Thursday, June 23, 2016

በኢትዮጵያ የተደረገው ጸረ – ኢሳያስ ኣፍወርቂ ሰልፍና የወያኔ ሚና


በኢትዮጵያ የተደረገው ጸረ – ኢሳያስ ኣፍወርቂ ሰልፍና የወያኔ ሚና
:- ጸረ – ኢሳያስ ኣፍወርቂ ሰልፍ በኣዲስ ኣበባ ሲደረግ ይህ የመጀመሪያው ኣይደለም በወያኔ ኣቀነባባሪነት አና መሪነት ብሎም ኣጃቢነት የተለያዩ ሰልፎች እና ስብሰባዎች ተስተናግደዋል፤ ወያኔ ስልጣኔን ያስረዝሙልኛል ያላቸውን ጉድጓዶች ሁሉ በመቆፈር ላይ ባለበት በዚህ ኣጣብቂኝ ወቅት ላይ የተባበሩት መንግስታትን የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ተከትሎ ያዙኝ ልቀቁኝ በማለት በ ኤርትራ ላይ አየደነፋ ከመገኘቱም በላይ ለኢትዮጵያውያን በገዛ ኣገራቸው የተከለከሉትን ሰልፍ በ ኤርትራውያን ሽፋን ለፖለቲካ ፍጆታው እየሮጠ ሲገኝ ይህን ጸረ ኢሳያስ ሰልፍ ተቃዋሚዎች ቢያዘጋጁት ኖሮ ግን ኣዲስ ኣበባ በጥይት ታምሳ ትደፈረስ ነበር ።
ወያኔ ለ ኤርትራ ሕዝብ እና በስደት ለሚኖረው ያዘነ በመምሰል ጸረ ኢሳያስ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በመርጨት በኣንድ ጎኑ ደግሞ ኤርትራውያን ወደ ሶስተኛ ኣገር የሚሸጋገሩበትን የጉዞ ሰነድ ስምና ፎቶ እየቀየረ የራሱን ሰላዮች የሆኑ ትግሪኛ ተናጋሪዎችን ወደ አውሮፓና ኣሜሪካ በመላክ እያጭበረበረ ይገኛል። ኣመድ በዱቄት ይስቃል እንደሚባለው የኢትዮጵያ ኣምባገነኖች የኢሳያስን ኣምባገነንነት ሲያማርሩ ይውላሉ።የራሷ አያረረባት የሰው ታማስላለች አንደሚባለው የወያኔ ባለስልጣናት የኢትዮጵያውያን የመኖር ሕልውናና ነጻነት ገፈው ስለ ዐርትራ እና ሱማሊያ ሕዝብ ጭቆና ሲደሰኩሩ ይውላሉ። መጃመሪያ ሰልፉን ያዘጋጀው ወያኔ ሲሆን በሰልፉ ላይ ኣብዛኛው ተሳታፊዎች የ ኤርትራ ባንዲራ ያነገቡ የሕወሓት ሰዎች መሆናቸው ኣደባባይ ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው።ወያኔ ከፊት ኤርትራውያንን ስደተኞች ለፎቶ በማስቀደም የፖለቲካ ፍጆታውን ሲሰራ ውሏል።
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.

No comments:

Post a Comment