Thursday, March 30, 2017

የፕ/ር ኃይሌ ላሬቦ ባለቤት ወ/ሮ እስከዳር አውላቸው በቅርቡ በባለቤታቸው ላይ የደረሰውን አስገራሚና አሳዛኝ ሁኔታ ገለፁ


By ሳተናውMarch 30, 2017 06:05



“….. ኃይሌ የግል ህይወቱን በሚመለከት ደግ ነው፣ ጥሩ የቤተሰብ ሰው ነው፣ ቤተሰቡን የሚያከብር፤ ከዛም ውጪ ልጆቹንምየሚንከባከብ፤ ከዛም አልፎ ደግሞ ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ …. በኢትዮጵያዊነቱ በመርዳርት የሚያምን ሰው ነው።
                                                                ወ/ሮ እስከዳር አውላቸው 121ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል ዳላስ ውስጥ ሲከበር ከተናገሩትየተወሰደ
121ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ባሳለፍነው ሳምንት በዳላስና ፎርትወርዝ የኢትዮጵያውያ ጉዳዮች የውይይት መድረክ ፎረም አዘጋጅቶ ፕ/ርኃይሌ ላሬቦን በክብር እንግድነት ከተጋበዙት አንዱ መሆናቸው የሚታወስ ነው። በእለቱ ከባሌቤታቸው ጋር እንዲመጡ የተጋበዙት የፕ/ር ኃይሌ ላሬቦባለቤት ወ/ሮ እስከዳር አውላቸው በስፍራው ተገኝተው ዝግጅቱን ያዘጋጀው ፎረም በማመስገን በኢትዮጵያ ጉዳዮች በተለያየ ወቅት የግልአስተያየታቸውና ጥናታዊ ፅሁፋቸውን በሚያበረክቱት ባለቤታቸው ከሚደርሰው ዛቻና ማስፈራሪያ በተጨማሪ በመላው ቤተሰቡ የሚደርሰው ጫናለታዳሚው አስረድተዋል። ይህ ተግባር ቀድማም የነበረ ቢሆንም በቅርቡ በኢሳትና በሌሎች ኢትዮጵያ ነክ በሆኑ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት አስተያየትያልተደሰቱ ግለሰቦችና ቡድኖች በተደራጀ መልኩ በመላው ቤተሰብ ጫዋነት የጎደለው ድርጊት በመፈፀም ከፍተኛ ጫና ሲፈጥሩባቸው እንደነበርገልፀዋል። በዚህ ሁሉ አስከፊ ወቅት ከባለቤታቸውና ከመላው ቤተሰብ ጎን መቆም አስፈላጊውን ሁሉ ሲያደርጉ የነበሩትን አመስግነዋል።

No comments:

Post a Comment