Saturday, August 27, 2016

ሕወሓት በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ቀጥሏል፤ ሕወሓት መስጊድ ውስጥ በተሰበስቡ ወጣቶች ላይ ቦምብ ወረወረ

 ሕወሓት በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ቀጥሏል። ሕወሓት መስጊድ ውስጥ በተሰበስቡ ወጣቶች ላይ ቦምብ ወረወረ። 

ለቅሶ የሚቀመጠው የሞተበትን ሃዘንተኛ የሚያሰቃየው የሕወሓት መንግስት በኦሮሚያ ክልል ግድያውን መቀጠሉን መረጃዎች ሲጠቁም በዛሬው እለት በምእራብ ሃረርጌ ማሳላ ወረዳ ልዩ ስሙ ዋልተሲስ በሚገኘው መስኪድ ላይ የኣግዓዚ ወታደሮች በመስኪዱና ውስጥ በነበሩት ሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ታወቀ።
በመስኪድ ውስጥ የነበሩ ወጣቶችን በመክበብ ለመያዝ ሲሞክሩ ሲከሽፍባቸው መስጊዱ ላይ ቦምብ በመወርወር ያቃጠሉት ሲሆን በውስጡ የተሰበሰቡ ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱ ሲታወቅ የሞትና የቁስለቱ ጉዳት ብዛት እስካሁን ለማረጋገጥ ኣልተቻለም፤ እስካሁን የታወቀው ኣብዲ ኢማም የተባለው ወጣት ከነሕይወቱ መቃጠሉ ሲሆን በርካቶች ላይ ከፍተኛ የእሳት ኣደጋ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

No comments:

Post a Comment