስላሴ ጉግሳን ፡ የመለስ ዜናውን አሰቃቂ እፍረት ታሪክ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጬ ቡድንን አሳፋሪ እራስን የሸጡ የመጀመርያዎቹ ጥቁሮች ታሪክ ለመሸፈን ሲባል በአጤ ምኒልክ ላይ እየተደረገ ያለው ዘመቻ በሃሰት ኤርትራን አሳልፈው ሰጥተዋል በሚል ቦታ ስለሌለው እስከመጨረሻው ትምህርት የጎደለብዎትን እንዲያገኙ እናደርጋለን የኢትዮጵያ ልጆች ለከርስ መጸሃፍ ለማሳተሚያ የማንገዛ። ጣሊያን እራሱ የጻፈውን እና ያሳተመውን በጊዜው ማንበብ ይኖርቦዎታል አሁን በውዞ የሰጠዎትን ትተው ይሄውም በማስረጃ እነሆ እናም ከጣሊያኖች ጋር ይጠያየቁበት። ባለቤትዎ ነጭ ስለሆኑ አዩ ነጭ ያለዎትን ይዘው መላክ የጻፈው አድርገው የሚያዩ ከሆኑ ከነጮቹ ሳጥን ይውጡ እና የአለም ታሪክ ሜዳ ላይ ይቁሙ። በስሜት ፡ በጥላቻ ፡ በገንዘብ ማንኛንም ታሪክ የጥሩም ይሁን የመጥፎ ሆንዋል እና ተመዝግቦ የገኛል እና ማንም ሊሰርዘው አይችልም መክኒያቱም ቴክኒዎሎጂው የረቀቀ በመሆኑ።
እንደገባኝ በጣሊያን ስለሚያምኑ ያውም ትግሬዎችን ሊውጣቸው መንጋጋውስጥ አግብቶ ምኒልክ አንበሳው በፍጥነት በነቃው አይምሮአቸው ደርሰው ያስተፉትን ወገኖችዎን የረፈረፋቸውን አማራው እና ኦሮሞው ሰራዊት በብዛት ግንባሩን እየሰጠ ያዳናቸውን እየሰደቡ ጣሊያንን ያለው ነው ትክክል ሲሉ በስብሰባ ላይ ስለተሰሙ ይሄው ሃቁን ያግኙት ከዚህ ቀጥሎ ባለው መጽሃፍ እና ገጽ ።
“Memoire d’ Afrique Page 393” “Adua. E. Bellavia. P. 227”
“La Prima Guerra d’ Africa, R. Battagalia, PP, 793—800.”
“Douze ans en Abyssinia…PP.528-530; Adua. Belavitta P, 394”
“L’ Italia in Africa, Serie Storico, Vol I, Tome II, A Vitale ,PP. 122-123”
ከዚህ በላይ ለፕሮፌሰር ተከስተ የጻፍኩት ታሪካዊ ስህተታቸውን እንዲያርሙ
ስለ አጤ ምንይልክ በወያኔ እየተደረገ ያለውን የሃሰት ዘመቻ በሚገባ ስለደረስኩበት አጤ ምኒልክን እና ጀግንነታቸውን አስመልክቶ የጻፍኩት በኢትዮፓትሪኦትስ ድህረ ገጽ መውጣቱን ለማረጋገጥ ስገባ ስለ አደዋ ክብረበአል ለመሳተፍ የሄዱ እህት አጤ ምንይልክ ሲሰደቡ ሰምተው መምጣታቸውን የጻፉትን ስመለከት ምናይነት አጋጣሚ ነው ብዬ ባንድ ፊት ስገረም በሌላ በኩል የፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽም በኤስቢኤስ ሬድዮ ከጋዜጠኛ ካሳሁን ሰቦቃ ጋር ያደረጉት ቃለምልልስ ስለ ጻፉት መጸሃፍ በሚገባ የተቀነባበረ የእፍረት ታሪክ መደለዣ በማድረግ ስለ ሴቶች እያወሩ ነገር ግን ዋና አላማው አጤ ምንይልክን የመንገሻ ዮሐንስ የልዋጭ ልዋጭን አሳፋሪ ከጣልያን ጋር ያደረጉትን ውል መረብን መሸጥ ማደብዘዣ ዜሮ ዘዳጋር አንድ ሆኖ አገኘሁት። ባይሆን ኖሮ ዩኒፎርም ወይም አንድ የሆነ ምንም ያልተዛነፈ መልክት እንደ አንድ አክተር አጥንቶ እንደሚጫወተው ተከስተም በዚህ መልክ ስለ አጤ ምኒልክ ባልተናገሩ ነበር። ሰውዬ ባጭሩ ከጣሊያን ያገኙት ጉርሻ እንዳለ ግልጽ ነው ብሎም ከወያኔ። በመሆኑም ኤስቢኤስ ላይ የተናገሩትን በአደዋም በአል ስብሰባ ላይ የደገሙት የዘመቻው ዋና አፈ ቀላጤ ስለተደርጉ ብቻ ነው። ሃቁ በሙሉ ተከስተ የተነጋሩት አጤ ምኒክን አስመክቶ ውሸት ነው ። በበኩሌ ኢትዮጵያ ብዙ የታሪክ እናት ስለሆነች የአጤ ምኒይልክ ጀግንነት ሃቅ ባይሆን ኖሮ የታሪክም ድሆች ከሆኑ ብሄሮች ስላልተፈጠርኩኝ የታሪክ ባለቤቶች ከሁኑት ከኢትዮጵያ ብሄሮች እንጂ ያውም የጦር እና የስልጣኔ ባለቤቶቹ ምንም ስለ አጤ ምኒልክ ባላስተባበልኩኝ ነበር በዚህ መልክ ። እኔ የምናገረውም ፡ የምጽፈውም ማስረጃ አምጪ በባል ማስረጃ የማቀብበት እና ማስረጃም ገና ሳልጠየቅ በማቅረብ እታወቃለሁ ስለምጽፈው ሁሉ። ይሄም የአጤ ምኒልክ ታሪክ ከዚህ የተለየ አይደለም።
ከኢትዮጵያወርቅ (የሐረርወርቅ) ጋሻው።
ዘብሄረ አንድ ኢትዮጵያ።
Email: yehar9@aol.com

No comments:

Post a Comment