Thursday, November 3, 2016

የጣሊያን ፖሊስ ወደ ሃገር የሚገቡ ስደተኞችን በኤሌክትሪክ ማሰቃያና በድብደባ ከፍተኛ የሆነ ሰቆቃ ይፈጽምባቸዋል ሲል ኣምነስቲ ኣጋለጠ።


የጣሊያን ፖሊስ ወደ ሃገር የሚገቡ ስደተኞችን በኤሌክትሪክ ማሰቃያና በድብደባ ከፍተኛ የሆነ ሰቆቃ ይፈጽምባቸዋል ሲል ኣምነስቲ ኣጋለጠ። (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ኣምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ መሰረት የጣሊያ የፖሊስ ሃይሎች በሊቢያ በኩል በባህር ወደ ጣሊያን የሚገቡ ስደተኞች ላይ ከፍተኛ የሆነ የማሰቃየት ተግባር ይፈጽማል ሲል ገልጿል። መግለጫው ከስደተኞችና ከጣሊያን ፖሊሶች ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ እንዳለው በድብደባ በኤሌክትሪክ ማሰቃያና በተለያዩ የቶርች ዘዴዎች ከፍተኛ ስቃይ በስደተኞቹ ላይ ይፈጸማሉ ሲል ኣጠንክሮ የፖሊሶቹን እኩይ ተግባር ኣውግዟል።
ይህ ከፍተኘ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሊከሰት የቻለው የኣውሮፓ ሕብረት ስደተኞቹ እንዳይገቡ በጣሊያን ላይ በሚያደርገው ጫና ሲሆን እጅግ ኣደገኛ የሆኑ ቶርቾች በሰው ላይ ይፈጸማሉ ሲሉ ሪፖርቱ ያስረዳል። (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ዝርዝር ዘገባው ከዚህ ያገኙታል፤ 
Minilik Salsawi in Rome Italy

No comments:

Post a Comment