Tuesday, January 31, 2017

የኢሳያስ መንግስት ለቴዎድሮስ አድሃኖም የአለም ጤና ምርጫ የድጋፍ ድምፅ በመስጠት የቁርጥ ቀን ወዳጅነቱን አረጋግጧል፡፡ ( Tesfaye Ru )

   


የኢሳያስ አፈወርቂ ጠላት አማራ እንጂ ወያኔ አለመሆኑን የኢሳያስ መንግስት ለቴዎድሮስ አድሃኖም የአለም ጤና ምርጫ የድጋፍ ድምፅ በመስጠት የቁርጥ ቀን ወዳጅነቱን አረጋግጧል፡፡( Tesfaye Ru )

ኤርትራ ላይ ያከማቸው ቁጥር አልባ የትህዴን ሰራዊት ዝግጅት ከአማራ ጋር ለሚደረግ የወደፊት ጦርነት ነው፡፡ ግንቦት 7ን የሚደግፈው፤ በግንቦት 7 በኩል አማራን ለመውጋት ሳይሆን፥ የአማራ ቁጣ ቀን ተሸሽጓ ማምለጫ ከለላ እንዲሆነው ይመስላል፡፡ ግንቦት 7 ለወያኔና ሻዕቢያ የመጨረሻው ከጥፋት የማምለጫ ካርድ ሊሆን ይችላል፡፡

ስልጣን ከ2ቱ ትግሬዎች ሲያመልጥ፥ የግንቦት 7 ፖለቲካ ን የይቅርታ መንገድ አድርገው ለመጠቀም ይፈልጋሉ፡፡ይህ ማለት ግንቦት 7 የአማራ ህዝብ ጠላት ነው ማለት ሳይሆን፥ በአንድነት ስም ዳግም ከኢትዮጵያ ጋር ለመቀጠል በር ከፋች መርህ ስላለው ነው፡፡ የማይቀረው እውነታ ይህ ነው፦ ወልቃይት አማራ ነኝ ማለት በጀመረበት ሰዓት፤ ይሮቦችም እኛም አማራ ነን ማለት ጀምረው ነበር፡፡ ይህ ምን ማለት ነው፦ ከሰሜናዊ ትግራይ እስከ ምፅዋ ወደብ የሚኖሩ ህዝቦች እኛም ከአማራ ጎን እንሰለፋለን ማለታቸው ነው፡፡

ይህ ማለት፦ አክሱም የአማራ ነው፣ ወልቃይትም የአማራ ነው፣ ምፅዋም የአማራ ነው፣ ሃሰብም የአማራ ነው፡፡ መቀሌና አስመራ ግን ብትፈልጉ ገደል ግቡ ማለት ነው፡፡መጪዋ ኢትዮጵያ የአሰመራና የመቀሌ ትግሬን በወገንነት ሳይሆን በጠላትነት የፈረጀች አዲስ አገር ልትሆን የምትችልበት ሰፊ አማራጭ አለ፡፡

No comments:

Post a Comment