Tuesday, December 13, 2016

ኮረኔል ሓጎስ ምስግና ለምን ተገደለ ማንስ ገደለው


ኮረኔል ሓጎስ ምስግና
ኮረኔል ሓጎስ ምስግና
ኮረኔል ሓጎስ ምስግና ለምን ተገደለ ማንስ ገደለው Konjit Sitotaw
*============================
ኮረኔል ሓጎስ ምስግና አሙዋሙዋት እስከዛሬ ምስጢር እንደሆነ ወላጅ እናቱ በሃዘን አዲግራት ባለ መኖሪያቸው በሃዘን ታስረው ዛሬ ላይ በህይወት ይኑሩ አይኑሩ የማውቀው ባይኖርም በዚህ ልጃቸው የሚተዳደሩ ነበሩ ። ኮነሬል ሓጎስ ባንድ ወቅት ወላጅ እናቱ (እማማ ሓዳስ) የሚልክላቸው ተቆራጭ ይቋረጣል ። ከዛን ጊዜ ጀምሮ በአለም አቀፉ ቢሮ ፤መቀለ ካለው መከላከያ እንዲሁ፤ አዲስ አበባ ካለው መከላከያ ተስፋ ሰጭ ወሬ ያጣሉ ።
ሆስፒታሎችን ሳይቀር እንዲመለከቱ ፍለጋው እንዲቀጥል ይሆናል ። (አልተሳካም)መጨረሻ ላይ አስከሬኑ እዚያው ዳርፉር UN የዩኤን ሰንደቅ ለብሶ በስም የማይታወቅ ወታደር ተብሎ እንደ ተራ ከወር በፊት እንደቀበሩት የአለም አቀፉ ቢሮ አስታወቀ ።
ኮነሬል ሓጎስ ወላጅ እናቱ (እማማ ሓዳስ)
በትግራይ ኢሮብ ወረዳ የተወለዱት የቀድሞ የህወሃት ታጋይና የመከላከያ መኮንን ኮ/ል ሃጎስ ሆን ተብሎ ከኌላ በተተኮሰባቸው ጥይት ጭንቅላታቸውን ተመተው መሞታቸው ሲታወቅ፣
የግድያው ምክንያት
============
ለግድያ ያበቃው ምክንያት በጥቂት ከፍተኛ ጄኔራሎች የሚፈፀመውን ሙስና በተለይ በሰላም አስከባሪነት በሚሰማራው ወታደር የሚደርስበት ብዝበዛን በመቃወሙ እንደሆነ ምንጮች አመልክተዋል። በ1996 ዓ.ም መለስ በመራው ስብሰባ “ከደርግ በምን ተሻልን?” በማለት እንዲሁም የባድመን ጉዳይ በመቃወም መለስንና የስርአቱን አካሄድ በማውገዙ ከሰራዊቱ ተገልሎና በቁም እስረኛ እንደቆየ ምንጮች አስታውሰዋል።
በሰላም ማስከበር ለሚሰማራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የተባበሩት መንግስታት ለአንድ ወታደር ወርሃዊ ደመወዝ 1 ሺህ 70 ዶላር ይመድባል። በሱዳን ለአንድ አመት ብቻ እንዲቆይ ሲደረግ በወር 37 ዶላር ብቻ “የኪስ” ተብሎ ይሰጠዋል። ዋናው ገንዘብ አገር ቤት እንደሚከፈል በጄኔራሎች ከተነገረው በኋላ ሰራዊቱ አገር ሲመለስ “ለመከላከያ ሚኒስቴር” በሚል 60 በመቶ ይቆረጣል። የአመት 283 ሺህ ብር ሲሆን፣ 193 ሺህ ብር ገደማ ተቆርጦ ለወታደሩ 90 ሺህ ብር እንደሚከፈለው ይነገረውና ክፍያውም እየተቆራረጠ በተለያየ ወራት እንደሚፈፀም ምንጮች አብራርተዋል። ይህን ብዝበዛ የተቃወሙ የላይቤሪያ ዘማቾች በ97 በፍቼ መስመር መንገድ ዘግተው ፍትሃዊ ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል። ከሰራዊቱ ከሚመዘብሩት አንዱ ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀል ሲጠቀሱ ቦሌ ቴሌ መድሃኒአለም በ90 ሚሊዮን ብር ህንፃ አስገንብተው እንደሚያከራዩ ይታወቃል። ኮ/ል ሓጎስ ለግድያ ያበቃው የእነጄ/ል ዮሃንስን ከፍተኛ ምዝበራ አጥብቆ በመቃወሙ እንደሆነ ምንጮች እየጠቆሙ ነው። በ1993 ጄኔራል በርሀ በቅፅል ስሙ ሻእቢያ ም ሆን ተብሎ ከነባለቤቱ መገደሉ የሚታወቅ ነው

No comments:

Post a Comment