Saturday, May 6, 2017

አስደንጋጭ ዜና ከወልቃይት ፀገዴ


“እስር ቤት ውስጥ ሞተ ተብሎ አስክሬን ተሰጠን” – የሟች እናት ከጽዮን ግርማ
በአማራ ክልል በተለይ በወልቃይት ፀገዴ ለወራት የዘለቁ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችን ተከትሎ፤ በቁጥጥር የሚውሉና የደረሱበት የማይታወቅ ሰዎች መበራከታቸውን በሰሜን ምእራባዊው ግዛት የባህልና ማንነት ጥያቄ አንስተው ይንቀሳቀሱ የነበሩ የማህበረሰብ ለውጥ አቀንቃኞች ይገልጻሉ። ዘነበ ጫቅሌ ዩሃንስ የተባለ የሁለት ልጆች አባትና የ32 ዓመት ወጣት ዳንሻ ከብት ገበያ ውስጥ ከብት በመነገድ ላይ እያለ መጋቢት 23 ቀን 2009 ዓ.ም በፖሊሶች ተይዞ ከተወሰደ ከሁለት ሳምንት በኋላ በእስር ቤት መሞቱን ቤተሰቡና በቅርብ የሚያውቁት ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ገልጸዋል። ሟች ለፋሲካ በዓል ለቤተሰቡ ደውሎ የቀረበበትን ክስ በፍርድ ቤት እንደሚሟገት ተናግሮ እንደነበል ወላጅ እናቱ ተናግረዋል።
እንዴት ሞተ? ቤተሰቦቹ የተሰጣቸው ምክንያት ለማመን የሚያስቸግር እንደሆነ ገልጸው፤ አስከሬኑ መመርመሩን ተነግሯቸው ውጤቱን ግን እንዳልሰሙ ተናግረዋል። በወልቃይት ፀገዴ የማንነት ጥያቄ ላይ የተሳተፉ፤ ከመሪዎቹ ጨምሮ በእስር ላይ መሆናቸውንና ደብዛቸው የሚጠፋና ድንገት የሚሞቱም አሉ ሲሉ የእንቅስቃሴው አደራጆች ገልጸውልናል።
የፀገዴ ወረዳና የሽሬ ፖሊስ እንዲህ የሚባል እስረኛ “እኛ ጋር አልነበረም። የኛ እስር ቤቶች የእስረኛ ዴሞክራሲያዊ መብት የሚከበረባቸው ናቸው” ብለዋል። የእንዳ አባ ጉና ፖሊስ ሃላፊ በበኩላቸው በአካል ካልተገኘን ምንም መረጃ እንደማይሰቱን ገልፀዋል።

No comments:

Post a Comment