Monday, May 1, 2017

መልስ ያላገኘው የሠራተኛው ጥያቄ ? – (ይድነቃቸው ከበደ)




ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) እ.አ.አ ከ1890 ተጀምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። የዘንድሮ የዓለም ሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) በዓለም ለ128ኛ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሠራተኛው መሰረታዊ የነፃነት ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ለ42ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው ። የሠራተኛው በነፃ የመደራጀት መብት ከፅንሰ ሃሳብ ባለፈ ለተግባራዊነቱ ዳተኝነት የሚያጠቃው የገዢው ሥርዓት መንግሥት፣ እንዲህ ዓይነቱን የቡዱን መብት አክብሬ አስከብራለው በማለት ቀን ከለሊት የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ከመለፍለፍ ባለፈ ለሠራተኛው ሙሉ ነፃነት የሚሰጥ አንዳችም ጠብ ያለ ነገር የለም። ይባስ ብሎ የሠራተኛው በነፃ የመደራጀት መብት ተደፍጥጦ ይገኛል።

የሠራተኛው መደብ ለመብቱና ለጥቅሙ በመደራጀት ፣ጥያቄዎች የማቅረብ እና ምላሽ የማግኘት የማይገደብ መሰረታዊ መብቱ አሁን ላይ በእጅ አዙር እንዲሁም በቀጥታ ጫና እየተደረገበት ነው። ለዚህም ብዙ እርቀት መሄድ ሣያስፈልግ፣ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መመልከት በራሱ በቂ ነው። (ኢሠማኮ) የማሀበሩ ስያሜ ከመሆኑ በስተቀር ፣ ለአገዛዙ ሥርዓት ፣ የሠራተኛው መብትና ጥቅም መውሰጃና መመለሻ የአቋራጭ መንገድ ቀይ ምንጣፍ ከመሆኑ ያለፍ እዚህ ገባ የሚባል ጥቅም የሌለው ማህበር ነው። ሠራተኞች በተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ በማህበር በማደራጀት መብትና ጥቅሞቻቸውን ማስከበርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንዲሁም በሃገር ጉዳይ በጎ አሰተዋአዖኦ ማበርከት ተቀባይነት ያለው ዓለም አቀፍ ጤናማ ሂደት ነው።

No comments:

Post a Comment