Monday, May 1, 2017

ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር የደረሠ ፍንዳታ የሠው ሕይወት አጠፋ…… (ትዝታ በላቸው-VOA)



ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር መስቀል አደባባይ በሚገኘው ሚሊኒዬም የወጣቶች ስፖርት ማዕከል ውስጥ ፍንዳታ ደርሶ የሁለት ሰው ሕይወት ማጥፋቱን ቢያንስ አምስት ሠዎች መቁሰላቸውን ከአካባቢው ያነጋገርናቸው ምንጮች ገልፀውታል፡፡
ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ምሽት በባህር ዳር መስቀል አደባባይ በሚገኘው ሚሊኒዬም የወጣቶች ስፖርት ማዕከል ውስጥ ፍንዳታ ደርሶ የሁለት ሰው ሕይወት ማጥፋቱን ቢያንስ አምስት ሠዎች መቁሰላቸውን ከአካባቢው ያነጋገርናቸው ምንጮች ገልፀውታል፡፡ፍንዳታው የደረሠው ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ሰለተገደሉትና ሰለቆሰሉት ሠዎች ማንነትና ቁጥር ለማጣራት ጥረት ተደርጓል፡፡
ወደ አማራ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ንግሡ ጥላሁን ያደረግነው ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ አልተሳካም፡፡ ጥረታችንን እንቀጥላለን፡፡

No comments:

Post a Comment