Wednesday, August 10, 2016

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በወያኔ የተካሄደውን ግድያ ተከትሎ ኣጣሪ ቡድን ለመላክ የሕወሓት ኣገዛዝን ጠየቀ



የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት እና ተቃዋሚ ባለሥልጣናት ከ90 በላይ ሰላማዊ ሰልፈኞች ቅዳሜና እሁድ ላይ በደህንነት ኃይሎች ‘ና ወታደሮች መገደላቸውን ተከትሎ ወደ ክልሎች ጉዳዩን የሚያጣራ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች እንዲያስገቡ እንዲፈቀድለት የክልል እና ፌዴራል ባለስልጣናት ጠየቀ።በጉዳዩ ዙሪያ የመጀመሪያ አስተያየታቸውን የሰጡት ዘይድ ራድ አል ሁሴን, የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር, በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ላይ ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል መጠቀም ክሶችን ምርመራ አስመልክቶ ከክልል እና ከፌዴራል ባለስልጣናት ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
“በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የቀጥታ ጥይቶችን መጠቀም,በየከተሞቹ ዞሮ ማጣራት ከባድ ቢሆንም የተቻላቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ኮሚስህነሩ ለሮይተርስ ገልጸውበሳምንቱ መጨረሻ ላይ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ ፀረ-መንግስት መፈክሮች በማድረግ ሰልፈኞቹ ባንድራችን ነው ያሉትን በማውለብለብ የመንግስትን ባንድራ እንደማይቀበሉ አሳይተዋል፤ ዘብጥያ የወረዱ የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን እንዲለቀቁ ጥያቄ አቀረቡ።ሪፖርቱ እንደሚጠቁመው ግድያ ላይ መረጃ ለማግኘት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል ሲሉ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።ስለዚህም በበቂ ሁነእታ ቦታው ድረስ ሄዶ ማጣራት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አስምረውበታል።
“ስለዚህ በጸጥታ ሃይሎች ላይ ምን እንደተከሰተ ለማወቅ እነርሱ ከመጠን ያለፈ ኃይል በመጠቀም ለምን እንደፈለጉ ለመጠየቅሕዝቡስ ጋር ያለውን መሰረታዊ ሁነእታ እና የችግሩና እርምጃውን መጠን ለማጣራት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በቦታው ተገኝተው እንዲያጣሩ የክልል እና የፌዴራል መንግስታት እንዲፈቅዱ ምርመራ እንዲደረግ ስንጠይቅ በሰላማዊ ሰልፉ ተይዘው የታሰሩ ሁሉ እንዲፈቱ እናሳስባለ ብለዋል ኮሚሽነሩ።

No comments:

Post a Comment