Monday, May 22, 2017

ባንዳው ማነው? መጋረጃው ሲገለጥ !……… [ቬሮኒካ መላኩ]

[ቬሮኒካ መላኩ]
…………………………
ባለፈው የፈረንጆቹ አዲስ አመት አካባቢ አንድወዳጄ ከወደ እንግሊዝ ” እስኪ እነዚህን ዶኪመንቶች የሚጠቅሙ ከሆነ ” በማለት ላከልኝ ። ሁለት መፅሃፎች እና የእንግሊዝ ፓርላማ በ 1868 አካባቢ ኢትዮጵያን ለመውረርና አፄ ቴዎድሮስን ለመውጋት ውይይት ያደረገባቸው ቃለ ጉባኤ ኮፒ ኖሯል የላከልኝ ። ያን ቃለ ጉባኤ ሳነበው አንዱ የእንግሊዝ ፓርላማ House of Lords አባል የትግራይ ገዥ የነበረውን በዝብዝ ካሳ (በኋላ አፄ ዮሃንስ) በባንዳነት እንደሚረዳቸው ማረጋገጫ እንዳገኘ የተፃፈውን አነበብኩኝ።
ሌላው መፅሃፍም ውስጥ የበዝብዝ ካሳ ሰራዊት ከዝሆንና ከበቅሎ የተረፈ የእንግሊዝን ጓዝ በትከሻው ተሸክሞ ወደ መቅደላ ሲገሰግስ ያሳያል ። እንደዚሁ በሌላም ቀን የአምባሳደር ዘውዴ ረታን መፅሃፍ ሳነብ የአፄ ዮሃንስ የልጅ ልጅ ደጃዝማች ሃይለስላሴ ጉግሳ መቀሌ ከተማ ላይ የኢትዮጵያን ባንድራ አውርዶ የጣሊያንን ባንድራ ሲሰቅል የሚያሳየውን ፎቶ ተመልክቼ ቅፍፍ ብሎኝ ውሎ ነበር።

ሰሞኑን በስፋት በዚህ ማህበራዊ ድረገፅ “ባንዳና ” “ኢትዮጵያዊ ” የሚሉት ስያሜዎች በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው። አስገራሚው ነገር ታዲያ “ባንዳ ” የሚለውን መጠሪያ ለሌላው እየተጠቀሙ ያሉት የባንዳወቹ የልጅ ልጆች ሲሆኑ “ኢትዮጵያዊ ” የሚለውንም ሲጠቀሙበት የታዩት ለወትሮው ኢትዮጵያ የሚል ስም ሲሰሙ የሚያንገሸግሻቸው እና ትግሬ ሪፐብሊክን ለመመስረት ትግል ከጀመሩት ኢትዮጵያ ጠል ከሆኑ ሰዎች መሆኑ ነው ።

ታድያ ይሄ ጉዳይ ሲደጋገምብኝ አንድ የአገሬ አርሶ አደር የተናገረውን ተረትን አስታወሰኝ፡፡ «አያ ለመሆኑ ብሳና ይነቅዛል ? ;» ቢለው
«… ምን ነካህ ለእንጨቱ ሁሉ ያስተማረው ማን ሆነና» አለ ይባላል።
እረ ጎበዝ እንከባበር እንጅ? “ለመሆኑ ባንዳነት ለአለም ህዝብ ማን ያስተማረውና? ” እንደው እንደዚህ ያለውን ድፍረትና ቅጥፈት ከወደየት አገኛችሁት?

ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ባለፉባቸው ዘመናት ማለት የሚፈልጉትን በቅኔ፣ በግጥምና በግዕዝ ችሎታቸው እየታገዙ ጠንካራና አመራማሪ መልዕክቶችን ያስተላልፉ ነበር አሉ ።
በጣሊያን ዘመን አገርን ከወረራ ለማዳን አርበኛው በዱር በገደሉ ሲዋጋ ህዝቡም ህይወቱን ሲሰዋ ጥቂት ሰዎች ግን ለጣሊያን በባንዳነት አድረው ክህደታቸውን በግልጽ ያሳዩ ነበር። የነዚህን አድር ባዮች መጥፎ ምግባር የሚያውቁት ነጋድራስም በቅኔ ሸንቆጥ ያደርጓቸው ነበር አሉ ።
ታድያ አንድ ቀን ንጉሡ በተገኙበት የዒላማ ተኩስ ላይ ከወደ ትግራይ የመጣ በፊት በባንዳነት የሚታወቅና ቤተ መንግስት አካባቢ የሚያረጠርጥ ሰው በመጀመሪያው ጥይት አልሞ ይመታል። ይህ ሰው በጠላት ወረራ ወቅት ባንዳ እንደነበረ የሚያውቁት ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ «ወይ ጉድ ባንዴ ቡን አረጋት»ሲሉ በቀልድ ባንዳነቱን ነገሩት አሉ ።
አንዱ የባንዳ ዋና ፀባይ ከመጣው ጋር ልጥፍ የማለት አስመሳይ ባህሪያቸው ነው ።

