Friday, November 4, 2016

ወያኔ የደረሰበትን የዋጋ ግሽበት ተከትሎ አንድ ዶላር ወደ ኣርባ ይጠጋጋል የሚል ከፍተኛ ስጋት ኣይሏል።


Image may contain: one or more people
 – ወያኔ የደረሰበትን የዋጋ ግሽበት ተከትሎ አንድ ዶላር ወደ ኣርባ ይጠጋጋል የሚል ከፍተኛ ስጋት ኣይሏል። የሕዝብ ተቃውሞ የሕዝብ ኣስተዳደር ችግር እዳ እና የዋጋ ግሽበት/የገንዘብ ውድቀት የሃገሪቱን ኢኮኖሚ ንዶታል::ለስርኣቱ ቅርበት አላቸው ያሉ ምንጮች በሕዝባዊው ንቅናቄ ጫና ወያኔ ወገቡ እንደተሰበረ እየተናገሩ ነው።
ሕዝባዊ ንቅናቄው በኢትዮጵያ ከተስፋፋ ጀምሮ የውጪ ምንዛሬ እጥረት ሳይሆን የተከሰተው የውጪ ምንዛሬ የለም። ባለፉት ስድስት ወራት የተገኙ የውጪ ምንዛሬዎች በባለስልጣናት ተዘርፈዋል ከውጪ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡ ምንዛሬዎች ወደ ባለስልጣናት ኣካውንት ተዛውረው ሃገር ቤት ሳይገቡ በመንገድ ተጠልፈዋል። የሃገሪቱ ካዝና የውጪ ምንዛሬ ናፍቆታል። የዶላር ያለህ እያለ ነው።
የዶላር ምንዛሬ በሃምሳ ፐርሰንት ኣድጎ ወደ ኣርባ ብር መዳረሻ ይገባል የሚሉ የወያኔ ኣገዛዝ የኢኮኖሚ ኣማካሪዎች መላ መዘየድ ኣቅቷቸው ፈጠዋል። ወያኔ ከፍተኛ ኣጣብቂኝ ውስጥ ይገኛል።ኢንቨስተሮች ገንዘባቸውን ከሃገር ኣውጥተው ጨርሰዋል ብር በጃቸው ያለ ሰዎች ብሩን በዶላር ቀይረው ዞር ብለዋል። የሃገሪቱ ኢኮኖሚ ሊቀበር ሰከንዶች በቀሩበት ሰዓት ላይ ወያኔ የሃሰት ፕሮፓጋንዳውን ቀጥሏል።
ለዚህ ሁሉ ምክንያቱ ሕዝብ በገዛ ኣገሩ ነጻነቱናን መብቱን ተገፎ የበይ ተመልካች መሆኑ ባለስልጣናት እና ዘርማንዘሮቻቸው በዘረፋ ላይ መሰማራታቸው እና ስርአቱ የሚከተለው የተጭበረበረ ፖለቲካ በሃሰት ፕሮፓጋንዳ መታጀቡ ነው::መፍትሄው ደሞ ስልጣን መልቀቅ ብቻ ነው::የወያኔ የፖለቲካና የኢኮኖሚ እንቅስቃሲዎች ተሽመድምዷል። ትግሉም ወሳኝ ምእራፍ ላይ መሆኑ ተረጋግጧል:: ወገን የሞተውን ወያኔን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የቀብር ስነ ስርአቱን የምንፈጽምበት ወቅት ላይ ነን ።ለስርኣቱ ቅርበት አላቸው ያሉ ምንጮች ወያኔ ወገቡ እንደተሰበረ እየተናገሩ ነው::ወያኔ ስልጣኑን ለህዝብ እንዲያስረክብ በተገኘው የትግል ስልት በመሳተፍ የዜግነት ድርሻችንን እነወጣ። #ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment