Monday, August 29, 2016

ውስጥ ውስጡ ሚኒስትሮች እየተነሱ ነው፤


የከተማ ልማት ሚኒስትሩ ተነስተው ወደ ጠ/ሚ ቢሮ በኣማካሪነት ተዘዋውረዋል።
ውስጥ ውስጡ ሚኒስትሮች እየተነሱ ነው፤ ወያኔ በለመደው ፕሮፓጋንዳ መሰረት በራስ ፈቃድ ያሰኛል። ዛሬ በከተማ ልማት ሚ/ር ወርሃዊ የሠራተኞች ስብሰባ ላይ ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ‹‹ከሌላ ከምትሰሙ ልንገራችሁ፣ ከስልጣኔ በራሴ ጥያቄ ለቅቄ ወደ ጠ/ሚ/ሩ አማካሪነት ተዛውሬኣለሁ ›› ሲሉ በተሰበረ ልብ የኑዛዜ ቃላቸውን አሰምተው ‹ጠንክራችሁ ሥሩ› የሚል ማሳሰቢያ ተናግረዋል፡፡ ይህ ማለት አቶ መኩሪያ ከአገርና ህዝብ ጥቅም የራሳቸውን ጥቅምና ድሎት ካስቀደሙ –ሥልጣናቸውን ለኪራይ ሰብሳቢነት ከተጠቀሙ ለኢህአዴግ መበስበስ ምክንያት ከሆኑ ባለሥልጣናት አንዱ ናቸው ማለት ነው– በወያኔያዊ መግለጫው መሰረት፡፡ #MinilikSalsawi

No comments:

Post a Comment