መቼም በቅርብ አመታት በተከታታይ በኢትዮጵያ ጦርነቶች በተሳተፉ ፈረንጅ የአይን እማኞች ታትመውና ተተርጉመው የወጡት መፃህፍት ስለ ባንዳነትና አገር ክህደት የዘረገፉት ታሪክ ጉድ የሚያስብል ነው። ለካ ባንዳም የሚበቅልበት የተወሰነ ቦታና መሬት አለው የሚያስብል ነው ።

በኮሌኔል አሌህንድሮ ዴልባዬ ተፅፎ በተስፋዬ መኮንን የተተረጎመው ” ቀይ አንበሳ ” እና የሃበሻ ጀብዱ በሚል ርእስ በተጫነ ጆብሬ መኰንን የተፃፈውን ታሪክ የጣሊያን ወረራን ለመመከት የኢትዮጵያ ጀግኖች ያደረጉትን ታላቅ መስዋዕትነት የሚተርኩና የትግራይ ባንዳዎች በአርበኞችና በአገር ላይ የፈፀሙትን ለመግለፅ እንኳን የሚያሸማቅቅ ጉድ ዘርግፈውታል ። ለአርበኞች በእንጀራና በውሃ የውሻ መርዝ እየጨመሩ እስከመስጠት የሚደርስ ባንዳዊ ተግባር ሲፈፅሙ ያስነብቡናል ።

የመጽሐፎቹ ጸሐፊ የቼክ ተወላጁ አዶልፍ ፓትሪክ እና አሌህንድሮ ደል ባዬ ጃንሆይ ከውጪ ሀገር ለጦር አማካሪነት ካስመጧቸው ጥቂት የውጪ ሰዎች መካከል ናቸው። ፓትሪክ በታማኝነት ልክ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ አርበኛ በቆራጥነት በተለያዩ ግንባሮች የጣሊያንን ጦር የተፋለሙና በቅርብ የራስ ካሳ አማካሪ በመሆን በተለያዩ የጦር አውድማ የተደረጉን ጦርነቶች በውጊያ በስለላና በምክር የራስ ካሳን ጦር እስከመጨረሻው ሲያግዙ የቆዩ በመሆናቸው ይህ መጽሐፋቸው ።
ጀግና ባለበት ጥቂት እንክርዳድ ባንዳ አይጠፋምና በትግራይ የነበሩ ሽፍቶች ከወገናቸው መሳሪያ ለመንጠቅ ሲሉ በወገናቸው ጦር ላይ በተለያየ ጊዜ ያደረሱት ጉዳት ቀላል እንዳልነበር ያስነብቡናል።

የአገራችን ሰው “ቆማጣን ቆማጣ ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል።>> አ ንደሚባለው ጭምብሉ ተገፎ እስኪታይ ድረስ ደግሞ ትርምስና መደነጋገር ውስጥ ሳይገቡ በረጋ መንፈስ ነገሮችን ለማጣራትና መርምሮ ከእውነቱ ለመድረስ ጊዜ መስጠት ያስፈልጋል በማለት ዝም ብንላቸው የሹምባሽ ልጆች ባልዋሉበት ኩበት ለቀማ ሲሄዱ መመልከት ትእግስት የሚያስጨርስ ጉዳይ ነው ።

ይች ለአለም ጤና ድርጅት የምትደረግ ውድድር ያመጣችው ጣጣ መሆኑ ነው። በዚህም የተነሳ የአርበኛ ልጅ ባንዳ ፣ የባንዳ ልጅ ደሞ አርበኛ ሲባል እየሰማን እያነበብንም ነው።
የወያኔዎች እና የልጆቻቸው ውሸት እና ተንኮል የሚገር መሆኑንም እየተመለከትን ነው ። የዘመኑ አራዶች «ስጥ፤ ቀደዳ፤ ረገጣ፤ ሌላም ሌላም» የሚሉት አይነት መሆኑ ነው ። ውሽት እንዲህ በተለያየ ስያሜ ሲጠራ የእሱ አጋፋሪ የሆኑት ደግሞ «ቀዳጅ፤ ሰጪ፤ ረጋጭ» መሆናቸው ነው ።
የቴዎድሮስ አድሃኖም አይነቱ ውሸታም ደግሞ ባልዞረ ባልነበረበት ጉዳይ እንደነበረና እንደተካፈለ አድርጎ «ሲረቅ ተመልክቻለሁ፤ ሲፈረምም አይቻለሁ» ብሎ ውሸቱን በመሀላ የሚያፀድቅ፤ ልፈለጥ፤ ልቆረጥ ብሎ የሚልና የሚምል፤ ምላጭ የሆነ ውሸታም ከአፈርኩ አይመልሰኝ የሚል ዓይነት ሰው ነው። የህፃን ብሪቱን ጉዳይ ማስታወሱ ብቻ በቂ ነው ። ሰሞኑን ዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣም ዉሸቱን በአለም አደባባይ ይፋ አውጥቶታል ።

ባለፈው ፅሁፌ ቴድሮስ አድሃኖምን የቬኑሱ ነጋዴ ሻይሎክን ነው ብዬ ነበር። ቴድሮስ ሻይሎክ ብቻ ሳይሆን ኢያጎም ጭምር ነው።
በሸክስፒር « ኦቴሎ» ቲያትር ውስጥ የተሳለው ገፀ- ባሕርይ ኢያጎ በውሸቱ የየዋሁን «ኦቴሎ» ን ልብ አታልሏል፡፡
የኢያጎ የሀሰት (የውሸት) ዘር ኦቴሎ ልቦና ላይ ተዘርቶ በሕሊናው በቅሎ ካደገ በኋላ ምንም በማታውቀው በዴዝዲሞና የሕይወት አውድማ ላይ ተወቅቷል፡፡ የውሸት ውጤት ጥፋት ሆኗል ። የሕይወት ዋጋ አስከፍሏል። የዋሾዎች ግብ ይሄው ነው። ኢያጎ በሰይጣናዊ ሀሳቡ ያተረፈው ነገር የለም። ሊኖርም አይችልም። ቴድሮስም ኢያጎና ሻይሎክን አጣምሮ የያዘ ከይሲ ነው። በአማራ ሴቶች ላይ የፈፀመውን ግፍ ማስታወሱ በቂ ነው ።

ሳላስበው ወደ ሌላ አጀንደ ገባሁኝ መሰለኝ ። ይሄ አህያ ቀንድ ፣ አሳማ ክንፍ አወጣ አይነት አስቂኝ የባንዳነት ባህሪ ለአማራው የሰጡት መሰለኝ ። << ጉድ በል ጎንደር> > ይሄ አይነት ውሃ ሽቅብ አይነት ሲገጥመው መሆኑ ነው ። ምፀቱም ይሄው ነው ።
አማራ የውጭ ጠላት በመጣ ቁጥር ክተት ሥራዊት እየተባለ በራሱ ስንቅና ትጥቅ በባዶ እግሩ በመዝመት የአገሩን ዳር ድንበርና ወገኖቹን ከውጭ ወራሪ ጠላትና ከባርያ ፈንጋይ የዓረብ ነጋዴዎች ሲከላከልና ሲጠብቅ
መኖሩን ታሪክ ምስክር ነው።
አማራ ለአገሩ መንግሥትም ሆነ ለወገኑ ታማኝ፤ ከመሆኑ የተነሳ ለውጭ ጠላት ፈጽሞ የማይመችና የማይታለል በመሆኑ ይኸው አገራችን ኢትዮጵያ ዳር ድንበሯ ሳይደፈር አሁን ላለው ትውልድ እንድትደርስ ከፍተኛውን አስተዋጽዖ ያደረገ ኩሩና ጀግና ሕዝብ መሆኑን አይደለም ኢትዮጵያዊ፤ የዓለም ሕዝብ ያውቀዋል።
ኢትዮዽያዊ ጀግንነት ሀገሬን አላስነካም ብለው የአርበኝነቱን ቀንዲል አብርተው በታላቅ መስዋእትነት የሐበሻን የጀግንነት ተጋድሎ አቀጣጥለው ወራሪውን የኢጣሊያ ሰራዊት በተቆጣጠራት አዲስ አበባ ግምባር ለግምባር ገጥመው በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰው ወደመጡበት እንድመለስ ተአማራዊ ህዝብ ነው። ስለአማራ አርበኝነት ለማውራት መሞከር አባይን በጭልፋ የሚሉት አይነት ነው።

አሁን ዛሬ ለእኛ ስለኢትዮጵያዊነት የሚሰብኩን ለትግራይ ሪፐብሪክ የተዋጉ ናቸው፡፡ ሶማሌ ኢትዮጵያን በወረረችበት ዘመን ከሶማሌ ጎን ኢትዮጵያን የወጉት ባንዶች ናቸው፡፡ መቋዲሾ ቢሮ ከፍተው በሱማሌ ፓስፖርት የታገሉን ናቸው ፡፡ ሌላም ሌላም … እንግዲህ የትግራይ ሪፐብሪክ ብሎ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚወጋ “ኢትዮጵያዊ ነኝ ” ፣ “አርበኛ ነኝ ተቆርቋሪ ነኝ” ሊል አይችልም፡፡

No comments:

Post a Comment