Tuesday, November 22, 2016

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የዜጎችን መብት እየገፈፈ ነው ተባለ

Ethiopia's State of Emergency

አንዳንድ ከፍተኛ የአመራር አባላቶቻቸውን ጨምሮ በርካታ አባላትና ቁጥራቸው የበዛ ደጋፊዎቻቸው የታሰሩባቸው መሆኑን፤ ከታሰሩባቸው የአካባቢ እስር ቤቶች ዘመድ ጠያቂ ወደማያገኙባቸው ካምፖች አዛውረዋቸዋል ሲሉ ሁለት የፖለቲካ ፓርቲዎች አማረሩ።
በአስቸኳይ አዋጁ ሥም የዜጎች መብት እየተገፈፈ ነው፤ ሲሉ የከሰሱት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በእስር ላይ የሚገኙ አባሎቻቸው ያሉበት ያልታወቀ መኖራቸውንም ተናግረዋል።
አዋጁ ከመደንገጉ አስቀድሞ የታሰሩ አንዳንድ የአመራር አባላቶቻችንን
“የታሰሩበት ጉዳይ አያስከስሳቸውም፣ ሊለቀቁ ይገባል” ሲል የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ለማረሚያ ቤቱና ለፖሊስ ደብዳቤ ቢፅፍም እስካሁን ያለመለቀቃቸውን፤ እንዲያውም እንደ አዲስ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲታይ እየተደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

No comments:

Post a Comment