Tuesday, November 22, 2016

ሊነበብ የሚገባው – ከእሬቻ ጭፍጨፋ ጀርባ የወያኔ ሴራ ሲጋለጥ – በወያኔ ቅጥረኝነት የኦሮሞን ሕዝብ እያስፈጁ ካይሮ መሸሸጊያ ሆኗል። (ቆንጂት ስጦታው)


ሊነበብ የሚገባው – ከእሬቻ ጭፍጨፋ ጀርባ የወያኔ ሴራ ሲጋለጥ – በወያኔ ቅጥረኝነት የኦሮሞን ሕዝብ እያስፈጁ ካይሮ መሸሸጊያ ሆኗል። (ቆንጂት ስጦታው)
እንንቃ እንንቃ እንንቃ
Image result for irreecha 2016 ዳውን ዳውን ወያኔ
በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ኣመጽ ተከትሎ ወያኔ የተለያዩ የደህንኔት ኣካላቶቹን በተቃውሞዎች መሃል በማስገባት የሕዝብን ሰላም በማደፍረስ ሕዝቡን ኣስፈራርቶ ሰጥ ረጭ ለማድረግ ጉልቤቱን ለመጠቀም እንዲያመቸው በግንባር ቀደምትነት የሚሳተፉ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ወጣቶችን በማሰማራት ቅስቀሳ ካደረገ በኋላ የሃይል እርምጃዎችን ወስዶ ቅስቀሳውን እንደመሩ የተቆጠረላቸውን ወጣቶች ሕወሓት ከጀርባ በሚነዳቸው ዲያስፖራ ሚዲያዎች ጄግኖች በማሰነት ስማቸውን ኣግዝፎ በመናገር የዋሕ ኢትዮጵያውያንን እያጭበረበረ ይገኛል።
በእሬቻ በዓል ላይ “ዳውን ዳውን ወያኔ” ያለው ወጣት ወደ ማይኩ ተጠግቶ የሚፈልገውን በማለት ከቀሰቀሰ በኋላ በወቅቱ የነበረው ሁኔታ ልብ ብሎ ለተመለከተው ሰው ነገሩን ሊያጤነው ይችላል።ማይኩን እንዲቆጣጠር የተሰጠው ክፍተት ማይኩን ለመንጠቅ የተሰጠው ክፍተት እንዲሁም በወቅቱ ጨካኞቹ የሕወሓት ፖሊሶች ምንም አይነት እርምጃ አለማሳየታቸው ሲልም ይህንን ከተናገረ በኋላ ከመድረኩ ጀርባ ከሰወች ጋር ፎቶ ሲነሳ መታየቱ እና በወቅቱ የነበረው ሁኔታ ብዙ ጥርጣሬ ያስጭራል።
እውን ትክክሌኛ ታጋይ ቢሆን ኖሮ ወያኔ በቀላሉ ታልፈዋለች እኔ እስክንድር ነጋ እነ አንዱኣለምና ሌሎች የፖሌቲካ ሰዎች ጋዜጠኞችና ኣክቲቭስቶች ወዘተ እየተለቀሙ በሚታሰሩባት ኣገር ይህ ግለሰብ ተናግሮ ሲወርድ የሚከታተለው አንድ የደህነንት ሰው ወያኔ ቸግሯት አጥሯት ነበር ማለት ጅልነት ነው። በተከታታይ ልጁ በቁጥጥር ስር ውሎ እንደነበር የሕወሓት ካድሬዎች ኣስረግጠው ሲናገሩ ነው ይህ ጉዳይ ከተረሳሳ በኋላ ወጣቱ ግብጽ ካይሮ ገባ ብሎ መናገር ልጁ ያለውን ተልእኮ ኣጠናቆ በወያኔ ድጋፍ ካይሮ መድረሱ ይታወቃል። ይህ ብቻ ሳይሆን ወጣቱ ካርቱም ድረስ በኣውቶብስ ተጉዞ ወደ ካይሮ በኣየር መብረሩን እማኞች ይናገራሉ። ከዚህ በተረፈ እያንዳንዱን እንቅስቃሴ እውቀቱ ያላቸው ሰዎች የሕወሓትን ተንኮል የሚያውቁ ሰዎች ሊያስረዱ ይችላሉ፤ የማይመስል ነገር ለሚስት ኣትናገር። ወያኔ ወጣቶቹን ቀስቃሽ በማድረግ የኦሮሞን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ ከተጠቀመባቸው ነኋላ ወደ ካይሮ ግብጽ ኣሼጋጌራችሀው ካይሮ ግብጽ እንዲሄዱ የተደረገው ደግሞ ግብጽ የኦሮሞን ትግል ትደግፋለች ብሎ ለመወንጀል እንዲያመች ነው። ለምን ኬንያ ሱዳን ጅቡቲ ኣልተመረጡም ???

No comments:

Post a Comment