Wednesday, May 24, 2017

የነገረ ኢትዬጵያ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ሽፈራው የጥፋተኝነት ዉሳኔ ተላለፈበት


By ሳተናውMay 24, 2017 07:38



( የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ሸንጎ የህዝብ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ)
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው
በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2009 ዓ.ም በዋለው ችሎት የጥፋተኝነት ውሳኔ በጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራሁ ላይ አስተላለፈ::በችሎቱ ላይ እንደተነበበው ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው የሰማያዊ ፓርቲ ልሳን የሆነውን ነገረ ኢትዬጵያ ጋዜጣ እንደሽፋን በመጠቀም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ ከሰማያዊ አባላት መረጃ በማሰባሰብ በውጭ ሀገር ለሚገኘው ኢሳት ለተሰኘ የቴሌቭዥን ጣብያና ለግንቦት 7 አመራሮች መረጃ ታስተላልፋለህ የሚል ነው::
የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት አርብ ግንቦት 18 2009 ዓ.ም ተቀጥሯል:: ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው የቅጣት ማቅለያ በችሎቱ እንዲያቀርብ ቢጠየቅም ማቅረብ እንደማይፈልግ ታውቋል::

No comments:

Post a Comment