Monday, November 14, 2016

የእርስ በእርስ የጅምላ ፍረጃ ይቁም።ኪሳራው ከባድ ነው።


Minilik Salsawi – የእርስ በእርስ የጅምላ ፍረጃ ይቁም።ኪሳራው ከባድ ነው። ሕወሓትን ከመታገል ይልቅ የጽንፍ ፖለቲካ ይዞ መላፋት ያሳፍራል። የትግሉ እውነታዎች እንደተጠበቁ ሆነው የትግል ሻሞ ያለ ይመስል ላም ባልዋለበት ኩበት መልቀምም ያሳፍራል።ኣደርባይነት ኣስመሳይነት እጅግ ኣደገኛ ነው። የእርስ በርስ መኮራኮም የጅምላ ፍረጃ ከሕዝብ ልብ የሚፈልቀውን ተኣማኒነት ያሳጣል።
የወያኔ ውሸት ስልችት ብሎን ባሌበት ጊዜ የቅፈላ ፖለቲካ የሚከተሉ የለውጥ ሃይሎች ጎታችነታቸውን ገትተው የመቻቻል የመከባበርና የመደማመጥ ፖለቲካ ኣካል ሊሆኑ ይገባል። ለውጥ የሚፈልጉ ሕዝቦች በተነሱ ሰዓት ሁሉ ኣበረታቹን ተበረታቹን የምንፈርጅ ከሆነ ኣደጋ ኣለው። ያውም ከባድ ኣደጋ። ትግል ምንም ጊዜ የሚፈልገው መቻቻልና መደማመጥ ሲሆን ፍረጃ ቅፈላ እና የውሸት ፖለቲካ ያልበሰሉ ካድሬዎች ጩኸት ስኬቱን ያኮላሸዋል፤
ዛሬ ላይ እኛ ብቻ እናውቅልሃለን ብለው ለሚናገሩ ሰዎች ደጋፊ የሆኑ ነገ ላይ ጠያቂ ሆነው መታለላቸውን መረዳታቸው ኣይቀርም።እውነት ቀኗን ጠብቃ ነጻ ትወጣለች።በግራ በቀኝም በመሃልም የቆማጩ የለውጥ ሃይሎች ከመፈራረጅና ከልፊያ ፖለቲካ ወጥታቹ ኪሳራቹን በማስላት ወደ ሕዝባዊ የጋራ ትግል ተሰባሰቡ።

No comments:

Post a Comment