Monday, November 21, 2016

ግንቦት ሰባት ያለመጠየቅ ህግን አዳብሯል ። ተከታዮቹ የመጠየቅ መብት የላቸውም ! ( ኄኖክ የሺጥላ )

ወያኔ ትግሬ ያለመጠየቅ መብትን ህጋዊ አድርጎ የሚንቀሳቀስ ቡድን ነው ። ህዝቡ የመናገር እና የመጠየቅ መብት እንደሌለው ወያኔ ትግሬ በሚያደርገው ነገሮች ሁሉ አሳይቷል። የመ-ፈራት ህግን አጥቷል ። በዚህም ህዝብ ለረጅም ጊዜ ይፈራው ነበር። ጥቂት ደፋሮች ቆርጠው ተነሱ ! የመለስ አምልኮ ብለው ፃፉ! ፊት ለፊት ተጋፈጡት! በመሳሪያ ሳይሆን በሃሳብ ። እስክንድር ጥይት ተኩሶ አይደለም የታሰረው ። የእስክንድር ጥይቱ ብዕሩ ነው ። ተመስገን ወታደር አቁሞ አይደለም የተፋለመው ! የተመስገን ጦሩ ሃሳቡ ነው። አንዷለም በርሃ ስለገባ አይደለም ለወያኔ ጭንቀት የሆነው ፥ የአንዷለም መልዕክቱ ግን ከቦንብ በላይ ወያኔን አቁስሎታል ። ስለዚህ ሃሳብን የሚፈራው ወያኔ ሃሳብን እያሳደደ ያስር ጀምር ።ሃሳብ እና የማሰብ ነፃነት ለዘላለም ይኖራል ወያኔ ግን አይቀጥልም ይወድቃል ! ውድቀት አንድ
ግንቦት ሰባት ያለመጠየቅ ህግን አዳብሯል ። ተከታዮቹ የመጠየቅ መብት የላቸውም ! ሃሳብ ማንሸራሸር ነውር ነው ። ለምን ማለት ክልክል ነው ! ዝም ብለህ ተከተል! ይህ የግንቦት ሰባት ህግ ነው ! እኛ ስራውን እንሰራለን ፥ አንተ ግን ስለምንም ነገር የማወቅ መብት የለህም! ከተከተልህ ትከተላለህ ! እጠይቃለው ፥ አውቃለው ካልህ ገደል ትገባለህ ! በጥያቄ እና በግንቦት ሰባት መሃከል የቻይናን ግንብ የሚያህል ትልቅ ጥርብ ድንጋይ አለ ። ከተወያየህም የምትወያየው ሰላማያወያይ ነገር ነው ። ይህንን ህግ ያፈረሰ በአድማ እንዳይሆኑ ተደርጎ ይዘለፋል! ይወረፋል ! በፍጥነት ከሰውነት ወደ እንስሳነት ( ወያኔነት ) ይሸጋገራል ! ሃሳቡን ከመረዳት ስሙን ማጥፋት ቀላሉ መንገድ ይሆናል ። ይህንንም ሲያደርጉ ለሌሎች ተከታዮቻቸው መቀጣጫም እንደሚሆን እያሳዩ ነው ። የመፈራት ህግን ልክ እንደ ወያኔ እያፀደቁ ነው ። ትዕቢት ነው ! ውድቀት ሁለት!
ኄኖክ የሺጥላ

No comments:

Post a Comment