Tuesday, May 23, 2017

አለም የሚመራው በለየላቸው ማጅራት መቾች ነው – መስቀሉ አየለ

May 23, 2017 22:10      




ጆርጅ ቡሽና ቶኒ ብሌየር ኢራቅ ውስጥ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሰው ገድለዋል።አካለ ጎደሎ ሆኖ የቀረውና የተፈናቀለውን ሰው ሲጨመርበት ደግሞ ስሌቱን ሆድ አይችለውም። ይኽ አሃዝ የጸጥታው ምክር ቤት እራሱ በሾማቸው አጣሪ ኮሚሽን የተረጋገጠ ቢሆንም በመጨረሻ ሰአት የምርመራው ውጤት ግን ለሚቀጥሉት ስልሳ አመታት ለህዝብ እንዳይገለጥ ወስነው በደንበኛ የብረት ካዝና ቆለፉበት። ያን ግዜ ተጠያቂዎቹ በህይወት ስለማይኖሩ እንዲሁ ወሬ ዘርተው ጋዜጣ ይሰሩበታል ነው ማለት ነው።
ሳውዲ አረቢያ የሚባለው አገር የአንድ ሰው ንብረት ነው። አገሩም የተጠራው የዛሬ መቶ አመት ገደማ በነበረው የዘላኖቹ አለቃ ስም ነው፤ አልሳውድ ይባል ነበር፤ የንጉሳዊ ቤተሰብ እየተባለ ዛሬ ድረስ የዘር ግንድ የሚመዘዘው ከዚህ ሰው ነው። የርሱ የልጅ ልጆች ደግሞ አይሲስ የሚባል አደገኛ ቫይረስ ፈጥረው ይኸው አለሙን መከራ ያበሉታል።ነገሩ እንዲህ ነው። በዚሁ በሳውዲ አረቢያ ውስጥ በአስገድዶ መድፈር፣ በድራግ ሽያጭ፣ በግድያ፣ በኦርጋን ትራፊኪንግና በሌሎች ከባባድ ወንጀሎች ተከሰው የሞት ፍርዳቸውን ይጠብቁ የተነበሩትን ወንጀለኞች በሚስጥር ከእስር ቤት አውጥተው አይሲስን ሲፈጥሩ እና መካከለኛውን ምስራቅ በእሳት ሲያነዱት የምዕራባውያን ቡራኬ ስላለበት ነው።
ዛሬ ሳውዲ አረቢያ የሚባል የፍየል ጠባቆዎች ስብስብ የመንን ከደቡብ አሜአሪካና ከምስራቅ አውሮፓ የጦር አውሮፕላን የሚያበሩ መርሰነሪ ገዝቶ ያስደበድባል፤ዛሬ የመን የሰው ደም ለጠማው የዘመኑ ኢሊምናቴና መሶናይት የተሰጠች የመስዋእት ጠቦት ሆና እለት እለት እንደመና የእሳት ድኝ ከሰማይ ይወርድላታል። በውስጥ በተደረገ ስምምነት ማንኛውም አይነት የምእራቡ የዜና ትቋም ስለየመን አዳርና ውሎ ትንፍሽ እንዳይል ተደርጎዋል።
የጸጥታው ምክር ቤትም ሆነ የተባበሩት መንግስታትም ቢሆኑ ስለጉዳዩ አጀንዳ ይዘው ለመወያየት እንኩዋን ፈቃደኛ አይደሉም።
ዩክሬንን ጨምሮ የምስራቅ አውሮፓ አገሮች ሁሉ ከአሜሪካኖቹ በላይ አሜሪካዊ መሆን በሚፈልጉ ባንዳ መሪዎች እንዲሞሉ ተደርጎዋል።አንደበተ ቁጥቧን ፕሬዝደንት ዲልማ ሮውሴፍን ያህል ቅን መሪ አንስተው ነፍሱን ለአሜሪካ የሸጠውን ማይክል ተመርን ያነገሱት ብራዚላውያን ዛሬ አይናቸው ሲገለጥ ውረድ ማለት ጀምረዋል።እርሱ ስልጣን ላይ በወጣ ማግስት ድፍን ብራዝሊን ለአሜሪካ በቆዳ ምላሽ መቸብቸብ ሲጀምር ብራዚላውያን ግን ዘግይተውም ቢሆን አይናቸውን በመግለጣቸው አገሪቱ ሌላ ዙር ትርምስ ውስጥ መገባቷ ነው መዘዙ።
እንዲህ ካናቱ የገማ አለማቀፍ ተቋም እረጋ ብለው ሲያዩት ነገሩ ሁሉ ይበልጥ ውስጡን ለቄስ ነው። በነፍስ የሚስያቡ ሰዎች ገብተው የሚወጡበት አይደለም።ዛሬ እነ ቢልጌት ደግሞ የአለምን የህዝብ ቁጥር ለመቀነስ ብዙ ገንዘብ የፈሰሰበት ትላልቅ ፕሮጀክት ይዘው በር ላይ እየጠበቁ ነው። ለዚህ ፖሊሲ ተፈጻሚነት ደግሞ ቴድሮስ አድሃኖም የመሳሰሉ የፍናፍንት ስነልቦና ያለው ደርቲ ሰው ያስፈልጋል። ሁለት አመት ሙሉ አሰልጣኝ ቀጥረው ሲያዘጋጁት መክረማቸው ለዚሁ ነበር።
ነጮችን የቢግባንግ ባሌቤት ያደረጋቸው የለም፤ ይኽች ምድር የሁሉም ናት ባለቤት የላትም። ሰው ሆነን የተፈጠርን እኛ ይሕችን ፕላኔት ከሁሉም ተጋርተን ለመኖር የማንም በጎ ፈቃድ አያስፈልገንም። ቆዳውን ቀይሮና ስሙን አሳምሮ ነገር ግን የሂትለሩን የዘር ፍጅት ሚንስቴር ጆሴፍ ጊዮብልስን ተክቶ የመጣው ቢል ጌትና ኩባንያው በዛሬው እለት ሁለት እግሩን በአለማቀፉ የጤና ድርጅት ላይ ተክሏል። ከዚህ ሴራ ጀርባ ያለውን እውነት ደግሞ ያየነው እኛ ኢትዮጵያውያን ብቻ በመሆናችን ብቻችንን ጮኸናል። በተጻራሪው ፤ጆሮ ዳባ ልበስ ማለቱን የመረጠው አለም ግን ከጩኸታችን ጀርባ ያነበረውን ቁጭት አንድ ቀን በዓይኑ ያየዋል።
ባለፈው ሰሞን የራሽያው ፕሬዝዳንት ፑቲን በአደባባይ ወጥቶ እንዳጋለጠው በኮንጎ ውስጥ ተበትኖ ድፍን ምእራብ አፍሪካ ከአንድ አመት ለበለጠ ግዜ ሲበላው ከከረመው የኢቮላ ሰደድ እሳት ጀርባ እጁ ያለበት ዋነኛው ሰው ቢልጌት መሆኑን እንዲሁም የአለም የጤና ድርጅት አፋጣኝ እርምጃ እንዳይወሰድና የሰዎችን ህይወት መታደግ እንዳይቻል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ለበርካታ ወራት ድምጹን ያጠፋው በዚህ በጡት አባቶቹ በነቢልጌት ተጽእኖ እንደ ነበረ እንቅጩን አውጥቶ ለአለም ህዝብ አሳይቷል።
በዚሁ አጋጣሚ ግን ግልጽ መሆን ያለበት አንዱ ቁልፍ ጉዳይ በግዜው ድፍን አለም የበረራ መስመሩን በሙሉ ፤ የንግድ እንዲሁም የቱሪዝም አገልግሎትን አቋርጦ፣በሩን በምዕራብ አፍሪካ ላይ ሲዘጋ፤እነ ሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫን እስከ መሰሰረዝ ሲደርሱ የወያኔው ሚንስቴር ግን ቁጭ ብሎ ሲያሰላ የነበረው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚገኘውን ትርፍ ሲሆን ይባስ ብሎ በመቶ የሚቆጠሩ ፤ዕእርዳታ ሰጭ ታስክ ፎርስዕ ወደ ላይቤሪያ ካዘመተበት ባዶ እብሪት ጀርባ ያለውን እውነት መጎርጎሩ አይከፋም።

No comments:

Post a Comment