Thursday, November 17, 2016

አንድ አባት ሦስት ልጆች እንደተገደለባቸው ገለፁ


ፎቶ ፋይል
“እኔ ገጠር ተቀምጬ ልጆቼን ከተማ ነበር የማኖራቸው፡፡ በታጣቂዎች መገደላቸውን ሰምቼ ወደ ሚኖሩበት ከተማ ስሄድ የሦስቱንም ወንድ ልጆቼን አስከሬን ደጄ ላይ ወድቆ አገኘሁት” – አቶ ጀማል ሰኢድ ለአሜሪካ ድምፅ ከተናገሩት የተወሰደ ነው፡፡
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በምስራቅ አርሲ ዞን ውስጥ በሽርካ ወረዳ ነዋሪ የሆኑ አቶ ጀማል ሁሴን የተባሉ ግለሰብ ሦስት ልጆቻቸው በታጣቂዎች እንደተገደሉባቸው ለአሜሪካ ድምጽ አፋን ኦሮሞ ዝግጅት ክፍል ገለጹ።
“ምናልባት በህይወት ኖሬ ዐይምሮዬ ትክክል ከሆነ ‘ልጆቼ ምን አደረጉህ?’ ብዬ መንግስትን እጠይቀው ይሆናል” ብለዋል።
የወረዳው አስተዳዳሪ ሁኔታውን በስልክ ከመስማት ውጪ አካባቢው ላይ ስለሌሉ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
በዚህ ዞን ሌላ ወረዳ ውስጥ ተጨማሪ ግድያ መፈፀሙን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ጃለኔ ገመዳ ያጠናቀረቸውን ሪፖርት ጽዮን ግርማ አሰናድታዋለች።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

No comments:

Post a Comment