Sunday, August 28, 2016

ጎጃም ጀግናው የዱርቤቴ ሕዝብ ትግሉን በመቀላቀል ወያኔን በቃኸኝ ብሎታል ።ለ3 ቀን የስራ ማቆም አድማ ደብረታቦር፣ ወረታ እና አዲሥ ዘመን


ከጎንደር ወልድያና ባሃርዳር መንገዶች ተዘግተዋል። ጎጃም ጀግናው የዱርቤቴ ሕዝብ ትግሉን በመቀላቀል ወያኔን በቃኸኝ ብሎታል ።ለ3 ቀን የስራ ማቆም አድማ ደብረታቦር፣ ወረታ እና አዲሥ ዘመን
በቲሊሊ ከተማ ህዝቡ እስረኞችን አስፈትቷል። በህዝቡና በፖሊስ መካከል የተፈጠረውን ፍጥጫ ቄሶቹ ታቦት ይዘው መሀል ላይ በመግባት ህዝቡ እስረኞችን ይዞ እስካሁኗ ሰአት ተቃውሞውን እያቀረበ ይገኛል ።በደብረታቦር፣ በወረታ እና በአዲሥ ዘመን ከተሞች ከዛሬ ጀምሮ ለ3 ቀን የስራ ማቆም አድማው የተጀመረ ሲሆን ደብረታቦር ከተማ ፀጥ ረጭ ብላለች።በአገው ምድር እንጅባራ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ከፍ ተደርጎ ተሰቅሏል።ዳንግላ፣ ዱርቤቴ፣ ኮሶበር ተቃውሞ በማድረግ ላይ ናቸው፥፥ በኮሶበር ፌደራሎች በህዝብ ላይ እየተኮሱ ነው፥፥ ኣንድ ሰው መገደሉንና ሶስት መቁሳላቸውን መረጃ ደርሶናል፥፥ በዳንግላ የመዘጋጃው ዘበኛ በህዝብ ላይ በመተኮሱ ቤቱ ተቃጥሏል፥፥ የደንበጫ ህዝብ የወታደሮችን እንቅስቃሴ ለመግታት ድልድይ በመዝጋት ተቃውሞውን እየገለፀ ነው::

የበላይ ልጆች በጎጃም የሚገኙ ድልድዮችን በሙሉ እየዘጉ ነው። ወያኔ ወገቡ ተቆርጧል። ከዚህ በኃላ ወደ ጎጃም ጎንደር በመኪና የሚደረገው ጉዞ ቆሟል። ጎንደር ወሎ ሸዋም ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጅቱን ጨርሷል። ድሉ በእጃችን እየገባ ነው!
የደቡብ ጎንደሯ እሥቴ(መካነ እየሡሥ) ከተማ የአማራ ተጋድሎውን በሥራ ማቆም አድማ ተቀላቀለች። በመካነ እየሡን ከተማ አገልግሎት ሠጭ ተቋማት በሙሉ ተዘግተዋል። በነገራችን ላይ መካነ እየሡሥ ከተማ ከዚህ በፊት የአማራ ተጋድሎን በመቀላቀል ግንባር ቀደሟ ነበረች። ከዚህ በፊት በሠላማዊ ሠልፍ የተጀመረው ተቃውሞ ዛሬ ከቤት ባለመውጣት ተቃውሞ ተደግሟል!በደቡብ ጎንደር ወረታ ከተማ የሥራ ማቆም አድማውን ተከትሎ ሱቆችንና ሆቴሎችን ለማሥከፈት የተደረገው ሙከራ ወደ ግጭት ማደጉን ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በአሁኑ ሠዓት የከተማው ህዝብ ወደ አደባባዮች የወጣ ሲሆን በአጸፋው የመንግሥት ታማኞች በየአቅጣጫው እየተኮሡ እንደሆነ ለማወቅ ችለናል ወረታ፤ ሃሙሲትና አመድበር ቀውጢ ተፈጥሯል!
የጉማራና ርብ ድልድዮች በተጋድሎ ወጣቶች ቁጥጥር ስር ወድቀዋል። ከጎንደር ወልድያና ባሃርዳር መንገዶች ተዘግተዋል። የገጠሩ ህዝብ ከነትጥቁና ፈረሱ እየፎከረና እየሸለለ ወደ ከተሞቹ ገብቷል፤ ከከተማው ወጣቶች ጋር በመሆንም አካባቤውን ተቆጣጥሯል። ሁኔታው ሁሉ በቃ ተቀይሯል።
ደብረታቦር አሁንም ፀጥ ብላለች። ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም።ፎገራ ወረታ ከተማ ታሪክ ተቀየረ፡፡ ጦርነቱ ተጀምሯል፡፡ ተደራጅተው የቆዩ ወጣቶች የገጠሩም የከተማውም ዝናሩን እያገማሸረ ታጥቆ ወጥቷል፡፡ጉጅሌና ፖሊስ ድራሹ ጠፍቷል፡፡ እየተቧደነ መደበቂያ ፍለጋ ላይ ነው፡፡ ሀሙሲቶችና የጉማራ ገበሬ ታጥቆ እየገባ ነው፡፡ ከደብረታቦር የታጠቁ ወጣቶች ወረታ ገብተዋል፡፡
 አዊ ዞን ከፍተኛ ተቃውሞ እየተካሄደ ነው ፤በጣም ከልክ ያለፈ ተኩስ አለ። ምን ያህል ሰው እንደሞተ እና እንደቆሰለ ኣልታወቀም። 
.

No comments:

Post a Comment