Tuesday, May 2, 2017

በወገኖቻችን ላይ በ ሕወሃት ና ደጋፊዎቹ የሚፈጸምውን የግፍ፣ ሰቆቃ ና ወንጀል በአለም አቀፍ ስለመምዝገብና ማስርጃ ስልመያዝ አስፍላጊነት። (በሙሉቀን ገበየው)




ባልፉት 26 አምታት በላይ፡ ሕወሃትና ደጋፊዎቹ  በኢትዮጲያውያን ወገኖቻችን ላይ የፈጸሙትና እይፈጸሙት ያሉት በደል፣ግፍ ና ስቃይ ስፍር ቁጥር የለውም። የሰው ልጅ በወገኑ ላይ እንዲህ ያለ ጭካኔ መፈጸሙን መስማት ለማመን ይከብዳል። ይህ ወንጀላቸው ግድያ፣ እስራትን፣ ግርፋትን፣ ማፍናቀልን፣ከስራ ማባረርን፣ ማስቃየትን(የአካል፣የኧአምሮ፣ ስሜት፣ የገንዝብ/ንብርት የምሳስሉትን) በዘር ማጽዳትና  ሌላውንም ይጨምራል።

በዚህ ስቃይ ያለፉ ወግኖቻችን፡ በቃልና በጽሁፍ የሚያቀርቡትን ማስርጃዎች መስማት እጅጉን አደርጎ ይረብሻል ፤ይዘገንናልም። ይህን ወንጅል የሚፈጽሙት ወንጅለኞች በህይውት ያሉና፣ በስልጣን ላይ የተቀመጡ፤ አሁንም እጥፍ ድርብ ሰቆቃን የሚፈጽሙ ናቸው።

ይህን አስከፊ ወንጀል ለመምዝገብና ለማስርጃነት ለመያዝ የሞከሩ ድርጅቶችና ግልሰቦች ቢኖሩም፤ ስፋትን ጥልቀት ባለው አብዛኛውን ሰቆቃ ለማስርጃነት መዝግቦ በቀጣይነት፤ እንዲሁም ኢትዮጲያውያን በቀላሉ ሊመዘግቡት በሚችል መልኩ የተዛጋጁ አይደለም። ይህም በሚደርሰው ጫናና በተለያዩ ምክንያቶች ነው።
የቀድምው የኢትዮጲያ ሰበአዊ መብት ጉባኤ (ኢሰመጉ በ ፕሮፌሰር መስፍን የተመሰርተው) እና በወጣቱ ጸሃፊ ሙሉቀን ተስፋሁን በአማራ ወጎኖች ላይ የደርሰውን እንግልትና ስⷃይ በመጽሃፉ ማስፈሩ የሚጠቀሱ መልካም ማስርጃ የማኖር ስራዊች ነብሩ።

አሁን ያልንበት ዘመን የመረጃ ዘምን ነው። መረጃ በቀላሉ የሚምዘገበብት፣ የሚሰራጭበት  ለሌላም ጊዜ ማስቀመጥ የሚቻልበት ዘመን ነው። ባልፉት 2 አምታት እንኳ በመሃበራዊ ሚዲያ የቀርቡ አንዳንድ ሰቆቃዎችን ለማየት፣ለማንበብ ችልናል። በተደራጀ፣ ቀለል ባል መልክ፣ ሁሉም ሊያየውና በማስርጃ ሊመዘግብ የሚያስችል  አለምአቀፋዊ መዝገብ (electronic) ያስፈልገናል።

ሳይመን ዊዘንታሃል የሚባል  በ ናዚ የስቅይ ማጎሪያ ቤት(Holocaust)  የተሰቃየና በኋላም ናዚዎችን የማደን (ማሳደድ)  እና በመከታተል፣ ማስርጃ ያኖር ይሁዳውያን  ታዋቂ ጸሃፉ ነበር። ሳይመን በወግኖቹ ላይ ሰቆቃ የፈጸሙትን የናዚ ወንጅለኞችን ማስረጃ በማሰባሰብና በመከታትል ብዙ ወንጅለኞቹን ከሁለትኛው የአለም ጦረነት ቦኋላ ለፍርድ ያቀረበ፡ በይሁዳውያን ላይ የደርሰወን ሰቆቃ የሚመዘግብ ማእከል በቪያና 1961 (እአአ) የመሰረተ ታላቅ ሰው ነበር። የሱ ስራዎች  ብዙ ናዚዎችን በህይወታቸው እርፍት የነሳና ለፈርድ ያቀርበ ስው ነበር።

እኛም ኢትዮጲያውያን የተደራጀ፣ በቀላሉ ሊሰበስብ የሚያስችል፣ ማንኛውም ኢትዮጲያዊ  የደረሰብትን፤ የተመለከተውን፣ ሌሎች ያሳወቁትን የሕውሃት ወንጀለን፤ ሊዝገብወ የሚገባ አለማቀፋዊ ባሀረ-ማስረጃ መዝገብ ያስፈልገናል። እንዚህ የህወሃት ወንጀልኞች የትም ቢደብቁ፣የሚፈጽሙት ወንጅል የማይረሳና ወደፊት እነርሱን በህግ ስር ለማቅርብ የሚረዳ መሆኑን ሊያውቁት ይገባል።

ስለዚህም፡ በአለም ላይ ያልችሁ ኢትዮጲያውያንና የኢትዮጲያን ወዳጆች ሁሉ፤ በመረጃ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በ ህግ ሞያ (Information Technology and Law) እውቀቱና ልምዱ ያላችሁ፡ ይህን አለምአቀፋዊ  ኢትዮጲያውያን ላይ የሚደርሰወን ወንጅል የሚመዘግብ ባህረ-መዝገብ (Data base, website) እንድታቋቁሙ ጥያቄ አቀርባልሁ። ለዚሁም በሚያስፈልገው መልክ (በምከር፣ በገንዝብ፣ በመሳስሉት) ለመርዳት ብዙዎቻችን ፍላጎቱ አለን።

እንዲህ ያል የመረጃ ማእከል፡በቀላሉ በይትኛውም የአለም ከፍል ያለ ኢትዮጲዊ የደርሰበትን፤ ያየወን ወይም የሰማውን መርጃ፣ ማስረጃ (የጹሁፍም ይሁን የድምጽ ወይም ምስል) እና ተገቢውን መረጃ በማን፤ የት፣መቼ፣ምን አይነት ስቅይ/በደል፣የወንጅሉ ውጤትና ሊሎችንም መምዝገብ ያስችላል።ለወደፊቱም ማስርጃ ይሆናል።
ዘመናዊ Information Technology ምስጋና ይገባውና ባሁኑ ሰአት መረጃ በ ወያኔ ላይ ለምሰብሰብ እንደ ሳይመን  ዊዘንተሃል ከአንዱ አለም ወደ ሌላ አለም መጓጓዝና መድከም የለብነም።

ምንም እንኳ ይህ ሃሳብ ቀለል ያለ ቢምስልም ወያኔ ላይ ለሚደረገው ትግል አስፈላጊና ጠቃሚም ነው። የዛሬ ባለስልጣኖች የነገ በፍርድ መንብር ተንበርካኪዊች እንዲሆኑ ያስችለናል።

(በዚህ ሃሳብ ላይ ኢትዮጲያውያን የሚሰጡትን ምክር ተከትሎ ሁለተኛ ክፍል ጽሁፍ ይቀጥላል።)

No comments:

Post a Comment