
ይህን እንድል ካስቻሉኝ ነገሮች በጥቂቱ

ላለፉት 40 አመታት የኦነግ ፖለቲከኞች የሳቸዉን ታሪክ በመጥቀስ ተሰድበናል እያሉ እንደማጣቀሻ ያደርጓቸዋል፣፣
ስለ ስዉር እጆች ይህን ካልኩ፣፣ ደራሲዉ የጀሚላ እናት የሚለዉን ድርሰት ከጣፈ በኋላ በኦ.ኤም.ኤን ቀርቦ በኩራት ይህ ታሪክ ሀሰት ነዉ የሚል መጥቶ ይሞግተኝ እያለ ሲያወራ እኔ በተጨበጠ መረጃ እንደምረታዉ አቅ ነበር፣፣ ነገር ግን እሱ በትልቅ ተቋማት ከለላ፣ በከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ፣ በብዙ ማወናበጃወች እየታገዘ፣ እኔ አንድ ለፍቶ አዳሪ ምን ለዉጥ ላመጣ ብየ የወጣት ጉልበቴን አደከምኩት፣፣ ግን ከልቤ አዘንኩ ፈጣሪየንም አምላኬ የዚህን ሰዉ ሴራ ለዚህ ህዝብ ግለጥለት ብየ ጠለይኩ፣፣ ወደ ጭብጡ ልግባ፣፣ ከላይ የለጠፍኩት ፎቶ በደቡብ ወሎ ወረኢሉ ከተማ ዉስጥ በቀዳማዊ ኀ/ ስላሴ ዘመን የተገነባዉ የልእልት የሽ እመቤት አሊ ትምህርት ቤት ነዉ፣፣ ልእልቷ የአሊ አባ ጋምጮ ልጅ ናቸዉ፣፣ ታሪኩን ዳዊት ከበደ ወይሳ በተብራራ ሁኔታ ስላስቀመጠዉ መድገም አልፈልግም፣፣ እኔ ከነዚህ ሰዎች ቤተሰብ ጋር አብሬ ነዉ ያደኩት፣ ሽማግሌወቹንም ደርሸባቸዋለሁ እሱ የሚለዉን ተረት አንዳቸዉም አልነገሩን፣፣ በተለይ የወንድማቸዉን የደርብ ሀሰን አሊ ቤተሰብ በአካልም ማቅረብ ይቻላል፣፣
ይህ ቤተሰብ ደርግ እስከመጣበት ድረስ በወረኢሉና በጃማ እጂግ የተከበረ ባለብዙ ሀብት ነበር፣፣ የነበረዉ ዘዉዳዊ ስርአት ሲወድቅ ልክ እንደሌሎቹ ሁሉ ከሀገሪቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ተገለለ እንጂ እሱ እንዳለዉ ሙስሊም በመሆናቸዉ የተገለለ የተገደሉ፣ ወይም እንዲጠፉ አልተደረጉሩም፣፣ ለዚህ ማሳያዉ በስማቸዉ የተሰራዉ ትምህርት ቤት አንዱ ነዉ፣፣
የተስፋየ ትልቁ ችሎታ የተወሰኑ የታሪክ ጭብጦችን ይሰበስብና ከላይ በልብ ወለድ ታሪክ ከሽኖ ያቀርበዋል፣፣ ሲያቀርብ ደግሞ የወቅቱን የፖለቲካ ትኩሳት በማየት ነዉ፣፣ ይህ ታሪክ ሲጥፍ በሀገራችን ከፍተኛ የሆነ የድምጣችን ይሰማ ሰላማዊ ትግል የነበረበት ወቅት ስለሆነ በግርግር የሰቅሰቂያ ጦሩን ይዞ ያሉብንን ጠባሳወች በደንብ አድርጎ እስኪደማ ድረስ ይሸቀሽቃቸዋል፣፣
ስለ ሀገራችን አፍራሽ ታሪክ በባእዳን ሰዎች ከብዙ አመታ በፊት ጀምሮ ሲጥፉ ነበር፣፣ በተለይ ጣሊያኖች ከአድዋ ሽንፈታቸዉ በኋላ አስመራ ዉስጥ ኤጀንሲያ ፕሮፖጋንዳ የሚባል ተቋም አቋቁመዉ ልክ አሁን ተስፋየ እንደሚያደርገዉ እዉነቱን ከዉሸቱ በመቀላቀል በኤርትራ እና በሶማሊያ ለህዝቡ ይረጩ ይበር፣፣ ያሁሉ መርዝ በኛ በኩል ምንም ጠንካራ ተቋም ስለሌለ እና ጉዳቱንም አርቀን ስለማንመለከት መከላከል አልቻልንም፣፣ ልብ ይስጠን፣፣
ጉግሳ ነኝ
የወረኢሉ ከተማ በከፊል
No comments:
Post a Comment