Thursday, May 18, 2017

ወያኔ በአዲስ አበባ ታክሲወች ላይ ያቀደው አደገኛ ሴራ ሲጋለጥ! – አስናቀው አበበ


By ሳተናውMay 18, 2017 06:47





 4  547  551
የግል ትምህርት ቤቶች የስለላ መዋቅር እየተዘረጋላቸው ነው
አዲስ የገንዘብ ማካበቻ ዘዴ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን ቢሮ የከተማዋን ባለታክሲዎች ከስራ ውጪ ለማድረግ ያሴረው ውጥን እንደሚከተለው ነው…
የአ.አ. ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን ቢሮ ከሚያዝያ 2009 ዓ.ም የመጨረሻ ሳምንት ጀምሮ እስከ 04/09/2009 ዓ.ም ድረስ በአጠቃላይ ለአፀደ ህፃናት እና ለ1ኛ/ደ/(ከ1-8) ት/ቤቶች በክፍያ ወደ ት/ቤት ለመሄድ እና ለመመለስ የተማሪዎች ትራንስፖርት ሰርቪስ/አገልግሎት እሰጣለሁ ብሏል፡፡ ለዚህም የፍላጎት መረጃ/Need assessment /ቅፅ ለሁሉም ት/ቤቶች በትኖ የተሞላውን መረጃ አሰባስቦ በቀጥታ ወደ ስራ እንደሚገባ ለየት/ቤቶች አሳውቋል፡፡ ይህ ድብቅና በተለይም ሁሉም የግል ት/ቤቶች ከተማሪ ወላጆች ጋር ስለፍላጎታቸው በቅርበት ያልተወያዩበት ጉዳይ መሆኑን ታውቆ ዋናው አላማውም የሚከተሉት ናቸው፡-
፨፨ መንግስት ገበያውን በብቸኝነት እና በበላይነት ተቆጣጥሮ በመቀጠል የእለት ኑሮአቸው እና ገቢያቸው ለተማሪዎች የትራንስፖርት ግልጋሎት በመስጠት የሚተዳደሩትን ባለታክሲዎች ሆን ተብሎ ለመጎድት
፨፨የከተማዋን ባለታክሲዎች በተለይም በአገልግሎት ቆይታቸው አርጅተዋል ተብለው ነገር ግን በአጭር ርቀትም ቢሆን እየሰሩ ያሉትን እና ሌሎችንም በትራንስፖርት ስምሪት ምድብ ውስጥ ገብተው መደበኛ አገልግሎት እየሰጡ
በተጨማሪ የእለት ኑሮን ለማሸነፍ ሲባል ጥዋትና ማታ ተማሪዎችን በኩንትራት ታክሲ የሚያመላልሱትን ከገበያ ለማስወጣት
፨፨ እንዲሁም በአሁኑ ሰዓት ወያኔ ተተኪ ትውሉዱን በሚፈልገው የሪወት አለም ቅኝት እንዲራመድ በመንግስት ት/ቤቶች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ በየት/ቤቱ አንድ፡አንድ የአደረጃጀት ርዕሰ መ/ር ተብሎ ቅጥር በመፈፀም ዋና ተግባራቸው የድርጅት አባል ከመምህራን ፡ከአስተዳደር ሰራተኛውና ከተማሪዎች በመመልመል ርስበርስ አስተሳስሮ እንዲማቅቅ ያደረጉበትን ዘዴ ጠቀሜታ ስለሚያውቁት፡ነገር ግን በግል ት/ቤቶች ምንም አይነት መሠል መዋቅሮችን ስለማይከተሉ እና አመፅ ይኖራል ብሎ ስለሚያስብ፡የተማሪውን ስሜት፡ውሎና አቅጣጫ በቀላሉ ለመከታተል
፨፨ ወያኔ እያጣ የመጣውን የገንዘብ ገቢ መጠን ልክ በነጋዴው ማህበረሰብ ያለጥናት አዲስ የግብር ተመን ጥሎ ለመሠብሰብ ከሚኳትነው ተጨማሪ ዘዴም ነው ተብሏል፡፡
ለዘውትር አምደኛ ሪፖርተር እናመሰግናለን!
አስናቀው አበበ

No comments:

Post a Comment