Wednesday, June 29, 2016

የኣቶ ሃብታሙ ኣያሌው ጤና የመጨረሻው ኣሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

የቁም እስረኛው አቶ ሃብታሙ ኣያሌው ጤና የመጨረሻው ኣሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ከሃገር ውጪ እንዳይታከም በ አቶ ጸጋዬ በርሄ የወያኔ ደህንነት ኣማካሪ ባለስልጣን በኩል የጠጣለው እገዳ አልተነሳለትም፤ በኣሁን ወቅት በኮማ ውስጥ ይገኛል።
ወጣት ሀብታሙ አያሌው ህይወቱ አደጋ ላይ ነው ወጣት ፓለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው በአሁኑ ሰአት በጠና ታሞ ሀኪም ቤት መግባቱን በአቅራቢያ ባሉ ሰዋች ሰምቻለሁ በዚህ ሰአት ሀኪም ቤት ይገኛል ሁላችንም ፀሎት ልናረግ ይገባል ህክምናውን በሀገር ውስጥ ማድረግ ባይቻል መንግስትን ከሀገር ውጪ ለመታከም ቢጠይቅም መንግስት ግን የቁም እስረኛ በማረግ ይሄን ወጣት ለከፍተኛ ህመም ዳርጎታል በዚህ ሰአት የሀብታሙ አያሌው ህይወት አደጋ ላይ ነው በጠና ታሞል ጀግኖችን መጠበቅ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሀላፌነት ነው

No comments:

Post a Comment