Wednesday, March 29, 2017

አማሮፎቢያ (መቀሉ አየለ)




እኒህ ትምህርት ጠልተው አሮጌ ጠመንጃ ይዘው በረሃ ያደጉ መደዴ ፍየል ጠባቂ ሁሉ፤ በቁጥር ሰላሳ ያህል ሆነው ዋሻ ውስጥ ሳሉ በአንድ ሻለቃ የደርግ ጦር ድንገት ቢከበቡና መውጫ ቢያጡ ለቀናት ያህል ያለ በቂ ምግብ መቆየታቸው የተነሳ የሚበሉት አልቆ ጠኔ ሲይዛቸው እርስ በእርሳቸው የተበላሉ በላዬ-ሰብዕ መሆናቸውን በማስረጃ ተደግፎ ወጥቶ አንብበናል።የዘመን ተውሳኮች ተባይ እንደወረሳቸው እንዲሁ ያለ መጫሚያ ወደ መሃል አገር ሲዘልቁ “አማራ ጠላት ነው” ከምትል አንዲት ቃል ሌላ የሚያውቁት ምንም ነገር አልነበራቸው። ዛሬ ገንዘብ መዝረፍ ብቻ ሳይሆን ከኦፕን ዩኒቨርሲቲ የተገዛ “የትምህርት ደረጃ” ከስማቸው አጠገብ ለጥፈው መኖራቸው በውስጣቸው የሚሰማቸውን የበታችነት ቁስል ሊያክላቸው አልቻለም። እነርሱ ሚኒሊክ ቤተመንግስት ተቀምጠው አንድ ጎጃሜ ሎተሪ አዙዋሪ መጥቶ ትኬት ሲሸጥላቸው የሚያሳይ ፎቶግራፍ ወደ ህዝቡ በመርጨት እንደ ገደል ማሚቶ ተመልሶ ለራሳቸው የሚያስተጋባ ተራ ፕሮፓጋንዳ ከመሆን ባለፈ በማንኛውም ጤነኛ ዜጋ ላይ ቅንጣት ታህል ነጥብ የማያስቆጥር የወረደ “ጀብዱ” በመስራት “እኛም በዘመናችን እንዲህ ነን” ለማለት ሞክረዋል። እውነታው ግን ስር በሰደደ የበታችነት ነቀርሳ የሚሰቃዩ መሆናቸውን በአንክሮ ማረራገጡ ነው።አንዳርጋቸው ጽጌን የመሰለ የዘመናችን ቸኮቬራ ማንበርከክ የተሳናቸው ድውያን የውርደታቸው ልክ መጨረሻ ቢያጣ ነው እንዲህ ሲሆኑ የምናያቸው። 
በ 77 ዓ/ም ድርቅ ከአንድ ሚሊዮን ዜጎቻችን እልቂት ጀርባ፣ ከእነዚያ የገዛ ቆዳቸው ከሰፋቸውና ከሰለሉ እጆች ጀርባ ለአለም የተገለጠው እውነት ያ-ኩሩ! የወሎ ገበሬ እንኩዋን እንደ ደደቢት በላየሰቦች የሰውን ስጋ ሊበላ ቀርቶ እርም ነው የሚለውን የአህያውን ስጋ አልሞከረውም፤ ይልቁንም በወተቷ ልጆቼን ያሳደገች ላም አንገት ላይ እንኳን ሳይቀር “ቢላዋዬን አሳርፍ ዘንድ የአባቶቸ አምላክ፤ የአምላከ እስራኤል እርግማን፤ በእኔ ላይ የለም” እያለ ከከብቶቹ በፊት ወደ መቃብር መወረዱ ነበር።

የማጠቃለያው እውነት ደግሞ በምንም መመዘኛ በእዚህ ፎቶ ላይ የሚታዩት, የለበሱት የሃር ከረባት የማያደምቃቸው፣ የደረቡት የሱፍ ኮት የማያሞቃቸው፣ የተጣበቁበት ዙፋን ምቾት የማይሰጣቸው ድውያን አንድ ላይ ቢሰፈሩ የዚህን አንድ ኩሩ ጎጃሜ የመንፈስ ልዕልና ጫፍ ላይ የማይደርሱ መሆናቸውን ነው። ዛሬም በራሱ የሚኮራ፣ የአቸናፊነትን ስነ ልቦናን የታደለ፣ ከማንነት ወደ ሰውነት ደረጃ ያደገ ኩሩ ፣ባለችው እረክቶ የሰላም እንቅልፉን የሚተኛ፣ከራሱ ጋር የታረቀና ለራሱ ክብር ያለው ባለታመብ ነው። በዚህ ሁሉ እርብርብ ውስጥ አልሰበር ያለውን ይኽን የሞራል የበላይነት ነው እንግዲህ ይኽ ወራዳ ስርዓት “ትምክህተኝት”፣ “ነፍጠኝነት” እያለ የሚፈርጀው።
 

No comments:

Post a Comment