Monday, May 29, 2017

የሕወሓት የደህንነት ቢሮ በኦሮሚያ ክልል የሕዝብ ንቅናቄና ግጭት ለመፍጠር እቅድ እየነደፈ ነው ።



የሕወሓት የደህንነት ቢሮ በኦሮሚያ ክልል የሕዝብ ንቅናቄና ግጭት ለመፍጠር እቅድ እየነደፈ ነው ።

Minilik Salsawi ከሕወሓት የደህንነት ሰወች የተገኘው መረጃ እንደ ሚጠቁመው የኦሕዴድ አባላት እንቅስቃሴ ያልጣመውና በኦሮሚያ ክልል ሕዝቡን የበይ ተመልካች ያደረጉት የሕወሓት ዘራፊዎች ጥቅም መነካቱ ፣ ሕወሓት በኦሮሚያ ያለውን የበላይነት እያጣ መሔዱ ፣ የኦህዴድ ሰወች ከጎሰኝነት ይልቅ የኢኮኖሚ ለውጥ ማለታቸው እንዲሁም በኢሕአዴግ ውስጥ የበላይነት ለመያዝ ኦህዴድ ማፍጠጡ ያስደነበራቸው ሕወሓቶች በኦሮሚያ ክልል የሕዝብ ንቅናቄና ግጭት ለመፍጠር እቅድ መንደፍ መጀመራቸው ታውቋል ።

በኦሮሚያና በአማራ ክልል የተሰማሩና በሕወሓት የሚደገፉ በዝባዥ የትግራይ ሰወች ስጋት ያዘለ አቤቱታ ለባለስልጣናት እያሰሙ ሲሆን የኦሕዴድ አመራሮችም በከፍተኛ ደረጃ ወደ ሕዝቡ ቢስፋፉም ሕዝቡን ዝም ለማሰኘት የተሸረበ ሴራ ነው ቢባልም አሁን አሁን ነገሮች ከሕወሓት ሐሳብና እቅድ ውጪ እየሆኑ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ ። የደሕንነት ቢሮው በኢሕአዴግ ውስጥ የተነሳውን ሽኩቻ በቁጥጥር ስር ለማዋልም እየሰራ ይገኛል ። #ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment