Saturday, June 18, 2016

የደሕንነት ቢሮ መርማሪ ግድያ = 2- ዲና ሙፍቲ ድንቁርና እና አደርባይነት ክፉ እርግማን ነው።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ሁለት ኣስገራሚ ጉዳዮች ባለፉት ሁለት ቀናት ሰምተናል ኣይተናል ኣንዱ በኣዲስ ኣበባ ደህንነት ቢሮ ውስጥ በኣሮጌ ኣይሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ በሚገኘው የምድር ለምድር እስር ቤት ውስጥ በተማረረ እስረኛ ባልተጠበቀ ሁኔታ የተገደለው የደህንነቱ መርማሪ ኪሮስ ሃብተማርያም ኣረጋይ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ድንቁርና እና ኣደርባይነት የተጠናወተው በኬንያ ቴሌቭዥን ላይ የተላለፈው የኢትዮጵያና የኤርትራ አምባሳደሮች መወናጨፍ ነው፥ ስለ ኤርትራው ኣምባሳደር ባይመለከተኝም በኢትዮጵያ ስም ግን የሚነግደው አምባሳደር ግን ምን ያህል ዶንቆሮ እና ኣደርባይ መሆኑን ማሳየቱ የወያኔን ኣገዛዝ ጸረ ኢትዮጵያ አቋም ቁልጭ ኣድርጎ ያሳያል።
አሃዱ ካልኩት የደህንነት መርማሪው ባልተጠበቀ ሁኔታ መገደል ስጀምር ኪሮስ ሃይለማርያም ኣረጋይ በኣሮጌ ኣይሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ በሚገኘው የምድር ለምድር እስር ቤት ውስጥ የተለያዩ የግፍ ምርመራዎችን ሲያደርግበት የነበረ እና ከኬንያ ታፍኖ ክ5 ወር በፊት የመጣ ኣራርሳ ሞቲ የተባለ የቀድሞ መንግስት የኣየር ወለድ ኣባል በሆነና አድሜው 58 በሚገመት ግለሰብ ተገሏል፤ ኣራርሳ ሊገለው የቻለው መርማሪው ባለው ሁሉ ተስማምቶ የተሰጠውን የከተማ ተልዕኮ ለመወጣት እንዲዘጋጅ ፈተውት በነበረ ሰዓት ባልተጠበቀ መልኩ ድንገት በወሰደው እርምጃ ሲሆን ወዲያው ገሎት ራሱም ላይ እርምጃ በመውሰድ መሞቱ ታውቋል።ምንሊክሳልሳዊ
ክልቱ የምለው ደግሞ ድንቁርና እና ኣደርባይነት የተጠናወተው በኬንያ ቴሌቭዥን ላይ የተላለፈው የኢትዮጵያና የኤርትራ አምባሳደሮች መወናጨፍ ነው፥ኣይቶ በየነን ለጊዜው እንርሳው እና አቶ ዲና የተባለውን የኣምባገነኖች ኣገልጋይ ላይ እንዝመት ዲና ሙፍቲ ለሁለት መንግስታት ኣደርባይ ሲሆን የዲፕሎማቲኩ መስክ ደንቆሮ ነው፥ ድህነትን አየተዋጋን ነው በሚል ሽፋን በሙስና የተዘፈቀው የወያኔ ኣገዛዝ ዛሬም በልማት ስም ጦርነትን እና ዘረፋን እያራመደ መሆኑ ኣምባሳደሩ ኣንጸባርቆታል፥ የኦሮሞ ልጆች ግድያ ሽምጥጥ ኣድርጎ የካደው ኣምባሳደር ተብየው ዲና የሕወሓት እና የሻእቢያን መሰረታዊ ማንነት አና ኣሁን ያለበትን የደረጃ ሂደት በፍጹም የማያውቅ እውቀት ኣልባ መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል፤ለሚጠየቀው ጥያቄ መልስ ለመስጠት እንደማይችል ልማትንና ድህነትን በሽፋንነት መጠቀሙ ድንቁርናውን ኣሳብቆበታል።
ኤርትራ ከጎረቤቶቿ ጋር ትጋጫለች ለሚለው ከግጭቱ ጀርባ ሕወሓት እንዳለ ሲጋለጥ በቂ መልስ መስጠት ኣለመቻሉ የኣለቆቹን ገመና እንዲጋለጥ ያደረገ ሲሆን ኦሮሞነቱን ሲናገር ግን ኣለም ያመነውን የኦሮሞ ልጆች ግድያ ግን እንዳልተደረገ መደስኮሩ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በሃገሪዉ እያለ የኤርትራን ጉዳይ ለማማሰል መሞከሩ ት ዝብት ላይ ጥሎታል እንዲሁም ኤርትራ ዜጎቿን የምታሰዽ ኣገር ናት ብሎ ሲናገር ከተለያዩ የስደተኛ ጣቢያዎች በ ኤርትራዊነት ወረቀት ተደብቀው ኣውሮፓና አሜሪካ ስለሚላኩ ትግሪኛ ተናጋሪ የሕወሓት ሰላዮች የሆኑ የትግራይ ልጆች መሆናቸውን እንደማያውቅ ሲሸፋፍን ኣስተውለናል፤ በኣጠቃላይ የሁለቱ ኣምባሳደሮች በስቱዲዮ ተገናኝተው ተወያዩ ሳይሆን ተወናጨፉ የሚባል ሲሆን ድንቁርና እና አደርባይነት ክፉ እርግማን ነው። ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment