Tuesday, January 24, 2017

የህብር ሬዲዮ ጥር 14 ቀን 2009 ፕሮግራም

<…ተቃዋሚዎች ጋር እንደራደራለን የሚሉት እነሱ ቀለብ ከሚሰፍሩላቸው የስም ተቃዋሚዎች ጋር አንዳንዶችም በስልክ እየተጠሩ ገና ለገና እንታሰራለን በሚል የሚደረግ ሕወሃት/ኢህአዴግ ለራሱ ፕፖፖጋንዳ የሚያደርገው እንጂ ዶ/ር መረራ፣በቀለ ገርባን ጨምሮ በርካታ የተቃዋሚ መሪዎችና አባላት፣ጋዜጠኞች ታስረው ተቃዋሚ አጥፍተው ያው ለምዕራባውያን ፍጆታ ካልሆነ እንዲህ ያለው ማታለያ አይሰራም…>
– አክቲቪስት ነጌሳ ኦዶ ዱቤ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ዓለም አቀፍ የድጋፍ ቡድን ሊቀመንበር ሰሞኑን ገዢው ፓርቲ በኢትዮጵያ ከተቃዋሚዎች ጋር እያደረኩ ነው ስለሚለው ውይይትና ድርድር በተመለከተ ከህብር ተጠይቀው ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ( ክፍል አንድን ያድምጡት)
<…የሕወሃት ባህሪ ከበረሃ ጀምሮ የሚከተለው ተመሳሳይ ስልት ነው። ሲጨንቀው እንደራደር ይላል በእውነተኛ ድርድር አያምንም። በረሃ ለድርድር የጠሯቸውን በተኙበት ገሏል። ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ሚከተሉት ያንኑ ነው። አሁን እነሱ ድርድር የሚሉትን ማጭበርበሪያ ማንም አይቀበለውም ይልቁን ራሳቸውን ነው የሚሸውዱት … ይሄ ሁሉ ተቃዋሚ ታስሮ ና ተደራደር ስትባል ከረቫት አስረህ መሄድ ክህደት ነው …>
– አክቲቪስት መስፍን አማን በኔዘርላንድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበርና ከቀድሞ የቅንጅት መሪዎች አንዱ ገዢው ፓርቲ እያደረኩ ነው ስለሚለው ድርድር ከሰጠን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ክፍል አንድን ያዳምጡት)
የአሜሪካው አዲሱ ፕ/ት ዶናልድ ትራም ስልጣን መጨበጥን ተከትሎ በአለም ላይ የተስተዋሉት የድጋፍ፥የተቃው እና የስጋት አስተያየቶች ሲቃኙ (ልዩ ጥንቅር)
<…የአማራ ጉባዔ ዓላማ አማራው በአማራነቱ ራሱን ችሎ የሚደራጅበትን ትልቅ መሰረት ለመጣል ነው። የአማራ ኮሚኒቲን ለማጠናከር ነው። በጉባዔው ላይ የተለያዩ የአማራ ድርጅቶችና ምሁራን ተገኝተው የተለያዩ ገለጻዎችን አድርገዋል። በስብሰባው ሰፊ ግንዛቤ የሚያስገኝ ስራ ሰርተናል ።አገር ቤት ላለው ትግል ጉባዔው ምን ፋይዳ ያደርጋል ለተባለው ግን …> አቶ ውብሸት መኮንን በሜሪላንድ ሲልቨር ስፕሪንግ የተደረገው የአማራ ጉባዔ አስተባባሪዎች አንዱ ስለ ጉባዔው ጠይቀናቸው ከተናገሩት(ቀሪውን ያድምጡት)
ከኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አመራር ከዶ/ር ኤርሚያስ አለሙ እና ከኢትዮጵአ ብሄራዊ የሽግግር ም/ቤት ሊቀመንበር አቶ ስለሺ ጥላሁን ጋር ያደረግነው ቃለ መጠይቅ ( ሁለተኛ ክፍል )
ሌሎችም
ዜናዎቻችን
ሕወሓት/ኢህአዴግ ተቃዋሚ አጥፍቶ የሚያደርገውን የይስሙላ ድርድር ሕዝቡ እንዳማይቀበለው ተገለጸ

No comments:

Post a Comment