Wednesday, June 8, 2016

ፍትሕን ማግኘት የምንችለው ስርዓቱን ታግለን ስናፈርስ ብቻ ነው።


ፍትሕን ማግኘት የምንችለው ስርዓቱን ታግለን ስናፈርስ ብቻ ነው።በዛሬው እለት የወያኔው ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት እነብርሃኑ ተክለያሬድን በተመለከተ ከዳኛው በኩል ከስርዓቱ ገዢዎች የወረደው ውሳኔ “መከላከያ ምስክር ማሰማት የለባችሁም ስለዚህ ለፍርድ ብይን ሃምሌ ፩፫፣ ፪፻፰ ቅረቡ”መባሉ በተደጋጋሚ የምናየውን የፍትሕን መቀበር እያሳየን ነው።ይህ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ኣዲስ ባይሆንም የሕግ የበላይነት አለመከበሩን ካወቅን ስርዓቱ ፈርሶ የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ወገባችንን አጥብቀን እንታገል፥ ፍትህ ካለ ሰላም አለ::ፍትህ ካለ እድገት አለ:;ፍትህ ካለ እስር ቤቶች በንጹሃን አይሞሉም:: ፍትህ ካለ ነጻነት እና መብት አለ:; ፍትህ ካለ የሚሸማቀቅ አይኖርም::ፍትህ ከተረጋገጠ ሕጎች ሁሉ በበላይነት የሕዝብ ይሆናሉ::ይህ ሁሉ የሚረጋገጠው በኛ ለኛ ከኛ ነው::እኛ አዎ እኛ በአሁን ወቅት እና ጊዜ ላይ ቆም ብለን ካሰብን የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር በራሳችን ትግል ነጻነታችንን እና መብቶቻችንን ታግለን ማረጋግጥ እንዲሁም አምባገነኖችን ላንዴና ላያዳግም መደምሰስ ነው::
በኢትዮጵያችን የሰብ አዊ መብት ጥሰት የመብቶችና የነጻነቶእ ገፈፋ የፍትህ ድንቁርና መንሰራፋቱን እናውቃለን ደጋግመን ብናወራው ለቀባሪው ጆሮ ፍሰት መፍጠር ካልሆነ በስተቀር ምንም አይፈይድም የሚፈይድልን ነገር ቢኖር እነዚህን እኩይ ተግባራት ታግለን በማስወገድ የሕግ የበላይነትን እና የራሳችንን ነጻነት እና መብት ማስከበር ነው:: አሁን ማወቅ ያለብን ይህንን ብቻ ነው::ፍትህ ፈላጊ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እስከፈለግን ድረስ ማንም ሰው ወይም አካል ከህግ በላይ ሊሆን አይችልም:: ህገ ወጥነትን መታገስም በራሱ ወንጀልን ማበረታታት ነው:: ስለዚህ የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የማድረገ ትግላችን ተጠናክሮ መቀጠል አለበት:;ለሕግ የበላይነት የምናደርገው ትግል በተግባራዊ ስራዎች እና ግንዛቤን ከበፊቱ በበለጠ በመፍጠር ሕዝባዊ ሰቆቃዎችን ለማስቀረት ታላቁን ስኬት ከግብ ለማድረስ ከጀመርነው ጉዞ ማፈግፈግ አያስፈልግም ::ሕዝቡ በሃገሪቱ ላይ የሚካሄደውን እና እየተካሄደ ያለውን የወያኔዎች አምባገነን አገዛዝ የፈጠረውን ጸረ ፍትህ አካሄድ አብጠርጥሮ ያውቃል ::ይህ ማለት ደሞ የለውጥ ሃይሎች የሚጠበቅባቸውን የለውጥ ስራዎች በመስራት ትግሉን ከግብ ለማድረስ አስፈላጊዉን የትግል መንገዶችን በመጠቀም ሕዝብን ከጎን በማሰለፍ ድሉን ማረጋገጥ ይጠበቅብናል::
በሃገራችን የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የምእራባውያንን አሳሳቢ በሚል የታጀበ መግለጫ አሊያም ድጋፍ መጠበቅ ለኛ ምንም አይፈይድም::እና ጠንክረን ከታገልን በአምባገነኖች ጫና ስር የወደቀውን ሕዝባችንን ነጻ ለማውጣት በምንገፋው ትግል ላይ የምናሳየው የትግል ታማኝነት እና ስኬት ምእራባውያንን ራሳቸውን ልንማርክ እና ሳንጠይቃቸው እርዳታውንን ለብሄራዊ ጥቅማቸው ሲሉ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ሳይታለም የተፈታ ነው:: ስለዚህ እኛ ራሳችን በጋራ ሆነን ይህንን አምባገነን ስርአት ለመጣል ወደፊት መገስገስ ያለብን እኛው በኛ ሲሆን የሕግ የበላይነት አለመከበሩን ካወቅን የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ወገባችንን አጥብቀን እንታገል::ፍትሕን ማግኘት የምንችለው ስርዓቱን ታግለን ስናፈርስ ብቻ ነው። ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬
Minilik Salsawi's photo.

No comments:

Post a Comment